1ነገር ግን ዳግመኛ በኀዘን ወደ እናንተ እንዳልመጣ ስለ እኔ ቆረጥሁ።
1But I have judged this with myself, not to come back to you in grief.
2እኔስ ባሳዝናችሁ፥ እንግዲያስ በእኔ ምክንያት ከሚያዝን በቀር ደስ የሚያሰኘኝ ማን ነው?
2For if *I* grieve you, who also [is] it that gladdens me, if not he that is grieved through me?
3ደስ ሊያሰኙኝ ከሚገባቸውም በመምጣቴ ኀዘን እንዳይሆንብኝ ይህንኑ ጻፍሁላችሁ፥ ደስታዬ የሁላችሁ ደስታ ነው ብዬ በሁላችሁ ታምኜአለሁና።
3And I have written this very [letter] [to you], that coming I may not have grief from those from whom I ought to have joy; trusting in you all that my joy is [that] of you all.
4በብዙ መከራና ከልብ ጭንቀት በብዙም እንባ ጽፌላችሁ ነበርና፤ ይህም እናንተን አብዝቼ የምወድበትን ፍቅር እንድታውቁ እንጂ እንዳሳዝናችሁ አይደለም።
4For out of much tribulation and distress of heart I wrote to you, with many tears; not that ye may be grieved, but that ye may know the love which I have very abundantly towards you.
5ነገር ግን ማንም አሳዝኖ ቢሆን፥ እንዳልከብድባችሁ፥ በክፍል ሁላችሁን እንጂ እኔን ያሳዘነ አይደለም።
5But if any one has grieved, he has grieved, not me, but in part (that I may not overcharge [you]) all of you.
6እንደዚህ ላለ ሰው ይህ ከእናንተ የምትበዙት የቀጣችሁት ቅጣት ይበቃዋልና እንደዚህ ያለው ከልክ በሚበዛ ኀዘን እንዳይዋጥ፥
6Sufficient to such a one [is] this rebuke which [has been inflicted] by the many;
7ይልቅ ተመልሳችሁ ይቅር ማለትና ማጽናናት ይገባችኋል።
7so that on the contrary ye should rather shew grace and encourage, lest perhaps such a one should be swallowed up with excessive grief.
8ስለዚህ ከእርሱ ጋር ፍቅርን እንድታጸኑ እለምናችኋለሁ፤
8Wherefore I exhort you to assure him of [your] love.
9ስለዚህ ደግሞ ጽፌ ነበርና፤ በሁሉ የምትታዘዙ እንደ ሆናችሁ የእናንተን መፈተን አውቅ ዘንድ አሳቤ ነበር።
9For to this end also I have written, that I might know, by putting you to the test, if as to everything ye are obedient.
10እናንተ ግን ይቅር የምትሉትን እኔ ደግሞ ይቅር እለዋለሁ፤ እኔም ይቅር ካልሁ፥ ይቅር ያልሁትን ስለ እናንተ በክርስቶስ ፊት ይቅር ብዬአለሁ፥
10But to whom ye forgive anything, *I* also; for I also, what I have forgiven, if I have forgiven anything, [it is] for your sakes in [the] person of Christ;
11በሰይጣን እንዳንታለል፤ የእርሱን አሳብ አንስተውምና።
11that we might not have Satan get an advantage against us, for we are not ignorant of *his* thoughts.
12ስለ ክርስቶስም ወንጌል ወደ ጢሮአዳ በመጣሁ ጊዜ፥ ለጌታ ሥራ በር ምንም ቢከፈትልኝ፥ ቲቶን ወንድሜን ስላላገኘሁት መንፈሴ ዕረፍት አልነበረውም፥
12Now when I came to Troas for the [publication of the] glad tidings of the Christ, a door also being opened to me in [the] Lord,
13ነገር ግን ከእነርሱ ተሰናብቼ ወደ መቄዶንያ ወጣሁ።
13I had no rest in my spirit at not finding Titus my brother; but bidding them adieu, I came away to Macedonia.
14ነገር ግን በክርስቶስ ሁልጊዜ ድል በመንሣቱ ለሚያዞረን በእኛም በየስፍራው ሁሉ የእውቀቱን ሽታ ለሚገልጥ ለአምላክ ምስጋና ይሁን፤
14But thanks [be] to God, who always leads us in triumph in the Christ, and makes manifest the odour of his knowledge through us in every place.
15በሚድኑቱና በሚጠፉቱ ዘንድ ለእግዚአብሔር የክርስቶስ መዓዛ ነንና፤
15For we are a sweet odour of Christ to God, in the saved and in those that perish:
16ለእነዚህ ለሞት የሚሆን የሞት ሽታ ለእነዚያም ለሕይወት የሚሆን የሕይወት ሽታ ነን። ለዚህም ነገር የሚበቃ ማን ነው?
16to the one an odour from death unto death, but to the others an odour from life unto life; and who [is] sufficient for these things?
17የእግዚአብሔርን ቃል ቀላቅለው እንደሚሸቃቅጡት እንደ ብዙዎቹ አይደለንምና፤ በቅንነት ግን ከእግዚአብሔር እንደ ተላክን በእግዚአብሔር ፊት በክርስቶስ ሆነን እንናገራለን።
17For we do not, as the many, make a trade of the word of God; but as of sincerity, but as of God, before God, we speak in Christ.