Amharic: New Testament

Darby's Translation

Acts

20

1ሁከቱም ከቀረ በኋላ ጳውሎስ ደቀ መዛሙርቱን አስመጥቶ መከራቸው፥ ተሰናብቶአቸውም ወደ መቄዶንያ ይሄድ ዘንድ ወጣ።
1But after the tumult had ceased, Paul having called the disciples to [him] and embraced [them], went away to go to Macedonia.
2ያንም አገር እያለፈ በብዙ ቃል ከመከራቸው በኋላ ወደ ግሪክ አገር መጣ።
2And having passed through those parts, and having exhorted them with much discourse, he came to Greece.
3በዚያም ሦስት ወር ተቀምጦ ወደ ሶርያ በመርከብ ሊሄድ ባሰበ ጊዜ፥ አይሁድ ሴራ ስላደረጉበት በመቄዶንያ አልፎ ይመለስ ዘንድ ቆረጠ።
3And having spent three months [there], a treacherous plot against him having been set on foot by the Jews, as he was going to sail to Syria, [the] resolution was adopted of returning through Macedonia.
4የሸኙትም የቤርያው ሱሲጳጥሮስ ከተሰሎንቄ ሰዎችም አርስጥሮኮስና ሲኮንዱስ የደርቤኑም ጋይዮስና ጢሞቴዎስ የእስያ ሰዎችም ቲኪቆስ ጥሮፊሞስም ነበሩ፤
4And there accompanied him as far as Asia, Sopater [son] of Pyrrhus, a Berean; and of Thessalonians, Aristarchus and Secundus, and Gaius and Timotheus of Derbe, and of Asia, Tychicus and Trophimus.
5እነዚህም ወደ ፊታችን አልፈው በጢሮአዳ ቆዩን።
5These going before waited for us in Troas;
6እኛ ግን ከቂጣ በዓል ቀን በኋላ ከፊልጵስዩስ በመርከብ ተነሥተን በአምስት ቀን ወደ ጢሮአዳ ወደ እነርሱ ደረስንና በዚያ ሰባት ቀን ተቀመጥን።
6but we sailed away from Philippi after the days of unleavened bread, and we came to them to Troas in five days, where we spent seven days.
7ከሳምንቱም በመጀመሪያ ቀን እንጀራ ለመቁረስ ተሰብስበን ሳለን፥ ጳውሎስ በነገው ሊሄድ ስላሰበ ከእነርሱ ጋር ይነጋገር ነበር፥ እስከ መንፈቀ ሌሊትም ነገሩን አስረዘመ።
7And the first day of the week, we being assembled to break bread, Paul discoursed to them, about to depart on the morrow. And he prolonged the discourse till midnight.
8ተሰብስበንም በነበርንበት ሰገነት እጅግ መብራት ነበረ።
8And there were many lights in the upper room where we were assembled.
9አውጤኪስ የሚሉትም አንድ ጎበዝ በመስኮት ተቀምጦ ታላቅ እንቅልፍ አንቀላፍቶ ነበር፤ ጳውሎስም ነገርን ባስረዘመ ጊዜ እንቅልፍ ከብዶት ከሦስተኛው ደርብ ወደ ታች ወደቀ፥ ሞቶም አነሡት።
9And a certain youth, by name Eutychus, sitting at the window-opening, overpowered by deep sleep, while Paul discoursed very much at length, having been overpowered by the sleep, fell from the third story down to the bottom, and was taken up dead.
10ጳውሎስም ወርዶ በላዩ ወደቀ፥ አቅፎም። ነፍሱ አለችበትና አትንጫጩ አላቸው።
10But Paul descending fell upon him, and enfolding [him] [in his arms], said, Be not troubled, for his life is in him.
11ወጥቶም እንጀራ ቆርሶም በላ፤ ብዙ ጊዜም እስኪነጋ ድረስ ተነጋገረ እንዲህም ሄደ።
11And having gone up, and having broken the bread, and eaten, and having long spoken until daybreak, so he went away.
12ብላቴናውንም ደኅና ሆኖ ወሰዱት እጅግም ተጽናኑ።
12And they brought [away] the boy alive, and were no little comforted.
13እኛ ግን ጳውሎስን ከዚያ እንቀበለው ዘንድ ስላለን ወደ መርከብ ቀድመን ሄድንና ወደ አሶን ተነሣን፤ እርሱ በመሬት ይሄድ ዘንድ ስላሰበ እንደዚህ አዞ ነበርና።
13And we, having gone before on board ship, sailed off to Assos, going to take in Paul there; for so he had directed, he himself being about to go on foot.
14በአሶንም ባገኘን ጊዜ ተቀብለነው ወደ ሚጢሊኒ መጣን፤
14And when he met with us at Assos, having taken him on board, we came to Mitylene;
15በማግሥቱም ከዚያ በባሕር ተነሥተን በኪዩ ፊት ለፊት ደረስን፥ በነገውም ወደ ሳሞን ተሻገርን በትሮጊሊዮም አድረን በማግሥቱ ወደ ሚሊጢን መጣን።
15and having sailed thence, on the morrow arrived opposite Chios, and the next day put in at Samos; and having stayed at Trogyllium, the next day we came to Miletus:
16ጳውሎስ በእስያ እጅግ እንዳይቀመጥ ኤፌሶንን ይተው ዘንድ ቆርጦ ነበርና ቢቻለውም በዓለ ኀምሳን በኢየሩሳሌም ይውል ዘንድ ይቸኩል ነበርና።
16for Paul thought it desirable to sail by Ephesus, so that he might not be made to spend time in Asia; for he hastened, if it was possible for him, to be the day of Pentecost at Jerusalem.
17ከሚሊጢንም ወደ ኤፌሶን ልኮ የቤተክርስቲያንን ሽማግሌዎች አስጠራቸው፤
17But from Miletus having sent to Ephesus, he called over [to him] the elders of the assembly.
18ወደ እርሱም በመጡ ጊዜ እንዲህ አላቸው። ወደ እስያ ከገባሁበት ከመጀመሪያ ቀን ጀምሮ፥ በትሕትና ሁሉና በእንባ ከአይሁድም ሴራ በደረሰብኝ ፈተና ለጌታ እየተገዛሁ ዘመኑን ሁሉ ከእናንተ ጋር እንዴት እንደ ኖርሁ እናንተው ታውቃላችሁ፤
18And when they were come to him, he said to them, *Ye* know how I was with you all the time from the first day that I arrived in Asia,
20ወደ እግዚአብሔር ዘንድ ንስሐንና በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ማመንን ለአይሁድና ለግሪክ ሰዎች እየመሰከርሁ በጉባኤም በየቤታችሁም አወራሁላችሁና አስተማርኋችሁ እንጂ፥ ከሚጠቅማችሁ ነገር አንዳች ስንኳ አላስቀረሁባችሁም።
19serving the Lord with all lowliness, and tears, and temptations, which happened to me through the plots of the Jews;
22አሁንም፥ እነሆ፥ እኔ በመንፈስ ታስሬ ወደ ኢየሩሳሌም እሄዳለሁ፥ በዚያም የሚያገኘኝ ምን እንደ ሆነ አላውቅም፤
20how I held back nothing of what is profitable, so as not to announce [it] to you, and to teach you publicly and in every house,
23ነገር ግን መንፈስ ቅዱስ። እስራትና መከራ ይቆይሃል ብሎ በየከተማው ሁሉ ይመሰክርልኛል።
21testifying to both Jews and Greeks repentance towards God, and faith towards our Lord Jesus Christ.
24ነገር ግን ሩጫዬንና ከጌታ ከኢየሱስ የተቀበልሁትን አገልግሎት እርሱም የእግዚአብሔርን ጸጋ ወንጌልን መመስከር እፈጽም ዘንድ ነፍሴን በእኔ ዘንድ እንደማትከብር እንደ ከንቱ ነገር እቆጥራለሁ።
22And now, behold, bound in my spirit *I* go to Jerusalem, not knowing what things shall happen to me in it;
25አሁንም፥ እነሆ፥ እኔ የእግዚአብሔርን መንግሥት እየሰበክሁ በመካከላችሁ የዞርሁ ሁላችሁ ከእንግዲህ ወዲህ ፊቴን እንዳትዩ አውቃለሁ።
23only that the Holy Spirit testifies to me in every city, saying that bonds and tribulations await me.
26ስለዚህ እኔ ከሰው ሁሉ ደም ንጹሕ እንደ ሆንሁ ዛሬ በዚች ቀን እመሰክርላችኋለሁ።
24But I make no account of [my] life [as] dear to myself, so that I finish my course, and the ministry which I have received of the Lord Jesus, to testify the glad tidings of the grace of God.
27የእግዚአብሔርን ምክር ሁሉ ነግሬአችኋለሁና፥ ምንም አላስቀረሁባችሁም።
25And now, behold, I know that ye all, among whom I have gone about preaching the kingdom [of God], shall see my face no more.
28በገዛ ደሙ የዋጃትን የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ትጠብቁአት ዘንድ መንፈስ ቅዱስ እናንተን ጳጳሳት አድርጎ ለሾመባት ለመንጋው ሁሉና ለራሳችሁ ተጠንቀቁ።
26Wherefore I witness to you this day, that I am clean from the blood of all,
29ከሄድሁ በኋላ ለመንጋው የማይራሩ ጨካኞች ተኩላዎች እንዲገቡባችሁ፥ ደቀ መዛሙርትንም ወደ ኋላቸው ይስቡ ዘንድ ጠማማ ነገርን የሚናገሩ ሰዎች በመካከላችሁ እንዲነሡ እኔ አውቃለሁ።
27for I have not shrunk from announcing to you all the counsel of God.
31ስለዚህ ሦስት ዓመት ሌሊትና ቀን በእንባ እያንዳንዳችሁን ከመገሠጽ እንዳላቋረጥሁ እያሰባችሁ ትጉ።
28Take heed therefore to yourselves, and to all the flock, wherein the Holy Spirit has set you as overseers, to shepherd the assembly of God, which he has purchased with the blood of his own.
32አሁንም ለእግዚአብሔርና ያንጻችሁ ዘንድ በቅዱሳንም ሁሉ መካከል ርስትን ይሰጣችሁ ዘንድ ለሚችል ለጸጋው ቃል አደራ ሰጥቻችኋለሁ።
29[For] *I* know [this,] that there will come in amongst you after my departure grievous wolves, not sparing the flock;
33ከማንም ብር ወይም ወርቅ ወይም ልብስ አልተመኘሁም፤
30and from among your own selves shall rise up men speaking perverted things to draw away the disciples after them.
34እነዚህ እጆቼ በሚያስፈልገኝ ነገር ለእኔና ከእኔ ጋር ላሉት እንዳገለገሉ እናንተ ታውቃላችሁ።
31Wherefore watch, remembering that for three years, night and day, I ceased not admonishing each one [of you] with tears.
35እንዲሁ እየደከማችሁ ድውዮችን ልትረዱና እርሱ ራሱ። ከሚቀበል ይልቅ የሚሰጥ ብፁዕ ነው እንዳለ የጌታን የኢየሱስን ቃል ልታስቡ ይገባችሁ ዘንድ በሁሉ አሳየኋችሁ።
32And now I commit you to God, and to the word of his grace, which is able to build [you] up and give [to you] an inheritance among all the sanctified.
36ይህንም ብሎ ተንበርክኮ ከሁላቸው ጋር ጸለየ።
33I have coveted [the] silver or gold or clothing of no one.
37ሁሉም እጅግ አለቀሱ፥ ጳውሎስንም አንገቱን አቅፈው ይስሙት ነበር፤
34Yourselves know that these hands have ministered to my wants, and to those who were with me.
38ይልቁንም። ከእንግዲህ ወዲህ ፊቴን አታዩም ስላላቸው ነገር እጅግ አዘኑ። እስከ መርከብም ድረስ ሸኙት።
35I have shewed you all things, that thus labouring [we] ought to come in aid of the weak, and to remember the words of the Lord Jesus, that he himself said, It is more blessed to give than to receive.
36And having said these things, he knelt down and prayed with them all.
37And they all wept sore; and falling upon the neck of Paul they ardently kissed him,
38specially pained by the word which he had said, that they would no more see his face. And they went down with him to the ship.