1ጳውሎስም ሸንጎውን ትኵር ብሎ ተመልክቶ። ወንድሞች ሆይ፥ እኔ እስከዚች ቀን ድረስ በመልካም ሕሊና ሁሉ በእግዚአብሔር ፊት ኖሬአለሁ አለ።
1And Paul, fixing his eyes on the council, said, Brethren, I have walked in all good conscience with God unto this day.
2ሊቀ ካህናቱም ሐናንያ አፉን ይመቱት ዘንድ በአጠገቡ ቆመው የነበሩትን አዘዘ።
2But the high priest Ananias ordered those standing by him to smite his mouth.
3በዚያን ጊዜ ጳውሎስ። አንተ በኖራ የተለሰነ ግድግዳ፥ እግዚአብሔር አንተን ይመታ ዘንድ አለው፤ አንተ በሕግ ልትፈርድብኝ ተቀምጠህ ሳለህ ያለ ሕግ እመታ ዘንድ ታዛለህን? አለው።
3Then Paul said to him, God will smite thee, whited wall. And *thou*, dost thou sit judging me according to the law, and breaking the law commandest me to be smitten?
4በአጠገቡ የቆሙትም። የእግዚአብሔርን ሊቀ ካህናት ትሳደባለህን? አሉት።
4And those that stood by said, Dost thou rail against the high priest of God?
5ጳውሎስም። ወንድሞች ሆይ፥ ሊቀ ካህናት መሆኑን ባላውቅ ነው፤ በሕዝብህ አለቃ ላይ ክፉ ቃል አትናገር ተብሎ ተጽፎአልና አላቸው።
5And Paul said, I was not conscious, brethren, that he was high priest; for it is written, Thou shalt not speak evilly of the ruler of thy people.
6ጳውሎስ ግን እኵሌቶቹ ሰዱቃውያን እኵሌቶቹም ፈሪሳውያን መሆናቸውን አይቶ። ወንድሞች ሆይ፥ እኔ ፈሪሳዊ የፈሪሳዊም ልጅ ነኝ፤ ስለ ተስፋና ስለ ሙታን መነሣት ይፈርዱብኛል ብሎ በሸንጎው ጮኸ።
6But Paul, knowing that the one part [of them] were of the Sadducees and the other of the Pharisees, cried out in the council, Brethren, *I* am a Pharisee, son of Pharisees: *I* am judged concerning the hope and resurrection of [the] dead.
7ይህንም ባለ ጊዜ በፈሪሳውያንና በሰዱቃውያን መካከል ጥል ሆነ ሸንጎውም ተለያየ።
7And when he had spoken this, there was a tumult of the Pharisees and the Sadducees, and the multitude was divided.
8ሰዱቃውያን። ትንሣኤም መልአክም መንፈስም የለም የሚሉ ናቸውና፤ ፈሪሳውያን ግን ሁለቱን ያምናሉ።
8For Sadducees say there is no resurrection, nor angel, nor spirit; but Pharisees confess both of them.
9ታላቅ ጩኸትም ሆነ፥ ከፈሪሳውያንም ወገን የሆኑት ጻፎች ተነሥተው። በዚህ ሰው ላይ ምንም ክፉ ነገር አላገኘንበትም፤ መንፈስ ወይስ መልአክ ተናግሮት ይሆን? ብለው ተከራከሩ።
9And there was a great clamour, and the scribes of the Pharisees' part rising up contended, saying, We find nothing evil in this man; and if a spirit has spoken to him, or an angel ...
10ብዙ ጥልም በሆነ ጊዜ የሻለቃው ጳውሎስን እንዳይገነጣጥሉት ፈርቶ ጭፍሮቹ ወርደው ከመካከላቸው እንዲነጥቁት ወደ ሰፈሩም እንዲያገቡት አዘዘ።
10And a great tumult having arisen, the chiliarch, fearing lest Paul should have been torn in pieces by them, commanded the troop to come down and take him by force from the midst of them, and to bring [him] into the fortress.
11በሁለተኛውም ሌሊት ጌታ በአጠገቡ ቆሞ። ጳውሎስ ሆይ፥ በኢየሩሳሌም ስለ እኔ እንደ መሰከርህ እንዲሁ በሮሜም ትመሰክርልኝ ዘንድ ይገባሃልና አይዞህ አለው።
11But the following night the Lord stood by him, and said, Be of good courage; for as thou hast testified the things concerning me at Jerusalem, so thou must bear witness at Rome also.
12በጠባም ጊዜ አይሁድ ጳውሎስን እስኪገድሉት ድረስ እንዳይበሉና እንዳይጠጡ በመሐላ ተስማሙ።
12And when it was day, the Jews, having banded together, put themselves under a curse, saying that they would neither eat nor drink till they should kill Paul.
13ይህንም ሴራ ያደረጉት ሰዎች ከአርባ ይበዙ ነበር፤
13And they were more than forty who had joined together in this oath;
14እነርሱም ወደ ካህናት አለቆችና ወደ ሽማግሌዎቹ መጥተው። ጳውሎስን እስክንገድል ድረስ ምንም እንዳንቀምስ ተረጋግመን ተማምለናል።
14and they went to the chief priests and elders, and said, We have cursed ourselves with a curse to taste nothing until we kill Paul.
15እንግዲህ አሁን እናንተ ከሸንጎው ጋር ሆናችሁ ስለ እርሱ አጥብቃችሁ እንደምትመረምሩ መስላችሁ ወደ እናንተ እንዲያወርደው ለሻለቃው አመልክቱት፤ እኛም ሳይቀርብ እንድንገድለው የተዘጋጀን ነን አሉአቸው።
15Now therefore do ye with the council make a representation to the chiliarch so that he may bring him down to you, as about to determine more precisely what concerns him, and we, before he draws near, are ready to kill him.
16የጳውሎስ የእኅቱ ልጅ ግን ደባቸውን በሰማ ጊዜ፥ መጥቶ ወደ ሰፈሩ ገባና ለጳውሎስ ነገረው።
16But Paul's sister's son, having heard of the lying in wait, came and entered into the fortress and reported [it] to Paul.
17ጳውሎስም ከመቶ አለቆች አንዱን ጠርቶ። ይህን ብላቴና ወደ ሻለቃው ውሰድ፥ የሚያወራለት ነገር አለውና አለው።
17And Paul, having called one of the centurions, said, Take this youth to the chiliarch, for he has something to report to him.
18እርሱም ይዞት ወደ ሻለቃው ወሰደውና። ይህ ብላቴና የሚነግርህ ነገር ስላለው እስረኛው ጳውሎስ ጠርቶ ወደ አንተ እንድወስደው ለመነኝ አለው።
18He therefore, having taken him with [him], led him to the chiliarch, and says, The prisoner Paul called me to [him] and asked me to lead this youth to thee, who has something to say to thee.
19የሻለቃውም እጁን ይዞ ፈቀቅ አለና ለብቻው ሆኖ። የምታወራልኝ ነገር ምንድር ነው? ብሎ ጠየቀው።
19And the chiliarch having taken him by the hand, and having gone apart in private, inquired, What is it that thou hast to report to me?
20እርሱም። አይሁድ ስለ ጳውሎስ ከፊት ይልቅ አጥብቀህ እንደምትመረምር መስለህ፥ ነገ ወደ ሸንጎ ታወርደው ዘንድ ሊለምኑህ ተስማምተዋል።
20And he said, The Jews have agreed together to make a request to thee, that thou mayest bring Paul down to-morrow into the council, as about to inquire something more precise concerning him.
21እንግዲህ አንተ በጅ አትበላቸው፤ እስኪገድሉት ድረስ እንዳይበሉና እንዳይጠጡ ተማምለው ከእነርሱ ከአርባ የሚበዙ ሰዎች ያደቡበታልና፤ አሁንም የተዘጋጁ ናቸው የአንተንም ምላሽ ይጠብቃሉ አለው።
21Do not thou then be persuaded by them, for there lie in wait for him of them more than forty men, who have put themselves under a curse neither to eat nor drink till they kill him; and now they are ready waiting the promise from thee.
22የሻለቃውም። ይህን ነገር ለእኔ ማመልከትህን ለማንም እንዳትገልጥ ብሎ ካዘዘ በኋላ ብላቴናውን አሰናበተው።
22The chiliarch then dismissed the youth, commanding [him], Utter to no one that thou hast represented these things to me.
23ከመቶ አለቆቹም ሁለት ጠርቶ። ወደ ቂሣርያ ይሄዱ ዘንድ ሁለት መቶ ወታደሮችንና ሰባ ፈረሰኞችን ሁለት መቶም ባለ ጦር መሣሪያዎችን ከሌሊቱ በሦስተኛው ሰዓት አዘጋጁ አላቸው።
23And having called to [him] certain two of the centurions, he said, Prepare two hundred soldiers that they may go as far as Caesarea, and seventy horsemen, and two hundred light-armed footmen, for the third hour of the night.
24ጳውሎስንም ወደ አገረ ገዡ ወደ ፊልክስ በደኅና እንዲያደርሱት የሚያስቀምጡበትን ከብት ያዘጋጁ ዘንድ አዘዛቸው።
24And [he ordered them] to provide beasts, that they might set Paul on them and carry [him] safe through to Felix the governor,
25ደብዳቤም ጻፈ እንዲህ የሚል።
25having written a letter, couched in this form:
26ከቀላውዴዎስ ሉስዮስ ወደ ክቡር አገረ ገዡ ወደ ፊልክስ፤ ሰላም ለአንተ ይሁን።
26Claudius Lysias to the most excellent governor Felix, greeting.
27ይህን ሰው አይሁድ ይዘው ሊገድሉት ባሰቡ ጊዜ ከጭፍሮቹ ጋር ደርሼ አዳንሁት፥ ሮማዊ እንደ ሆነ አውቄ ነበርና።
27This man, having been taken by the Jews, and being about to be killed by them, I came up with the military and took out [of their hands], having learned that he was a Roman.
28የሚከሰስበትንም ምክንያት አውቅ ዘንድ አስቤ ወደ ሸንጎአቸው አወረድሁት፤
28And desiring to know the charge on which they accused him, I brought him down to their council;
29በሕጋቸውም ስለ መከራከር እንደ ከሰሱት አገኘሁ እንጂ ለሞት ወይም ለእስራት የሚያደርስ ክስ አይደለም።
29whom I found to be accused of questions of their law, but to have no charge laid against him [making him] worthy of death or of bonds.
30በዚህም ሰው አይሁድ ሴራ እንዲያደርጉበት ባመለከቱኝ ጊዜ ያን ጊዜውን ወደ አንተ ሰደድሁት፥ ከሳሾቹንም ደግሞ በፊትህ ይከሱት ዘንድ አዘዝኋቸው። ደኅና ሁን።
30But having received information of a plot about to be put in execution against the man [by the Jews], I have immediately sent him to thee, commanding also his accusers to say before thee the things that are against him. [Farewell.]
31ወታደሮቹም እንደ ታዘዙት ጳውሎስን ይዘው በሌሊት ወደ አንቲጳጥሪስ አደረሱት፤
31The soldiers therefore, according to what was ordered them, took Paul and brought him by night to Antipatris,
32በነገውም ከእርሱ ጋር ይሄዱ ዘንድ ፈረሰኞችን ትተው ወደ ሰፈር ተመለሱ።
32and on the morrow, having left the horsemen to go with him, returned to the fortress.
33እነዚያም ወደ ቂሣርያ ገብተው ደብዳቤውን ለአገረ ገዡ በሰጡ ጊዜ ጳውሎስን ደግሞ በፊቱ አቆሙት።
33And these, having entered into Caesarea, and given up the letter to the governor, presented Paul also to him.
34ካነበበውም በኋላ የወዴት አውራጃ እንደ ሆነ ጠየቀው፤ የኪልቅያ ሰው መሆኑንም ባወቀ ጊዜ።
34And having read [it], and asked of what eparchy he was, and learned that [he was] of Cilicia,
35ከሳሾችህ ደግሞ ሲመጡ እሰማሃለሁ አለው፤ በሄሮድስም ግቢ ውስጥ ይጠብቁት ዘንድ አዘዘ።
35he said, I will hear thee fully when thine accusers also are arrived. And he commanded him to be kept in Herod's praetorium.