Amharic: New Testament

Darby's Translation

Colossians

4

1ጌቶች ሆይ፥ እናንተ ደግሞ በሰማይ ጌታ እንዳላችሁ ታውቃላችሁና ለባሪያዎቻችሁ በጽድቅና በቅንነት አድርጉላቸው።
1Masters, give to bondmen what is just and fair, knowing that *ye* also have a Master in [the] heavens.
2ከማመስገን ጋር በጸሎት እየነቃችሁ ለእርሱ ትጉ።
2Persevere in prayer, watching in it with thanksgiving;
3በዚያን ጊዜም ስለ እርሱ ደግሞ የታሰርሁበትን የክርስቶስን ምሥጢር እንድንነግር እግዚአብሔር የቃሉን ደጅ ይከፍትልን ዘንድ ስለ እኛ ደግሞ ጸልዩ።
3praying at the same time for us also, that God may open to us a door of the word to speak the mystery of Christ, on account of which also I am bound,
4ልናገር እንደሚገባኝ ያህል እገልጠው ዘንድ ጸልዩልኝ።
4to the end that I may make it manifest as I ought to speak.
5ዘመኑን እየዋጃችሁ፥ በውጭ ባሉቱ ዘንድ በጥበብ ተመላለሱ።
5Walk in wisdom towards those without, redeeming opportunities.
6ለእያንዳንዱ እንዴት እንድትመልሱ እንደሚገባችሁ ታውቁ ዘንድ ንግግራችሁ ሁልጊዜ፥ በጨው እንደ ተቀመመ፥ በጸጋ ይሁን።
6[Let] your word [be] always with grace, seasoned with salt, [so as] to know how ye ought to answer each one.
7የተወደደ ወንድምና የታመነ አገልጋይ በጌታም አብሮኝ ባሪያ የሆነ ቲኪቆስ ኑሮዬን ሁሉ ያስታውቃችኋል።
7Tychicus, the beloved brother and faithful minister and fellow-bondman in [the] Lord, will make known to you all that concerns me;
8ወሬያችንን እንድታውቁና ልባችሁን እንዲያጽናና፥ ከእናንተ ከሆነውና ከታመነው ከተወደደውም ወንድም ከአናሲሞስ ጋር ወደ እናንተ የምልከው ስለዚህ ምክንያት ነው። የዚህን ስፍራ ወሬ ሁሉ ያስታውቁአችኋል።
8whom I have sent to you for this very purpose, that he might know your state, and that he might encourage your hearts:
10ከተገረዙት ወገን ያሉት፥ አብሮ ከእኔ ጋር የታሰረ አርስጥሮኮስ የበርናባስም የወንድሙ ልጅ ማርቆስ ኢዮስጦስም የተባለ ኢያሱ ሰላምታ ያቀርቡላችኋል። ስለ ማርቆስ። ወደ እናንተ ቢመጣ፥ ተቀበሉት የሚል ትእዛዝ ተቀበላችሁ። በእግዚአብሔር መንግሥት ከእኔ ጋር አብረው የሚሠሩት እነዚህ ብቻ ናቸው፥ እኔንም አጽናንተውኛል።
9with Onesimus, the faithful and beloved brother, who is [one] of you. They shall make known to you everything here.
12ከእናንተ የሆነ የክርስቶስ ባሪያ ኤጳፍራ ሰላምታ ያቀርብላችኋል። በእግዚአብሔር ፈቃድ ሁሉ ተረድታችሁና ፍጹማን ሆናችሁ እንድትቆሙ፥ ሁልጊዜ ስለ እናንተ በጸሎቱ ይጋደላል።
10Aristarchus my fellow-captive salutes you, and Mark, Barnabas's cousin, concerning whom ye have received orders, (if he come to you, receive him,)
13ስለ እናንተ በሎዶቅያም በኢያራ ከተማም ስላሉቱ እጅግ እንዲቀና እመሰክርለታለሁና።
11and Jesus called Justus, who are of the circumcision. These [are the] only fellow-workers for the kingdom of God who have been a consolation to me.
14የተወደደው ባለ መድኃኒቱ ሉቃስ ዴማስም ሰላምታ ያቀርቡላችኋል።
12Epaphras, who is [one] of you, [the] bondman of Christ Jesus, salutes you, always combating earnestly for you in prayers, to the end that ye may stand perfect and complete in all [the] will of God.
15በሎዶቅያ ላሉቱ ወንድሞችና ለንምፉን በቤቱም ላለች ቤተ ክርስቲያን ሰላምታ አቅርቡልን።
13For I bear him witness that he labours much for you, and them in Laodicea, and them in Hierapolis.
16ይህችም መልእክት በእናንተ ዘንድ ከተነበበች በኋላ፥ በሎዶቅያ ሰዎች ማኅበር ደግሞ እንድትነበብ አድርጉ። ከሎዶቅያም የምትገኘውን መልእክት እናንተ ደግሞ አንብቡ።
14Luke, the beloved physician, salutes you, and Demas.
17ለአክሪጳም። በጌታ የተቀበልኸውን አገልግሎት እንድትፈጽሙው ተጠንቀቅ በሉልኝ።
15Salute the brethren in Laodicea, and Nymphas, and the assembly which [is] in his house.
18በገዛ እጄ የተጻፈ የእኔ የጳውሎስ ሰላምታ ይህ ነው። እስራቴን አስቡ። ጸጋ ከእናንተ ጋር ይሁን።
16And when the letter has been read among you, cause that it be read also in the assembly of Laodiceans, and that *ye* also read that from Laodicea.
17And say to Archippus, Take heed to the ministry which thou hast received in [the] Lord, to the end that thou fulfil it.
18The salutation by the hand of me Paul. Remember my bonds. Grace [be] with you.