Amharic: New Testament

Darby's Translation

Ephesians

5

1እንግዲህ እንደ ተወደዱ ልጆች እግዚአብሔርን የምትከተሉ ሁኑ፥
1Be ye therefore imitators of God, as beloved children,
2ክርስቶስም ደግሞ እንደ ወደዳችሁ ለእግዚአብሔርም የመዓዛ ሽታ የሚሆንን መባንና መሥዋዕትን አድርጎ ስለ እናንተ ራሱን አሳልፎ እንደ ሰጠ በፍቅር ተመላለሱ።
2and walk in love, even as the Christ loved us, and delivered himself up for us, an offering and sacrifice to God for a sweet-smelling savour.
3ለቅዱሳን እንደሚገባ ግን ዝሙትና ርኵሰት ሁሉ ወይም መመኘት በእናንተ ዘንድ ከቶ አይሰማ፤
3But fornication and all uncleanness or unbridled lust, let it not be even named among you, as it becomes saints;
4የሚያሳፍር ነገርም የስንፍና ንግግርም ወይም ዋዛ የማይገቡ ናቸውና አይሁኑ፥ ይልቁን ምስጋና እንጂ።
4and filthiness and foolish talking, or jesting, which are not convenient; but rather thanksgiving.
5ይህን እወቁ፤ አመንዝራም ቢሆን ወይም ርኵስ ወይም የሚመኝ እርሱም ጣዖትን የሚያመልክ በክርስቶስና በእግዚአብሔር መንግሥት ርስት የለውም።
5For this ye are [well] informed of, knowing that no fornicator, or unclean person, or person of unbridled lust, who is an idolater, has inheritance in the kingdom of the Christ and God.
6ከዚህ የተነሣ በማይታዘዙት ልጆች ላይ የእግዚአብሔር ቁጣ ይመጣልና ማንም በከንቱ ንግግር አያታልላችሁ።
6Let no one deceive you with vain words, for on account of these things the wrath of God comes upon the sons of disobedience.
7እንግዲህ ከእነርሱ ጋር ተካፋዮች አትሁኑ፤
7Be not ye therefore fellow-partakers with them;
8ቀድሞ ጨለማ ነበራችሁና፥ አሁን ግን በጌታ ብርሃን ናችሁ፤
8for ye were once darkness, but now light in [the] Lord; walk as children of light,
9የብርሃኑ ፍሬ በበጎነትና በጽድቅ በእውነትም ሁሉ ነውና ለጌታ ደስ የሚያሰኘውን እየመረመራችሁ፥ እንደ ብርሃን ልጆች ተመላለሱ፤
9(for the fruit of the light [is] in all goodness and righteousness and truth,)
11ፍሬም ከሌለው ከጨለማ ሥራ ጋር አትተባበሩ፥ ይልቁን ግለጡት እንጂ፥
10proving what is agreeable to the Lord;
12እነርሱ በስውር ስለሚያደርጉት መናገር እንኳ ነውር ነውና፤
11and do not have fellowship with the unfruitful works of darkness, but rather also reprove [them],
13ሁሉ ግን በብርሃን ሲገለጥ ይታያል፤ የሚታየው ሁሉ ብርሃን ነውና።
12for the things that are done by them in secret it is shameful even to say.
14ስለዚህ። አንተ የምትተኛ ንቃ ከሙታንም ተነሣ ክርስቶስም ያበራልሃል ይላል።
13But all things having their true character exposed by the light are made manifest; for that which makes everything manifest is light.
15እንግዲህ እንደ ጥበበኞች እንጂ ጥበብ እንደሌላቸው ሳይሆን እንዴት እንድትመላለሱ በጥንቃቄ ተጠበቁ፤
14Wherefore he says, Wake up, [thou] that sleepest, and arise up from among the dead, and the Christ shall shine upon thee.
16ቀኖቹ ክፉዎች ናቸውና ዘመኑን ዋጁ።
15See therefore how ye walk carefully, not as unwise but as wise,
17ስለዚህ የጌታ ፈቃድ ምን እንደ ሆነ አስተውሉ እንጂ ሞኞች አትሁኑ።
16redeeming the time, because the days are evil.
18መንፈስ ይሙላባችሁ እንጂ በወይን ጠጅ አትስከሩ ይህ ማባከን ነውና፤
17For this reason be not foolish, but understanding what [is] the will of the Lord.
19በመዝሙርና በዝማሬ በመንፈሳዊም ቅኔ እርስ በርሳችሁ ተነጋገሩ፤ ለጌታ በልባችሁ ተቀኙና ዘምሩ፤
18And be not drunk with wine, in which is debauchery; but be filled with the Spirit,
20ሁልጊዜ ስለ ሁሉ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አምላካችንንና አባታችንን ስለ ሁሉ አመስግኑ።
19speaking to yourselves in psalms and hymns and spiritual songs, singing and chanting with your heart to the Lord;
21ለእያንዳንዳችሁ በክርስቶስ ፍርሃት የተገዛችሁ ሁኑ።
20giving thanks at all times for all things to him [who is] God and [the] Father in the name of our Lord Jesus Christ,
22ሚስቶች ሆይ፥ ለጌታ እንደምትገዙ ለባሎቻችሁ ተገዙ፤
21submitting yourselves to one another in [the] fear of Christ.
23ክርስቶስ ደግሞ የቤተ ክርስቲያን ራስ እንደ ሆነ እርሱም አካሉን የሚያድን እንደ ሆነ ባል የሚስት ራስ ነውና።
22Wives, [submit yourselves] to your own husbands, as to the Lord,
24ዳሩ ግን ቤተ ክርስቲያን ለክርስቶስ እንደምትገዛ እንዲሁ ሚስቶች ደግሞ በሁሉ ለባሎቻቸው ይገዙ።
23for a husband is head of the wife, as also the Christ [is] head of the assembly. *He* [is] Saviour of the body.
25ባሎች ሆይ፥ ክርስቶስ ደግሞ ቤተ ክርስቲያንን እንደ ወደዳት ሚስቶቻችሁን ውደዱ፤ በውኃ መታጠብና ከቃሉ ጋር አንጽቶ እንዲቀድሳት ስለ እርስዋ ራሱን አሳልፎ ሰጠ፤
24But even as the assembly is subjected to the Christ, so also wives to their own husbands in everything.
27እድፈት ወይም የፊት መጨማደድ ወይም እንዲህ ያለ ነገር ሳይሆንባት ቅድስትና ያለ ነውር ትሆን ዘንድ ክብርት የሆነችን ቤተ ክርስቲያን ለራሱ እንዲያቀርብ ፈለገ።
25Husbands, love your own wives, even as the Christ also loved the assembly, and has delivered himself up for it,
28እንዲሁም ባሎች ደግሞ እንደ ገዛ ሥጋቸው አድርገው የገዛ ሚስቶቻቸውን ሊወዱአቸው ይገባቸዋል። የገዛ ሚስቱን የሚወድ ራሱን ይወዳል፤
26in order that he might sanctify it, purifying [it] by the washing of water by [the] word,
29ማንም የገዛ ሥጋውን የሚጠላ ከቶ የለምና፥ ነገር ግን የአካሉ ብልቶች ስለሆንን፥ ክርስቶስ ደግሞ ለቤተ ክርስቲያን እንዳደረገላት፥ ይመግበዋል ይከባከበውማል።
27that *he* might present the assembly to himself glorious, having no spot, or wrinkle, or any of such things; but that it might be holy and blameless.
31ስለዚህ ሰው አባቱንና እናቱን ይተዋል ከሚስቱም ጋር ይተባበራል ሁለቱም አንድ ሥጋ ይሆናሉ።
28So ought men also to love their own wives as their own bodies: he that loves his own wife loves himself.
32ይህ ምሥጢር ታላቅ ነው፥ እኔ ግን ይህን ስለ ክርስቶስና ስለ ቤተ ክርስቲያን እላለሁ።
29For no one has ever hated his own flesh, but nourishes and cherishes it, even as also the Christ the assembly:
33ሆኖም ከእናንተ ደግሞ እያንዳንዱ የገዛ ሚስቱን እንዲህ እንደ ራሱ አድርጎ ይውደዳት፥ ሚስቱም ባልዋን ትፍራ።
30for we are members of his body; [we are of his flesh, and of his bones.]
31Because of this a man shall leave his father and mother, and shall be united to his wife, and the two shall be one flesh.
32This mystery is great, but *I* speak as to Christ, and as to the assembly.
33But *ye* also, every one of you, let each so love his own wife as himself; but as to the wife [I speak] that she may fear the husband.