Amharic: New Testament

Darby's Translation

Hebrews

3

1ስለዚህ፥ ከሰማያዊው ጥሪ ተካፋዮች የሆናችሁ ቅዱሳን ወንድሞች ሆይ፥ የሃይማኖታችንን ሐዋርያና ሊቀ ካህናት ኢየሱስ ክርስቶስን ተመልከቱ፤
1Wherefore, holy brethren, partakers of [the] heavenly calling, consider the Apostle and High Priest of our confession, Jesus,
2ሙሴ ደግሞ በቤቱ ሁሉ የታመነ እንደሆነ፥ እርሱ ለሾመው የታመነ ነበረ።
2who is faithful to him that has constituted him, as Moses also in all his house.
3ቤትን የሚያዘጋጀው ከቤቱ ይልቅ የሚበልጥ ክብር እንዳለው መጠን፥ እንዲሁ እርሱ ከሙሴ ይልቅ የሚበልጥ ክብር የተገባው ሆኖ ተቆጥሮአልና።
3For *he* has been counted worthy of greater glory than Moses, by how much he that has built it has more honour than the house.
4እያንዳንዱ ቤት በአንድ ሰው ተዘጋጅቶአልና፥ ሁሉን ያዘጋጀ ግን እግዚአብሔር ነው።
4For every house is built by some one; but he who has built all things [is] God.
5ሙሴስ በኋላ ስለሚነገረው ነገር ምስክር ሊሆን በቤቱ ሁሉ እንደ ሎሌ የታመነ ነበረ፥ ክርስቶስ ግን እንደ ልጅ በቤቱ ላይ የታመነ ነው፤
5And Moses indeed [was] faithful in all his house, as a ministering servant, for a testimony of the things to be spoken after;
6እኛም የምንደፍርበትን የምንመካበትንም ተስፋ እስከ መጨረሻው አጽንተን ብንጠብቅ ቤቱ ነን።
6but Christ, as Son over his house, whose house are *we*, if indeed we hold fast the boldness and the boast of hope firm to the end.
7ስለዚህ መንፈስ ቅዱስ እንደሚል።
7Wherefore, even as says the Holy Spirit, To-day if ye will hear his voice,
8ዛሬ ድምፁን ብትሰሙት፥ አባቶቻችሁ እኔን የፈተኑበት የመረመሩበትም አርባ ዓመትም ሥራዬን ያዩበት በምድረ በዳ በፈተና ቀን በማስመረር እንደ ሆነ፥ ልባችሁን እልከኛ አታድርጉ።
8harden not your hearts, as in the provocation, in the day of temptation in the wilderness;
10ስለዚህ ያን ትውልድ ተቆጥቼ። ዘወትር በልባቸው ይስታሉ መንገዴን ግን አላወቁም አልሁ፤
9where your fathers tempted [me], by proving [me], and saw my works forty years.
11እንዲሁ። ወደ ዕረፍቴ አይገቡም ብዬ በቍጣዬ ማልሁ።
10Wherefore I was wroth with this generation, and said, They always err in heart; and *they* have not known my ways;
12ወንድሞች ሆይ፥ ምናልባት ሕያው እግዚአብሔርን የሚያስክዳችሁ ክፉና የማያምን ልብ ከእናንተ በአንዳችሁ እንዳይኖር ተጠንቀቁ፤
11so I swore in my wrath, If they shall enter into my rest.
13ነገር ግን ከእናንተ ማንም በኃጢአት መታለል እልከኛ እንዳይሆን፥ ዛሬ ተብሎ ሲጠራ ሳለ፥ በእያንዳንዱ ቀን እርስ በርሳችሁ ተመካከሩ፤
12See, brethren, lest there be in any one of you a wicked heart of unbelief, in turning away from [the] living God.
14የመጀመሪያ እምነታችንን እስከ መጨረሻው አጽንተን ብንጠብቅ፥ የክርስቶስ ተካፋዮች ሆነናልና፤
13But encourage yourselves each day, as long as it is called To-day, that none of you be hardened by the deceitfulness of sin.
15እየተባለ። ዛሬ ድምጹን ብትሰሙት፥ በማስመረር እንደሆነ ልባችሁን እልከኛ አታድርጉ።
14For we are become companions of the Christ if indeed we hold the beginning of the assurance firm to the end;
16ሰምተው ያስመረሩት እነማን ነበሩ? በሙሴ ተመርተው ከግብጽ የወጡ ሁሉ አይደሉምን?
15in that it is said, To-day if ye will hear his voice, do not harden your hearts, as in the provocation;
17አርባ አመትም የተቆጣባቸው እነማን ነበሩ? ሬሳቸው በምድረ በዳ የወደቀ፥ ኃጢአትን ያደረጉት እነርሱ አይደሉምን?
16(for who was it, who, having heard, provoked? but [was it] not all who came out of Egypt by Moses?
18ካልታዘዙትም በቀር ወደ እረፍቱ እንዳይገቡ የማለባቸው እነማን ነበሩ?
17And with whom was he wroth forty years? [Was it] not with those who had sinned, whose carcases fell in the wilderness?
19ባለማመናቸውም ጠንቅ ሊገቡ እንዳልተቻላቸው እናያለን።
18And to whom sware he that they should not enter into his rest, but to those who had not hearkened to the word?
19And we see that they could not enter in on account of unbelief;)