1ከዚህም በኋላ ኢየሱስ አይሁድ ሊገድሉት ይፈልጉ ስለ ነበር በይሁዳ ሊመላለስ አይወድም ነበርና በገሊላ ይመላለስ ነበር።
1And after these things Jesus walked in Galilee, for he would not walk in Judaea, because the Jews sought to kill him.
2የአይሁድም የዳስ በዓል ቀርቦ ነበር።
2Now the tabernacles, the feast of the Jews, was near.
3እንግዲህ ወንድሞቹ። ደቀ መዛሙርትህ ደግሞ የምታደርገውን ሥራ እንዲያዩ ከዚህ ተነሣና ወደ ይሁዳ ሂድ፤
3His brethren therefore said to him, Remove hence and go into Judaea, that thy disciples also may see thy works which thou doest;
4ራሱ ሊገለጥ እየፈለገ በስውር የሚሠራ የለምና። እነዚህን ብታደርግ ራስህን ለዓለም ግለጥ አሉት።
4for no one does anything in secret and himself seeks to be [known] in public. If thou doest these things, manifest thyself to the world:
5ወንድሞቹ ስንኳ አላመኑበትም ነበርና።
5for neither did his brethren believe on him.
6ኢየሱስም እንዲህ አላቸው። ጊዜዬ ገና አልደረሰም፥ ጊዜያችሁ ግን ዘወትር የተመቸ ነው።
6Jesus therefore says to them, My time is not yet come, but your time is always ready.
7ዓለም እናንተን ሊጠላ አይቻለውም፤ እኔ ግን ሥራው ክፉ መሆኑን እመሰክርበታለሁና እኔን ይጠላኛል።
7The world cannot hate you, but me it hates, because I bear witness concerning it that its works are evil.
8እናንተ ወደዚህ በዓል ውጡ፤ እኔስ ጊዜዬ ገና ስላልተፈጸመ ወደዚህ በዓል ገና አልወጣም።
8Ye, go ye up to this feast. I go not up to this feast, for *my* time is not yet fulfilled.
9ይህንም አላቸውና በገሊላ ቀረ።
9Having said these things to them he abode in Galilee.
10ወንድሞቹ ግን ወደ በዓሉ ከወጡ በኋላ በዚያን ጊዜ እርሱ ደግሞ በግልጥ ሳይሆን ተሰውሮ ወጣ።
10But when his brethren had gone up, then he himself also went up to the feast, not openly, but as in secret.
11አይሁድም። እርሱ ወዴት ነው? እያሉ በበዓሉ ይፈልጉት ነበር።
11The Jews therefore sought him at the feast, and said, Where is he?
12በሕዝብም መካከል ስለ እርሱ ብዙ ማንጐራጐር ነበረ፤ አንዳንዱም። ደግ ሰው ነው፤ ሌሎች ግን። አይደለም፥ ሕዝቡን ግን ያስታል ይሉ ነበር።
12And there was much murmuring concerning him among the crowds. Some said, He is [a] good [man]; others said, No; but he deceives the crowd.
13ዳሩ ግን አይሁድን ስለ ፈሩ ማንም ስለ እርሱ በግልጥ አይናገርም ነበር።
13However, no one spoke openly concerning him on account of [their] fear of the Jews.
14አሁንም በበዓሉ እኩሌታ ኢየሱስ ወደ መቅደስ ወጥቶ ያስተምር ነበር።
14But when it was now the middle of the feast, Jesus went up into the temple and taught.
15አይሁድም። ይህ ሰው ሳይማር መጻሕፍትን እንዴት ያውቃል? ብለው ይደነቁ ነበር።
15The Jews therefore wondered, saying, How knows this [man] letters, having never learned?
16ስለዚህ ኢየሱስ መለሰ እንዲህም አላቸው። ትምህርቴስ ከላከኝ ነው እንጂ ከእኔ አይደለም፤
16Jesus therefore answered them and said, My doctrine is not mine, but [that] of him that has sent me.
17ፈቃዱን ሊያደርግ የሚወድ ቢኖር፥ እርሱ ይህ ትምህርት ከእግዚአብሔር ቢሆን ወይም እኔ ከራሴ የምናገር ብሆን ያውቃል።
17If any one desire to practise his will, he shall know concerning the doctrine, whether it is of God, or [that] I speak from myself.
18ከራሱ የሚናገር የራሱን ክብር ይፈልጋል፤ የላከውን ክብር የሚፈልግ ግን እርሱ እውነተኛ ነው በእርሱም ዓመፃ የለበትም።
18He that speaks from himself seeks his own glory; but he that seeks the glory of him that has sent him, he is true, and unrighteousness is not in him.
19ሙሴ ሕግን አልሰጣችሁምን? ከእናንተ ግን ሕግን የሚያደርግ አንድ ስንኳ የለም። ልትገድሉኝ ስለ ምን ትፈልጋላችሁ?
19Has not Moses given you the law, and no one of you practises the law? Why do ye seek to kill me?
20ሕዝቡ መለሱና። ጋኔን አለብህ፤ ማን ሊገድልህ ይፈልጋል? አሉት።
20The crowd answered [and said], Thou hast a demon: who seeks to kill thee?
21ኢየሱስ መለሰ አላቸውም። አንድ ሥራ አደረግሁ ሁላችሁም ታደንቃላችሁ።
21Jesus answered and said to them, I have done one work, and ye all wonder.
22ስለዚህ ሙሴ መገረዝን ሰጣችሁ፤ ከአባቶችም ነው እንጂ ከሙሴ አይደለም፤ በሰንበትም ሰውን ትገርዛላችሁ።
22Therefore Moses gave you circumcision (not that it is of Moses, but of the fathers), and ye circumcise a man on sabbath.
23የሙሴ ሕግ እንዳይሻር ሰው በሰንበት መገረዝን የሚቀበል ከሆነስ ሰውን ሁለንተናውን በሰንበት ጤናማ ስላደረግሁ ትቈጡኛላችሁን?
23If a man receives circumcision on sabbath, that the law of Moses may not be violated, are ye angry with me because I have made a man entirely sound on sabbath?
24ቅን ፍርድ ፍረዱ እንጂ በመልክ አትፍረዱ።
24Judge not according to sight, but judge righteous judgment.
25እንግዲህ ከኢየሩሳሌም ሰዎች አንዳንዶቹ እንዲህ አሉ። ሊገድሉት የሚፈልጉት ይህ አይደለምን?
25Some therefore of those of Jerusalem said, Is not this he whom they seek to kill?
26እነሆም፥ በግልጥ ይናገራል አንዳችም አይሉትም። አለቆቹ ይህ ሰው በእውነት ክርስቶስ እንደ ሆነ በእውነት አወቁን?
26and behold, he speaks openly, and they say nothing to him. Have the rulers then indeed recognised that this is the Christ?
27ነገር ግን ይህን ከወዴት እንደ ሆነ አውቀናል፤ ክርስቶስ ሲመጣ ግን ከወዴት እንደ ሆነ ማንም አያውቅም።
27But [as to] this [man] we know whence he is. Now [as to] the Christ, when he comes, no one knows whence he is.
28እንግዲህ ኢየሱስ በመቅደስ ሲያስተምር። እኔንም ታውቁኛላችሁ ከወዴትም እንደ ሆንሁ ታውቃላችሁ፤ እኔም በራሴ አልመጣሁም ነገር ግን እናንተ የማታውቁት የላከኝ እውነተኛ ነው፤
28Jesus therefore cried out in the temple, teaching and saying, Ye both know me and ye know whence I am; and I am not come of myself, but he that sent me is true, whom ye do not know.
29እኔ ግን ከእርሱ ዘንድ ነኝ እርሱም ልኮኛልና አውቀዋለሁ ብሎ ጮኸ።
29I know him, because I am from him, and *he* has sent me.
30ስለዚህ ሊይዙት ይፈልጉ ነበር፤ ነገር ግን ጊዜው ገና ስላልደረሰ ማንም እጁን አልጫነበትም።
30They sought therefore to take him; and no one laid his hand upon him, because his hour had not yet come.
31ከሕዝቡ ግን ብዙዎች አመኑበትና። ክርስቶስ በመጣ ጊዜ ይህ ካደረጋቸው ምልክቶች ይልቅ ያደርጋልን? አሉ።
31But many of the crowd believed on him, and said, Will the Christ, when he comes, do more signs than those which this [man] has done?
32ፈሪሳውያንም ሕዝቡ ሰለ እርሱ እንደዚህ ሲያንጐራጕሩ ሰሙ፤ የካህናት አለቆችም ፈሪሳውያም ሊይዙት ሎሌዎችን ላኩ።
32The Pharisees heard the crowd murmuring these things concerning him, and the Pharisees and the chief priests sent officers that they might take him.
33ኢየሱስም። ገና ጥቂት ጊዜ ከእናንተ ጋር እቆያለሁ ወደ ላከኝም እሄዳለሁ።
33Jesus therefore said, Yet a little while I am with you, and I go to him that has sent me.
34ትፈልጉኛላችሁ አታገኙኝምም፤ እኔም ወዳለሁበት እናንተ ልትመጡ አትችሉም አለ።
34Ye shall seek me and shall not find [me], and where I am ye cannot come.
35እንግዲህ አይሁድ። እኛ እንዳናገኘው ይህ ወዴት ይሄድ ዘንድ አለው? በግሪክ ሰዎች መካከል ተበትነው ወደሚኖሩት ሊሄድና የግሪክን ሰዎች ሊያስተምር አለውን?
35The Jews therefore said to one another, Where is he about to go that we shall not find him? Is he about to go to the dispersion among the Greeks, and teach the Greeks?
36እርሱ። ትፈልጉኛላችሁ አታገኙኝምም እኔም ወዳለሁበት እናንተ ልትመጡ አትችሉም የሚለው ይህ ቃል ምንድር ነው? ብለው እርስ በርሳቸው ተነጋገሩ።
36What word is this which he said, Ye shall seek me and shall not find [me]; and where I am ye cannot come?
37ከበዓሉም በታላቁ በኋለኛው ቀን ኢየሱስ ቆሞ። ማንም የተጠማ ቢኖር ወደ እኔ ይምጣና ይጠጣ።
37In the last, the great day of the feast, Jesus stood and cried saying, If any one thirst, let him come to me and drink.
38በእኔ የሚያምን መጽሐፍ እንዳለ፥ የሕይወት ውኃ ወንዝ ከሆዱ ይፈልቃል ብሎ ጮኸ።
38He that believes on me, as the scripture has said, out of his belly shall flow rivers of living water.
39ይህን ግን በእርሱ የሚያምኑ ሊቀበሉት ስላላቸው ስለ መንፈስ ተናገረ፤ ኢየሱስ ገና ስላልከበረ መንፈስ ገና አልወረደም ነበርና።
39But this he said concerning the Spirit, which they that believed on him were about to receive; for [the] Spirit was not yet, because Jesus had not yet been glorified.
40ስለዚህ ከሕዝቡ አያሌ ሰዎች ይህን ቃል ሲሰሙ። ይህ በእውነት ነቢዩ ነው አሉ፤
40[Some] out of the crowd therefore, having heard this word, said, This is truly the prophet.
41ሌሎች። ይህ ክርስቶስ ነው አሉ፤ ሌሎች ግን። ክርስቶስ በእውኑ ከገሊላ ይመጣልን?
41Others said, This is the Christ. Others said, Does then the Christ come out of Galilee?
42ክርስቶስ ከዳዊት ዘር ዳዊትም ከነበረባት መንደር ከቤተ ልሔም እንዲመጣ መጽሐፍ አላለምን? አሉ።
42Has not the scripture said that the Christ comes of the seed of David, and from the village of Bethlehem, where David was?
43እንግዲህ ከእርሱ የተነሣ በሕዝቡ መካከል መለያየት ሆነ፤
43There was a division therefore in the crowd on account of him.
44ከእነርሱም አንዳንዶቹ ሊይዙት ወደዱ ነገር ግን እጁን ማንም አልጫነበትም።
44But some of them desired to take him, but no one laid hands upon him.
45ሎሌዎቹም ወደ ካህናት አለቆችና ወደ ፈሪሳውያን መጡ፤ እነዚያም። ያላመጣችሁት ስለ ምን ነው? አሉአቸው።
45The officers therefore came to the chief priests and Pharisees, and they said to them, Why have ye not brought him?
46ሎሌዎቹ። እንደዚህ ሰው ማንም እንዲሁ ከቶ አልተናገረም ብለው መለሱ።
46The officers answered, Never man spoke thus, as this man [speaks].
47እንግዲህ ፈሪሳውያን። እናንተ ደግሞ ሳታችሁን?
47The Pharisees therefore answered them, Are ye also deceived?
48ከአለቆች ወይስ ከፈሪሳውያን በእርሱ ያመነ አለን?
48Has any one of the rulers believed on him, or of the Pharisees?
49ነገር ግን ሕግን የማያውቀው ይህ ሕዝብ ርጉም ነው ብለው መለሱላቸው።
49But this crowd, which does not know the law, are accursed.
50ከእነርሱ አንዱ በሌሊት ቀድሞ ወደ እርሱ መጥቶ የነበረ ኒቆዲሞስ።
50Nicodemus says to them (being one of themselves),
51ሕጋችን አስቀድሞ ከእርሱ ሳይሰማ ምንስ እንዳደረገ ሳያውቅ በሰው ይፈርዳልን? አላቸው።
51Does our law judge a man before it have first heard from himself, and know what he does?
52እነርሱም መለሱና። አንተም ደግሞ ከገሊላ ነህን? ነቢይ ከገሊላ እንዳይነሣ መርምርና እይ አሉት።
52They answered and said to him, Art thou also of Galilee? Search and look, that no prophet arises out of Galilee.
53እያንዳንዱም ወደ ቤቱ ሄደ።
53And every one went to his home.