1ፋሲካም የሚባለው የቂጣ በዓል ቀረበ።
1Now the feast of unleavened bread, which [is] called the passover, drew nigh,
2የካህናት አለቆችና ጻፎችም እንዴት እንዲያጠፉት ይፈልጉ ነበር፤ ሕዝቡን ይፈሩ ነበርና።
2and the chief priests and the scribes sought how they might kill him; for they feared the people.
3ሰይጣንም ከአሥራ ሁለቱ ቍጥር አንዱ በነበረው የአስቆሮቱ በሚባለው በይሁዳ ገባ፤
3And Satan entered into Judas, who was surnamed Iscariote, being of the number of the twelve.
4ሄዶም እንዴት አሳልፎ እንዲሰጣቸው ከካህናት አለቆችና ከመቅደስ አዛዦች ጋር ተነጋገረ።
4And he went away and spoke with the chief priests and captains as to how he should deliver him up to them.
5እነርሱም ደስ አላቸው፥ ገንዘብም ሊሰጡት ተዋዋሉ።
5And they were rejoiced, and agreed to give him money.
6እሺም አለ፥ ሕዝብም በሌለበት አሳልፎ እንዲሰጣቸው ምቹ ጊዜ ይፈልግ ነበር።
6And he came to an agreement to do it, and sought an opportunity to deliver him up to them away from the crowd.
7ፋሲካንም ሊያርዱበት የሚገባው የቂጣ በዓል ደረሰ፤
7And the day of unleavened bread came, in which the passover was to be killed.
8ጴጥሮስንና ዮሐንስንም። ፋሲካን እንድንበላ ሄዳችሁ አዘጋጁልን ብሎ ላካቸው።
8And he sent Peter and John, saying, Go and prepare the passover for us, that we may eat [it].
9እነርሱም። ወዴት እናዘጋጅ ዘንድ ትወዳለህ? አሉት።
9But they said to him, Where wilt thou that we prepare [it]?
10እርሱም አላቸው። እነሆ፥ ወደ ከተማ ስትገቡ ማድጋ ውኃ የተሸከመ ሰው ይገናኛችኋል፤ ወደ ሚገባበት ቤት ተከተሉት፤
10And he said to them, Behold, as ye enter into the city a man will meet you, carrying an earthen pitcher of water; follow him into the house where he goes in;
11ለባለቤቱም። መምህሩ። ከደቀ መዛሙርቴ ጋር ፋሲካን የምበላበት የእንግዳ ቤት ክፍል ወዴት ነው? ይልሃል በሉት፤
11and ye shall say to the master of the house, The Teacher says to thee, Where is the guest-chamber where I may eat the passover with my disciples?
12ያም በደርብ ላይ ያለውን የተነጠፈ ታላቅ አዳራሽ ያሳያችኋል፤ በዚያም አሰናዱልን።
12And *he* will shew you a large upper room furnished: there make ready.
13ሄደውም እንዳላቸው አገኙና ፋሲካን አሰናዱ።
13And having gone they found it as he had said to them; and they prepared the passover.
14ሰዓቱም በደረሰ ጊዜ ከአሥራ ሁለቱ ሐዋርያት ጋር በማዕድ ተቀመጠ።
14And when the hour was come, he placed himself at table, and the [twelve] apostles with him.
15እርሱም። ከመከራዬ በፊት ከእናንተ ጋር ይህን ፋሲካ ልበላ እጅግ እመኝ ነበር፤
15And he said to them, With desire I have desired to eat this passover with you before I suffer.
16እላችኋለሁና፥ በእግዚአብሔር መንግሥት እስኪፈጸም ድረስ፥ ወደ ፊት ከዚህ አልበላም አላቸው።
16For I say unto you, that I will not eat any more at all of it until it be fulfilled in the kingdom of God.
17ጽዋንም ተቀበለ አመስግኖም። ይህን እንካችሁ በመካከላችሁም ተካፈሉት፤
17And having received a cup, when he had given thanks he said, Take this and divide it among yourselves.
18እላችኋለሁና፥ የእግዚአብሔር መንግሥት እስክትመጣ ድረስ ከአሁን ጀምሮ ከወይኑ ፍሬ አልጠጣም አለ።
18For I say unto you, that I will not drink at all of the fruit of the vine until the kingdom of God come.
19እንጀራንም አንሥቶ አመሰገነ ቆርሶም ሰጣቸውና። ስለ እናንተ የሚሰጠው ሥጋዬ ይህ ነው፤ ይህን ለመታሰቢያዬ አድርጉት አለ።
19And having taken a loaf, when he had given thanks, he broke [it], and gave [it] to them, saying, This is my body which is given for you: this do in remembrance of me.
20እንዲሁም ከእራት በኋላ ጽዋውን አንሥቶ እንዲህ አለ። ይህ ጽዋ ስለ እናንተ በሚፈሰው በደሜ የሚሆን አዲስ ኪዳን ነው።
20In like manner also the cup, after having supped, saying, This cup [is] the new covenant in my blood, which is poured out for you.
21ነገር ግን አሳልፎ የሚሰጠኝ እጅ እነሆ በማዕድ ከእኔ ጋር ናት።
21Moreover, behold, the hand of him that delivers me up [is] with me on the table;
22የሰው ልጅስ እንደ ተወሰነው ይሄዳል፥ ነገር ግን አልፎ ለሚሰጥበት ለዚያ ሰው ወዮለት።
22and the Son of man indeed goes as it is determined, but woe unto that man by whom he is delivered up.
23ከእነርሱም ይህን ሊያደርግ ያለው ማን እንደ ሆነ እርስ በርሳቸው ይጠያየቁ ጀመር።
23And *they* began to question together among themselves who then it could be of them who was about to do this.
24ደግሞም ማናቸውም ታላቅ ሆኖ እንዲቈጠር በመካከላቸው ክርክር ሆነ።
24And there was also a strife among them which of them should be held to be [the] greatest.
25እንዲህም አላቸው። የአሕዛብ ነገሥታት ይገዙአቸዋል፥ በላያቸውም የሚሠለጥኑት ቸርነት አድራጊዎች ይባላሉ።
25And he said to them, The kings of the nations rule over them, and they that exercise authority over them are called benefactors.
26እናንተ ግን እንዲህ አትሁኑ፤ ነገር ግን ከእናንተ ታላቅ የሆነ በመካከላችሁ እንደ ታናሽ፥ የሚገዛም እንደሚያገለግል ይሁን።
26But *ye* [shall] not [be] thus; but let the greater among you be as the younger, and the leader as he that serves.
27በማዕድ የተቀመጠ ወይስ የሚያገለግል ማናቸው ታላቅ ነው? የተቀመጠው አይደለምን? እኔ ግን በመካከላችሁ እንደሚያገለግል ነኝ።
27For which [is] greater, he that is at table or he that serves? [Is] not he that is at table? But *I* am in the midst of you as the one that serves.
28ነገር ግን እናንተ በፈተናዎቼ ከእኔ ጋር ጸንታችሁ የኖራችሁ ናችሁ፤
28But *ye* are they who have persevered with me in my temptations.
29አባቴ እኔን እንደ ሾመኝ እኔ ደግሞ በመንግሥቴ ከማዕዴ ትበሉና ትጠጡ ዘንድ፥ በአሥራ ሁለቱ በእስራኤል ነገድ ስትፈርዱ በዙፋኖች ትቀመጡ ዘንድ ለመንግሥት እሾማችኋለሁ።
29And *I* appoint unto you, as my Father has appointed unto me, a kingdom,
31ጌታም። ስምዖን ስምዖን ሆይ፥ እነሆ፥ ሰይጣን እንደ ስንዴ ሊያበጥራችሁ ለመነ፤
30that ye may eat and drink at my table in my kingdom, and sit on thrones judging the twelve tribes of Israel.
32እኔ ግን እምነትህ እንዳይጠፋ ስለ አንተ አማለድሁ፤ አንተም በተመለስህ ጊዜ ወንድሞችህን አጽና አለ።
31And the Lord said, Simon, Simon, behold, Satan has demanded to have you, to sift [you] as wheat;
33እርሱም። ጌታ ሆይ፥ ወደ ወኅኒም ወደ ሞትም ከአንተ ጋር ለመሄድ የተዘጋጀሁ ነኝ አለው።
32but *I* have besought for thee that thy faith fail not; and *thou*, when once thou hast been restored, confirm thy brethren.
34እርሱ ግን። ጴጥሮስ ሆይ፥ እልሃለሁ፥ እንዳታውቀኝ ሦስት ጊዜ እስክትክደኝ ድረስ ዛሬ ዶሮ አይጮኽም አለው።
33And he said to him, Lord, with thee I am ready to go both to prison and to death.
35ደግሞም። ያለ ኮረጆና ያለ ከረጢት ያለ ጫማም በላክኋችሁ ጊዜ፥ አንዳች ጐደለባችሁን? አላቸው። እነርሱም። አንዳች እንኳ አሉ።
34And he said, I tell thee, Peter, [the] cock shall not crow to-day before that thou shalt thrice deny that thou knowest me.
36እርሱም። አሁን ግን ኮረጆ ያለው ከእርሱ ጋር ይውሰድ፥ ከረጢትም ያለው እንዲሁ፤ የሌለውም ልብሱን ሽጦ ሰይፍ ይግዛ።
35And he said to them, When I sent you without purse and scrip and sandals, did ye lack anything? And they said, Nothing.
37እላችኋለሁና፥ ይህ። ከዓመፀኞች ጋር ተቈጠረ ተብሎ የተጻፈው በእኔ ሊፈጸም ግድ ነው፤ አዎን፥ ስለ እኔ የሚሆነው አሁን ይፈጸማልና አላቸው።
36He said therefore to them, But now he that has a purse let him take [it], in like manner also a scrip, and he that has none let him sell his garment and buy a sword;
38እነርሱም። ጌታ ሆይ፥ እነሆ፥ በዚህ ሁለት ሰይፎች አሉ አሉት። እርሱም። ይበቃል አላቸው።
37for I say unto you, that this that is written must yet be accomplished in me, And he was reckoned with [the] lawless: for also the things concerning me have an end.
39ወጥቶም እንደ ልማዱ ወደ ደብረ ዘይት ሄደ፤ ደቀ መዛሙርቱም ደግሞ ተከተሉት።
38And they said, Lord, behold here are two swords. And he said to them, It is enough.
40ወደ ስፍራውም ደርሶ። ወደ ፈተና እንዳትገቡ ጸልዩ አላቸው።
39And going forth he went according to his custom to the mount of Olives, and the disciples also followed him.
41ከእነርሱም የድንጋይ ውርወራ የሚያህል ራቀ፥ ተንበርክኮም። አባት ሆይ፥
40And when he was at the place he said to them, Pray that ye enter not into temptation.
42ብትፈቅድ ይህችን ጽዋ ከእኔ ውሰድ፤ ነገር ግን የእኔ ፈቃድ አይሁን የአንተ እንጂ እያለ ይጸልይ ነበር።
41And he was withdrawn from them about a stone's throw, and having knelt down he prayed,
43ከሰማይም መጥቶ የሚያበረታ መልአክ ታየው።
42saying, Father, if thou wilt remove this cup from me: -- but then, not my will, but thine be done.
44በፍርሃትም ሲጣጣር አጽንቶ ይጸልይ ነበር፤ ወዙም በምድር ላይ እንደሚወርድ እንደ ደም ነጠብጣብ ነበረ።
43And an angel appeared to him from heaven strengthening him.
45ከጸሎትም ተነሥቶ ወደ ደቀ መዛሙርቱ መጣና ከኀዘን የተነሣ ተኝተው ሲያገኛቸው።
44And being in conflict he prayed more intently. And his sweat became as great drops of blood, falling down upon the earth.
46ስለ ምን ትተኛላችሁ? ወደ ፈተና እንዳትገቡ ተነሥታችሁ ጸልዩ አላቸው።
45And rising up from his prayer, coming to the disciples, he found them sleeping from grief.
47ገናም ሲናገር እነሆ፥ ሰዎች መጡ፤ ከአሥራ ሁለቱ አንዱም ይሁዳ የሚባለው ይቀድማቸው ነበር፥ ሊስመውም ወደ ኢየሱስ ቀረበ።
46And he said to them, Why sleep ye? rise up and pray that ye enter not into temptation.
48ኢየሱስ ግን። ይሁዳ ሆይ፥ በመሳም የሰውን ልጅ አሳልፈህ ትሰጣለህን? አለው።
47As he was yet speaking, behold, a crowd, and he that was called Judas, one of the twelve, went on before them, and drew near to Jesus to kiss him.
49በዙሪያውም የነበሩት የሚሆነውን ባዩ ጊዜ። ጌታ ሆይ፥ በሰይፍ እንምታቸውን? አሉት።
48And Jesus said to him, Judas, deliverest thou up the Son of man with a kiss?
50ከእነርሱም አንዱ የሊቀ ካህናቱን ባሪያ መትቶ ቀኝ ጆሮውን ቈረጠው።
49And they who were around him, seeing what was going to follow, said [to him], Lord, shall we smite with [the] sword?
51ኢየሱስ ግን መልሶ። ይህንስ ፍቀዱ አለ፤ ጆሮውንም ዳስሶ ፈወሰው።
50And a certain one from among them smote the bondman of the high priest and took off his right ear.
52ኢየሱስም ወደ እርሱ ለመጡበት ለካህናት አለቆችና ለመቅደስ አዛዦች ለሽማግሌዎችም። ወንበዴን እንደምትይዙ ሰይፍና ጐመድ ይዛችሁ ወጣችሁን?
51And Jesus answering said, Suffer thus far; and having touched his ear, he healed him.
53በመቅደስ ዕለት ዕለት ከእናንተ ጋር ስሆን እጆቻችሁን አልዘረጋችሁብኝም፤ ይህ ግን ጊዜያችሁና የጨለማው ሥልጣን ነው አላቸው።
52And Jesus said to the chief priests and captains of the temple and elders, who were come against him, Have ye come out as against a robber with swords and sticks?
54ይዘውም ወሰዱት ወደ ሊቀ ካህናት ቤትም አገቡት፤ ጴጥሮስም ርቆ ይከተለው ነበር።
53When I was day by day with you in the temple ye did not stretch out your hands against me; but this is your hour and the power of darkness.
55በግቢ መካከልም እሳት አንድደው በአንድነት ተቀምጠው ሳሉ ጴጥሮስ በመካከላቸው ተቀመጠ።
54And having laid hold on him, they led him [away], and they led [him] into the house of the high priest. And Peter followed afar off.
56በብርሃኑም በኩል ተቀምጦ ሳለ አንዲት ገረድ አየችውና ትኵር ብላ። ይህ ደግሞ ከእርሱ ጋር ነበረ አለች።
55And they having lit a fire in the midst of the court and sat down together, Peter sat among them.
57እርሱ ግን። አንቺ ሴት፥ አላውቀውም ብሎ ካደ።
56And a certain maid, having seen him sitting by the light, and having fixed her eyes upon him, said, And this [man] was with him.
58ከጥቂት ጊዜም በኋላ ሌላው አይቶት። አንተ ደግሞ ከእነርሱ ወገን ነህ አለው። ጴጥሮስ ግን። አንተ ሰው፥ እኔ አይደለሁም አለ።
57But he denied [him], saying, Woman, I do not know him.
59አንድ ሰዓትም የሚያህል ቆይቶ ሌላው አስረግጦ። እርሱ የገሊላ ሰው ነውና በእውነት ይህ ደግሞ ከእርሱ ጋር ነበረ አለ።
58And after a short time another seeing him said, And *thou* art of them. But Peter said, Man, I am not.
60ጴጥሮስ ግን። አንተ ሰው፥ የምትለውን አላውቅም አለ። ያን ጊዜም ገና ሲናገር ዶሮ ጮኸ።
59And after the lapse of about one hour another stoutly maintained it, saying, In truth this [man] also was with him, for also he is a Galilaean.
61ጌታም ዘወር ብሎ ጴጥሮስን ተመለከተው፤ ጴጥሮስም። ዛሬ ዶሮ ሳይጮኽ ሦስት ጊዜ ትክደኛለህ እንዳለው የጌታ ቃል ትዝ አለው።
60And Peter said, Man, I know not what thou sayest. And immediately, while he was yet speaking, [the] cock crew.
62ጴጥሮስም ወደ ውጭ ወጥቶ ምርር ብሎ አለቀሰ።
61And the Lord, turning round, looked at Peter; and Peter remembered the word of the Lord, how he said to him, Before [the] cock crow thou shalt deny me thrice.
63ኢየሱስንም የያዙት ሰዎች ይዘብቱበትና ይደበድቡት ነበር፤
62And Peter, going forth without, wept bitterly.
64ሸፍነውም ፊቱን ይመቱት ነበርና። በጥፊ የመታህ ማን ነው? ትንቢት ተናገር እያሉ ይጠይቁት ነበር።
63And the men who held him mocked him, beating [him];
65ሌላም ብዙ ነገር እየተሳደቡ በእርሱ ላይ ይናገሩ ነበር።
64and covering him up, asked him saying, Prophesy, who is it that struck thee?
66በነጋም ጊዜ የሕዝቡ ሽማግሌዎችና የካህናት አለቆች ጻፎችም ተሰብስበው ወደ ሸንጎአቸው ወሰዱትና
65And they said many other injurious things to him.
67ክርስቶስ አንተ ነህን? ንገረን አሉት። እርሱ ግን እንዲህ አላቸው። ብነግራችሁ አታምኑም፤
66And when it was day, the elderhood of the people, both [the] chief priests and scribes, were gathered together, and led him into their council, saying,
68ብጠይቅም አትመልሱልኝም አትፈቱኝምም።
67If *thou* art the Christ, tell us. And he said to them, If I tell you, ye will not at all believe;
69ነገር ግን ከአሁን ጀምሮ የሰው ልጅ በእግዚአብሔር ኃይል ቀኝ ይቀመጣል።
68and if I should ask [you], ye would not answer me at all, nor let me go;
70ሁላቸውም። እንግዲያስ አንተ የእግዚአብሔር ልጅ ነህን? አሉት። እርሱም። እኔ እንደ ሆንሁ እናንተ ትላላችሁ አላቸው።
69but henceforth shall the Son of man be sitting on the right hand of the power of God.
71እነርሱም። ራሳችን ከአፉ ሰምተናልና ከእንግዲህ ወዲህ ምን ምስክር ያስፈልገናል? አሉ።
70And they all said, *Thou* then art the Son of God? And he said to them, *Ye* say that I am.
71And they said, What need have we any more of witness, for we have heard ourselves out of his mouth?