1የእግዚአብሔር ልጅ የኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌል መጀመሪያ።
1Beginning of the glad tidings of Jesus Christ, Son of God;
2እነሆ፥ መንገድህን የሚጠርግ መልክተኛዬን በፊትህ እልካለሁ የጌታን መንገድ አዘጋጁ ጥርጊያውንም አቅኑ እያለ በምድረ በዳ የሚጮኽ ሰው ድምፅ ተብሎ በነቢዩ በኢሳይያስ እንደ ተጻፈ፥
2as it is written in [Isaiah] the prophet, Behold, *I* send my messenger before thy face, who shall prepare thy way.
4ዮሐንስ በምድረ በዳ እያጠመቀ የንስሐንም ጥምቀት ለኃጢአት ስርየት እየሰበከ መጣ።
3Voice of one crying in the wilderness, Prepare the way of [the] Lord, make his paths straight.
5የይሁዳም አገር ሁሉ የኢየሩሳሌምም ሰዎች ሁሉ ወደ እርሱ ይወጡ ነበር፥ ኃጢአታቸውንም እየተናዘዙ በዮርዳኖስ ወንዝ ከእርሱ ይጠመቁ ነበር።
4There came John baptising in the wilderness, and preaching [the] baptism of repentance for remission of sins.
6ዮሐንስም የግመል ጠጉር ለብሶ በወገቡ ጠፍር ይታጠቅ አንበጣና የበረሀ ማርም ይበላ ነበር።
5And there went out to him all the district of Judaea, and all they of Jerusalem, and were baptised by him in the river Jordan, confessing their sins.
7ተጎንብሼ የጫማውን ጠፍር መፍታት የማይገባኝ ከእኔ የሚበረታ በኋላዬ ይመጣል።
6And John was clothed in camel's hair, and a leathern girdle about his loins, and ate locusts and wild honey.
8እኔ በውኃ አጠመቅኋችሁ እርሱ ግን በመንፈስ ቅዱስ ያጠምቃችኋል እያለ ይሰብክ ነበር።
7And he preached, saying, There comes he that is mightier than I after me, the thong of whose sandals I am not fit to stoop down and unloose.
9በዚያ ወራትም ኢየሱስ ከገሊላ ናዝሬት መጥቶ ከዮሐንስ በዮርዳኖስ ወንዝ ተጠመቀ።
8*I* indeed have baptised you with water, but *he* shall baptise you with [the] Holy Spirit.
10ወዲያውም ከውኃው በወጣ ጊዜ ሰማያት ሲቀደዱ መንፈስም እንደ ርግብ ሲወርድበት አየና። የምወድህ ልጄ አንተ ነህ፥
9And it came to pass in those days [that] Jesus came from Nazareth of Galilee, and was baptised by John at the Jordan.
11በአንተ ደስ ይለኛል የሚል ድምፅ ከሰማያት መጣ።
10And straightway going up from the water, he saw the heavens parting asunder, and the Spirit, as a dove, descending upon him.
12ወዲያውም መንፈስ ወደ ምድረ በዳ አወጣው።
11And there came a voice out of the heavens: *Thou* art my beloved Son, in thee I have found my delight.
13በምድረ በዳም ከሰይጣን እየተፈተነ አርባ ቀን ሰነበተ ከአራዊትም ጋር ነበረ፥ መላእክቱም አገለገሉት።
12And immediately the Spirit drives him out into the wilderness.
14ዮሐንስም አልፎ ከተሰጠ በኋላ ኢየሱስ የእግዚአብሔርን መንግሥት ወንጌል እየሰበከና። ዘመኑ ተፈጸመ የእግዚአብሔርም መንግሥት ቀርባለች ንስሐ ግቡ በወንጌልም እመኑ እያለ ወደ ገሊላ መጣ።
13And he was in the wilderness forty days tempted by Satan, and was with the wild beasts; and the angels ministered to him.
16በገሊላ ባሕርም አጠገብ ሲያልፍ ስምዖንን ወንድሙንም እንድርያስን መረባቸውን ወደ ባሕር ሲጥሉ አየ፥ ዓሣ አጥማጆች ነበሩና።
14But after John was delivered up, Jesus came into Galilee preaching the glad tidings of the kingdom of God,
17ኢየሱስም። በኋላዬ ኑና ሰዎችን አጥማጆች እንድትሆኑ አደርጋችኋለሁ አላቸው።
15and saying, The time is fulfilled and the kingdom of God has drawn nigh; repent and believe in the glad tidings.
18ወዲያውም መረባቸውን ትተው ተከተሉት።
16And walking by the sea of Galilee, he saw Simon, and Andrew, [Simon's] brother, casting out a net in the sea, for they were fishers.
19ከዚያም ጥቂት እልፍ ብሎ የዘብዴዎስን ልጅ ያዕቆብን ወንድሙንም ዮሐንስን ደግሞ በታንኳ ላይ መረባቸውን ሲያበጁ አየ።
17And Jesus said to them, Come after me, and I will make you become fishers of men;
20ወዲያውም ጠራቸው አባታቸውንም ዘብዴዎስን ከሞያተኞቹ ጋር በታንኳ ላይ ትተው ተከትለውት ሄዱ።
18and straightway leaving their trawl-nets they followed him.
21ወደ ቅፍርናሆምም ገቡ፤ ወዲያውም በሰንበት ወደ ምኵራብ ገብቶ አስተማረ።
19And going on thence a little, he saw James the [son] of Zebedee, and John his brother, and these [were] in the ship repairing the trawl-nets;
22እንደ ባለ ሥልጣን ያስተምራቸው ነበር እንጂ እንደ ጻፎች አይደለምና በትምህርቱ ተገረሙ።
20and straightway he called them; and leaving their father Zebedee in the ship with the hired servants, they went away after him.
23በዚያን ጊዜም በምኩራባቸው ርኵስ መንፈስ ያለው ሰው ነበረ፤
21And they go into Capernaum. And straightway on the sabbath he entered into the synagogue and taught.
24እርሱም። የናዝሬቱ ኢየሱስ ሆይ፥ ከአንተ ጋር ምን አለን? ልታጠፋን መጣህን? ማን እንደ ሆንህ አውቄአለሁ፥ የእግዚአብሔር ቅዱሱ ብሎ ጮኸ።
22And they were astonished at his doctrine, for he taught them as having authority, and not as the scribes.
25ኢየሱስም። ዝም በል ከእርሱም ውጣ ብሎ ገሠጸው።
23And there was in their synagogue a man [possessed] by an unclean spirit, and he cried out
26ርኵሱም መንፈስ አንፈራገጠውና በታላቅ ድምፅ ጮኾ ከእርሱ ወጣ።
24saying, Eh! what have we to do with thee, Jesus, Nazarene? Art thou come to destroy us? I know thee who thou art, the holy one of God.
27ሁሉም። ይህ ምንድር ነው? በሥልጣን ርኵሳን መናፍስትን ያዝዛል፤ እነርሱም ይታዘዙለታልና ይህ አዲስ ትምህርት ምንድር ነው? ብለው እስኪጠያየቁ ድረስ አደነቁ።
25And Jesus rebuked him, saying, Hold thy peace and come out of him.
28ዝናውም ወዲያው በየስፍራው ወደ ገሊላ ዙሪያ ሁሉ ወጣ።
26And the unclean spirit, having torn him, and uttered a cry with a loud voice, came out of him.
29ወዲያውም ከምኵራብ ወጥቶ ከያዕቆብና ከዮሐንስ ጋር ወደ ስምዖንና ወደ እንድርያስ ቤት ገባ።
27And all were amazed, so that they questioned together among themselves, saying, What is this? what new doctrine is this? for with authority he commands even the unclean spirits, and they obey him.
30የስምዖንም አማት በንዳድ ታማ ተኝታ ነበር፥ ስለ እርስዋም ወዲያው ነገሩት።
28And his fame went out straightway into the whole region of Galilee around.
31ቀርቦም እጅዋን ይዞ አስነሣት ንዳዱም ወዲያው ለቀቃትና አገለገለቻቸው።
29And straightway going out of the synagogue, they came with James and John into the house of Simon and Andrew.
32ፀሐይም ገብቶ በመሸ ጊዜ፥ የታመሙትንና አጋንንት ያደረባቸውን ሁሉ ወደ እርሱ አመጡ፤
30And the mother-in-law of Simon lay in a fever. And straightway they speak to him about her.
33ከተማይቱም ሁላ በደጅ ተሰብስባ ነበር።
31And he went up to [her] and raised her up, having taken her by the hand, and straightway the fever left her, and she served them.
34በልዩ ልዩ ደዌም የታመሙትን ብዙዎችን ፈወሰ፥ ብዙዎችንም አጋንንት አወጣ፥ አጋንንትም ክርስቶስ መሆኑን አውቀው ነበርና ሊናገሩ አልፈቀደላቸውም።
32But evening being come, when the sun had gone down, they brought to him all that were suffering, and those possessed by demons;
35ማለዳም ተነሥቶ ገና ሌሊት ሳለ ወጣ ወደ ምድረ በዳም ሄዶ በዚያ ጸለየ።
33and the whole city was gathered together at the door.
36ስምዖንና ከእርሱ ጋር የነበሩትም ገሥግሠው ተከተሉት፥
34And he healed many suffering from various diseases; and he cast out many demons, and did not suffer the demons to speak because they knew him.
37ባገኙትም ጊዜ። ሁሉ ይፈልጉሃል አሉት።
35And rising in the morning long before day, he went out and went away into a desert place, and there prayed.
38እርሱም። በዚያ ደግሞ ልሰብክ ወደ ሌላ ስፍራ በቅርብ ወዳሉ መንደሮች እንሂድ ስለዚህ ወጥቻለሁና አላቸው።
36And Simon and those with him went after him:
39በምኵራባቸውም እየሰበከ አጋንንትንም እያወጣ ወደ ገሊላ ሁሉ መጣ።
37and having found him, they say to him, All seek thee.
40ለምጻምም ወደ እርሱ መጥቶ ተንበረከከና። ብትወድስ ልታነጻኝ ትችላለህ ብሎ ለመነው።
38And he says to them, Let us go elsewhere into the neighbouring country towns, that I may preach there also, for for this purpose am I come forth.
41ኢየሱስም አዘነለት እጁንም ዘርግቶ ዳሰሰውና። እወድዳለሁ፤ ንጻ አለው።
39And he was preaching in their synagogues in the whole of Galilee, and casting out demons.
42በተናገረም ጊዜ ለምጹ ወዲያው ለቀቀውና ነጻ።
40And there comes to him a leper, beseeching him, and falling on his knees to him, and saying to him, If thou wilt thou canst cleanse me.
43በብርቱም ተናግሮ ወዲያው አወጣው፤
41But Jesus, moved with compassion, having stretched out his hand, touched him, and says to him, I will, be thou cleansed.
44ለማንም አንዳች እንዳትናገር ተጠንቀቅ፥ ነገር ግን ሄደህ ራስህን ለካህን አሳይ ለእነርሱም ምስክር እንዲሆን ስለ መንጻትህ ሙሴ ያዘዘውን አቅርብ አለው።
42And as he spoke straightway the leprosy left him, and he was cleansed.
45እርሱ ግን ሲወጣ ብዙ ሊሰብክና ነገሩን ሊያወራ ጀመረ፥ ስለዚህም ኢየሱስ ተገልጦ ወደ ከተማ መግባት ወደ ፊት ተሳነው፥ ነገር ግን በውጭ በምድረ በዳ ይኖር ነበር፤ ከየስፍራውም ወደ እርሱ ይመጡ ነበር።
43And having sharply charged him, he straightway sent him away,
44and says to him, See thou say nothing to any one, but go, shew thyself to the priest, and offer for thy cleansing what Moses ordained, for a testimony to them.
45But he, having gone forth, began to proclaim [it] much, and to spread the matter abroad, so that he could no longer enter openly into the city, but was without in desert places, and they came to him from every side.