1ወዲያውም ማለዳ የካህናት አለቆች ከሽማግሌዎችና ከጻፎች ከሸንጎውም ሁሉ ጋር ከተማከሩ በኋላ፥ ኢየሱስን አሳስረው ወሰዱትና ለጲላጦስ አሳልፈው ሰጡት።
1And immediately in the morning the chief priests, having taken counsel with the elders and scribes and the whole sanhedrim, bound Jesus and carried [him] away, and delivered [him] up to Pilate.
2ጲላጦስም። አንተ የአይሁድ ንጉሥ ነህን? ብሎ ጠየቀው። እርሱም። አንተ አልህ ብሎ መለሰለት።
2And Pilate asked him, Art *thou* the King of the Jews? And he answered and said to him, *Thou* sayest.
3የካህናት አለቆችም ብዙ ያሳጡት ነበር፤ እርሱ ግን ምንም አልመለሰም።
3And the chief priests accused him urgently.
4ጲላጦስም ደግሞ። አንዳች አትመልስምን? እነሆ፥ በስንት ነገር ያሳጡሃል ብሎ ጠየቀው።
4And Pilate asked him again, saying, Answerest thou nothing? See of how many things they bear witness against thee.
5ኢየሱስም ከዚያ በኋላ ጲላጦስ እስኪደነቅ ድረስ ምንም አልመለሰም።
5But Jesus still answered nothing, so that Pilate marvelled.
6በዚያም በዓል የለመኑትን አንድ እስረኛ ይፈታላቸው ነበር።
6But at [the] feast he released to them one prisoner, whomsoever they begged [of him].
7በዓመፅም ነፍስ ከገደሉት ከዓመፀኞች ጋር የታሰረ በርባን የተባለ ነበረ።
7Now there was the [person] named Barabbas bound with those who had made insurrection with [him], [and] that had committed murder in the insurrection.
8ሕዝቡም ወጥተው እንደ ልማዱ ያደርግላቸው ዘንድ እየጮኹ ይለምኑት ጀመር።
8And the crowd crying out began to beg [that he would do] to them as he had always done.
9ጲላጦስም። የአይሁድን ንጉሥ እፈታላችሁ ዘንድ ትወዳላችሁን? ብሎ መለሰላቸው፤
9But Pilate answered them saying, Will ye that I release to you the King of the Jews?
10የካህናት አለቆች በቅንዓት አሳልፈው እንደ ሰጡት ያውቅ ነበርና።
10for he knew that the chief priests had delivered him up through envy.
11የካህናት አለቆች ግን በርባንን በእርሱ ፈንታ ይፈታላቸው ዘንድ ሕዝቡን አወኩአቸው።
11But the chief priests stirred up the crowd that he might rather release Barabbas to them.
12ጲላጦስም ዳግመኛ መልሶ። እንግዲህ የአይሁድ ንጉሥ የምትሉትን ምን ላደርገው ትወዳላችሁ? አላቸው።
12And Pilate answering said to them again, What will ye then that I do [to him] whom ye call King of the Jews?
13እነርሱም ዳግመኛ። ስቀለው እያሉ ጮኹ።
13And they cried out again, Crucify him.
14ጲላጦስም። ምን ነው? ያደረገው ክፋት ምንድር ነው? አላቸው። እነርሱ ግን። ስቀለው እያሉ ጩኸት አበዙ።
14And Pilate said to them, What evil then has he done? But they cried out the more urgently, Crucify him.
15ጲላጦስም የሕዝቡን ፈቃድ ሊያደርግ ወዶ በርባንን ፈታላቸው፥ ኢየሱስንም ገርፎ እንዲሰቀል አሳልፎ ሰጠ።
15And Pilate, desirous of contenting the crowd, released to them Barabbas, and delivered up Jesus, when he had scourged him, that he might be crucified.
16ወታደሮችም ፕራይቶሪዮን ወደሚባል ግቢ ውስጥ ወሰዱት፥ ጭፍራውንም ሁሉ በአንድነት ጠሩ።
16And the soldiers led him away into the court which is [called the] praetorium, and they call together the whole band.
17ቀይ ልብስም አለበሱት፥ የእሾህ አክሊልም ጎንጉነው ደፉበት፤
17And they clothe him with purple, and bind round on him a crown of thorns which they had plaited.
18የአይሁድ ንጉሥ ሆይ፥ ሰላም ለአንተ ይሁን እያሉ እጅ ይነሱት ጀመር፤
18And they began to salute him, Hail, King of the Jews!
19ራሱንም በመቃ መቱት ተፉበትም፥ ተንበርክከውም ሰገዱለት።
19And they struck his head with a reed, and spat on him, and, bending the knee, did him homage.
20ከተዘባበቱበትም በኋላ ቀዩን ልብስ ገፈፉት፥ ልብሱንም አለበሱት፥ ሊሰቅሉትም ወሰዱት።
20And when they had mocked him, they took the purple off him, and put his own clothes on him; and they lead him out that they may crucify him.
21አንድ መንገድ አላፊም የአሌክስንድሮስና የሩፎስ አባት ስምዖን የተባለ የቀሬና ሰው ከገጠር ሲመጣ መስቀሉን ይሸከም ዘንድ አስገደዱት።
21And they compel to go [with them] a certain passer-by, Simon, a Cyrenian, coming from the field, the father of Alexander and Rufus, that he might carry his cross.
22ትርጓሜውም የራስ ቅል ስፍራ ወደሚሆን ጎልጎታ ወደተባለ ስፍራ ወሰዱት።
22And they bring him to the place [called] Golgotha, which, being interpreted, is Place of a skull.
23ከርቤም የተቀላቀለበትን የወይን ጠጅ እንዲጠጣ ሰጡት፤ እርሱ ግን አልተቀበለም።
23And they offered him wine [to drink] medicated with myrrh; but he did not take [it].
24ሰቀሉትም፥ ልብሱንም ማን ማን እንዲወስድ ዕጣ ተጣጥለው ተካፈሉ።
24And having crucified him, they part his clothes amongst [themselves], casting lots on them, what each one should take.
25በሰቀሉትም ጊዜ ሦስት ሰዓት ነበረ።
25And it was the third hour, and they crucified him.
26የክሱ ጽሕፈትም። የአይሁድ ንጉሥ የሚል ተጽፎ ነበር።
26And the superscription of what he was accused of was written up: The King of the Jews.
27ከእርሱም ጋር ሁለት ወንበዶች አንዱን በቀኙ አንዱንም በግራው ሰቀሉ።
27And with him they crucify two robbers, one on his right hand, and one on his left.
28መጽሐፍም። ከአመፀኞች ጋር ተቆጠረ ያለው ተፈጸመ።
28[And the scripture was fulfilled which says, And he was reckoned with the lawless.]
29የሚያልፉትም ራሳቸውን እየነቀነቁ ይሰድቡት ነበርና። ዋ፥ ቤተ መቅደስን የምታፈርስ በሦስት ቀንም የምትሠራ፥
29And they that passed by reviled him, shaking their heads, and saying, Aha, thou that destroyest the temple and buildest it in three days,
30ከመስቀል ወርደህ ራስህን አድን አሉ።
30save thyself, and descend from the cross.
31እንዲሁም የካህናት አለቆች ደግሞ ከጻፎች ጋር እርስ በርሳቸው እየተዘባበቱ። ሌሎችን አዳነ፤ ራሱን ሊያድን አይችልም፤
31In like manner the chief priests also, with the scribes, mocking with one another, said, He saved others; himself he cannot save.
32አይተን እናምን ዘንድ የእስራኤል ንጉሥ ክርስቶስ አሁን ከመስቀል ይውረድ አሉ። ከእርሱም ጋር የተሰቀሉት ይነቅፉት ነበር።
32Let the Christ the King of Israel descend now from the cross, that we may see and may believe. And they that were crucified with him reproached him.
33ስድስት ሰዓትም በሆነ ጊዜ፥ እስከ ዘጠኝ ሰዓት በምድር ሁሉ ላይ ጨለማ ሆነ።
33And when [the] sixth hour was come, there came darkness over the whole land until [the] ninth hour;
34በዘጠኝ ሰዓትም ኢየሱስ። ኤሎሄ፥ ኤሎሄ፥ ላማ ሰበቅታኒ? ብሎ በታላቅ ድምፅ ጮኸ፤ ትርጓሜውም አምላኬ፥ አምላኬ፥ ለምን ተውኸኝ? ማለት ነው።
34and at the ninth hour, Jesus cried with a loud voice, [saying], Eloi, Eloi, lama sabachthani? which is, being interpreted, My God, my God, why hast thou forsaken me?
35በዚያም ከቆሙት ሰዎች ሰምተው። እነሆ፥ ኤልያስን ይጠራል አሉ።
35And some of those who stood by, when they heard [it], said, Behold, he calls for Elias.
36አንዱም ሮጦ ሆምጣጤ በሰፍነግ ሞላ በመቃም አድርጎ። ተዉ፤ ኤልያስ ሊያወርደው ይመጣ እንደ ሆነ እንይ እያለ አጠጣው።
36And one, running and filling a sponge with vinegar, fixed it on a reed, and gave him to drink, saying, Let alone, let us see if Elias comes to take him down.
37ኢየሱስም በታላቅ ድምፅ ጮኸ ነፍሱንም ሰጠ።
37And Jesus, having uttered a loud cry, expired.
38የቤተ መቅደስም መጋረጃ ከላይ እስከ ታች ከሁለት ተቀደደ።
38And the veil of the temple was rent in two from the top to the bottom.
39በዚያም በአንጻሩ የቆመ የመቶ አለቃ እንደዚህ ጮኾ ነፍሱን እንደ ሰጠ ባየ ጊዜ። ይህ ሰው በእውነት የእግዚአብሔር ልጅ ነበረ አለ።
39And the centurion who stood by over against him, when he saw that he had expired having thus cried out, said, Truly this man was Son of God.
40ሴቶችም ደግሞ በሩቅ ሆነው ይመለከቱ ነበር፤ ከእነርሱም በገሊላ ሳለ ይከተሉትና ያገለግሉት የነበሩ መግደላዊት ማርያም የታናሹ ያዕቆብና የዮሳም እናት ማርያም ሰሎሜም ነበሩ፥ ከእርሱም ጋር ወደ ኢየሩሳሌም የወጡ ሌሎች ብዙዎች ሴቶች ነበሩ።
40And there were women also looking on from afar off, among whom were both Mary of Magdala, and Mary the mother of James the less and of Joses, and Salome;
42አሁንም በመሸ ጊዜ የሰንበት ዋዜማ የሆነ የማዘጋጀት ቀን ስለ ነበረ፥ የከበረ አማካሪ የሆነ የአርማትያስ ዮሴፍ መጣ፥
41who also, when he was in Galilee, followed him and ministered to him; and many others who came up with him to Jerusalem.
43እርሱም ደግሞ የእግዚአብሔርን መንግሥት ይጠባበቅ ነበር፤ ደፍሮም ወደ ጲላጦስ ገባና የኢየሱስን ሥጋ ለመነው።
42And when it was already evening, since it was [the] preparation, that is, [the day] before a sabbath,
44ጲላጦስም አሁኑን እንዴት ሞተ ብሎ ተደነቀ፥ የመቶ አለቃውንም ጠርቶ ከሞተ ቆይቶአልን? ብሎ ጠየቀው፤
43Joseph of Arimathaea, an honourable councillor, who also himself was awaiting the kingdom of God, coming, emboldened himself and went in to Pilate and begged the body of Jesus.
45ከመቶ አለቃውም ተረድቶ በድኑን ለዮሴፍ ሰጠው።
44And Pilate wondered if he were already dead; and having called to [him] the centurion, he inquired of him if he had long died.
46በፍታም ገዝቶ አውርዶም በበፍታ ከፈነው ከዓለትም በተወቀረ መቃብር አኖረው፥ በመቃብሩ ደጃፍም ድንጋይ አንከባለለ።
45And when he knew from the centurion, he granted the body to Joseph.
47መግደላዊትም ማርያም የዮሳም እናት ማርያም ወዴት እንዳኖሩት ይመለከቱ ነበር።
46And having bought fine linen, [and] having taken him down, he swathed him in the fine linen, and laid him in a sepulchre which was cut out of rock, and rolled a stone to the door of the sepulchre.
47And Mary of Magdala and Mary the [mother] of Joses saw where he was put.