Amharic: New Testament

Darby's Translation

Matthew

14

1በዚያ ዘመን የአራተኛው ክፍል ገዥ ሄሮድስ የኢየሱስን ዝና ሰማ፥
1At that time Herod the tetrarch heard of the fame of Jesus,
2ለሎሌዎቹም። ይህ መጥምቁ ዮሐንስ ነው፤ እርሱ ከሙታን ተነሥቶአል፥ ስለዚህም ኃይል በእርሱ ይደረጋል አለ።
2and said to his servants, This is John the baptist: *he* is risen from the dead, and because of this these works of power display their force in him.
3ሄሮድስ በወንድሙ በፊልጶስ ሚስት በሄሮድያዳ ምክንያት ዮሐንስን አስይዞ አሳስሮት በወህኒ አኑሮት ነበርና፤
3For Herod had seized John, and had bound him and put him in prison on account of Herodias the wife of Philip his brother.
4ዮሐንስ። እርስዋ ለአንተ ትሆን ዘንድ አልተፈቀደም ይለው ነበርና።
4For John said to him, It is not lawful for thee to have her.
5ሊገድለውም ወዶ ሳለ፥ ሕዝቡ እንደ ነቢይ ስለ አዩት ፈራቸው።
5And [while] desiring to kill him, he feared the crowd, because they held him for a prophet.
6ነገር ግን ሄሮድስ የተወለደበት ቀን በሆነ ጊዜ፥ የሄሮድያዳ ልጅ በመካከላቸው ዘፈነች ሄሮድስንም ደስ አሰኘችው፤
6But when Herod's birthday was celebrated, the daughter of Herodias danced before them, and pleased Herod;
7ስለዚህም የምትለምነውን ሁሉ እንዲሰጣት በመሐላ ተስፋ አደረገላት።
7whereupon he promised with oath to give her whatsoever she should ask.
8እርስዋም በእናትዋ ተመክራ። የመጥምቁን የዮሐንስን ራስ በዚህ በወጭት ስጠኝ አለችው።
8But she, being set on by her mother, says, Give me here upon a dish the head of John the baptist.
9ንጉሡም አዘነ፥ ነገር ግን ስለ መሐላው ከእርሱም ጋር ተቀምጠው ስላሉት ሰዎች እንዲሰጡአት አዘዘ፤
9And the king was grieved; but on account of the oaths, and those lying at table with [him], he commanded [it] to be given.
10ልኮም የዮሐንስን ራስ በወህኒ አስቆረጠው።
10And he sent and beheaded John in the prison;
11ራሱንም በወጭት አምጥተው ለብላቴናይቱ ሰጡአት፥ ወደ እናትዋም ወሰደችው።
11and his head was brought upon a dish, and was given to the damsel, and she carried [it] to her mother.
12ደቀ መዛሙርቱም ቀርበው በድኑን ወሰዱና ቀበሩት፥ መጥተውም ለኢየሱስ አወሩለት።
12And his disciples came and took the body and buried it, and came and brought word to Jesus.
13ኢየሱስም በሰማ ጊዜ ከዚያ ብቻውን ወደ ምድረ በዳ በታንኳ ፈቀቅ አለ፤ ሕዝቡም ሰምተው ከከተማዎቹ በእግር ተከተሉት።
13And Jesus, having heard it, went away thence by ship to a desert place apart. And the crowds having heard [of it] followed him on foot from the cities.
14ወጥቶም ብዙ ሕዝብ አየና አዘነላቸው ድውዮቻቸውንም ፈወሰ።
14And going out he saw a great crowd, and was moved with compassion about them, and healed their infirm.
15በመሸም ጊዜ ደቀ መዛሙርቱ ወደ እርሱ ቀርበው። ቦታው ምድረ በዳ ነው አሁንም ሰዓቱ አልፎአል፤ ወደ መንደሮች ሄደው ለራሳቸው ምግብ እንዲገዙ ሕዝቡን አሰናብት አሉት።
15But when even was come, his disciples came to him saying, The place is desert, and [much of] the [day] time already gone by; dismiss the crowds, that they may go into the villages and buy food for themselves.
16ኢየሱስም። እናንተ የሚበሉትን ስጡአቸው እንጂ ሊሄዱ አያስፈልግም አላቸው።
16But Jesus said to them, They have no need to go: give *ye* them to eat.
17እነርሱም። ከአምስት እንጀራና ከሁለት ዓሣ በቀር በዚህ የለንም አሉት።
17But they say to him, We have not here save five loaves and two fishes.
18እርሱም። እነዚያን ወደዚህ አምጡልኝ አላቸው።
18And he said, Bring them here to me.
19ሕዝቡም በሣር ላይ እንዲቀመጡ አዘዘ፥ አምስቱንም እንጀራና ሁለቱን ዓሣ ይዞ ወደ ሰማይ አሻቅቦ አየና ባረከ፥ እንጀራውንም ቆርሶ ለደቀ መዛሙርቱ ሰጠ፥ ደቀ መዛሙርቱም ለሕዝቡ።
19And having commanded the crowds to recline upon the grass, having taken the five loaves and the two fishes, he looked up to heaven, and blessed: and having broken the loaves, he gave [them] to the disciples, and the disciples [gave them] to the crowds.
20ሁሉም በልተው ጠገቡ፥ የተረፈውንም ቁርስራሽ አሥራ ሁለት መሶብ ሙሉ አነሡ።
20And all ate and were filled, and they took up what was over and above of fragments twelve hand-baskets full.
21ከሴቶችና ከልጆችም በቀር የበሉት አምስት ሺህ ወንዶች ያህሉ ነበር።
21But those that had eaten were about five thousand men, besides women and children.
22ወዲያውም ሕዝቡን ሲያሰናብት ሳለ፥ ደቀ መዛሙርቱ በታንኳይቱ ገብተው ወደ ማዶ እንዲቀድሙት ግድ አላቸው።
22And immediately he compelled the disciples to go on board ship, and to go on before him to the other side, until he should have dismissed the crowds.
23ሕዝቡንም አሰናብቶ ይጸልይ ዘንድ ብቻውን ወደ ተራራ ወጣ። በመሸም ጊዜ ብቻውን በዚያ ነበረ።
23And having dismissed the crowds, he went up into the mountain apart to pray. And when even was come, he was alone there,
24ታንኳይቱም አሁን በባሕር መካከል ሳለች፥ ነፋስ ከወደ ፊት ነበርና በማዕበል ትጨነቅ ነበር።
24but the ship was already in the middle of the sea tossed by the waves, for the wind was contrary.
25ከሌሊቱም በአራተኛው ክፍል ኢየሱስ በባሕር ላይ እየሄደ ወደ እነርሱ መጣ።
25But in the fourth watch of the night he went off to them, walking on the sea.
26ደቀ መዛሙርቱም በባሕር ላይ ሲሄድ ባዩት ጊዜ። ምትሐት ነው ብለው ታወኩ በፍርሃትም ጮኹ።
26And the disciples, seeing him walking on the sea, were troubled, saying, It is an apparition. And they cried out through fear.
27ወዲያውም ኢየሱስ ተናገራቸውና። አይዞአችሁ፥ እኔ ነኝ፤ አትፍሩ አላቸው።
27But Jesus immediately spoke to them, saying, Take courage; it is *I*: be not afraid.
28ጴጥሮስም መልሶ። ጌታ ሆይ፥ አንተስ ከሆንህ በውኃው ላይ ወደ አንተ እንድመጣ እዘዘኝ አለው።
28And Peter answering him said, Lord, if it be *thou*, command me to come to thee upon the waters.
29እርሱም። ና አለው። ጴጥሮስም ከታንኳይቱ ወርዶ ወደ ኢየሱስ ሊደርስ በውኃው ላይ ሄደ።
29And he said, Come. And Peter, having descended from the ship, walked upon the waters to go to Jesus.
30ነገር ግን የነፋሱን ኃይል አይቶ ፈራ፥ ሊሰጥምም በጀመረ ጊዜ። ጌታ ሆይ፥ አድነኝ ብሎ ጮኸ።
30But seeing the wind strong he was afraid; and beginning to sink he cried out, saying, Lord, save me.
31ወዲያውም ኢየሱስ እጁን ዘርግቶ ያዘውና። አንተ እምነት የጎደለህ፥ ስለምን ተጠራጠርህ? አለው።
31And immediately Jesus stretched out his hand and caught hold of him, and says to him, O thou of little faith, why didst thou doubt?
32ወደ ታንኳይቱም በወጡ ጊዜ ነፋሱ ተወ።
32And when they had gone up into the ship, the wind fell.
33በታንኳይቱም የነበሩት። በእውነት የእግዚአብሔር ልጅ ነህ ብለው ሰገዱለት።
33But those in the ship came and did homage to him, saying, Truly thou art God's Son.
34ተሻግረውም ወደ ጌንሴሬጥ ምድር መጡ።
34And having crossed over they came to the land of Gennesaret.
35የዚያ ቦታ ሰዎችም ባወቁት ጊዜ በዙርያው ወዳለ አገር ሁሉ ላኩ፥ ሕመምተኞችንም ሁሉ ወደ እርሱ አመጡ፤
35And when the men of that place recognised him, they sent to that whole country around, and they brought to him all that were ill,
36የልብሱንም ጫፍ ብቻ ሊዳስሱ ይለምኑት ነበር፤ የዳሰሱትም ሁሉ ዳኑ።
36and besought him that they might only touch the hem of his garment; and as many as touched were made thoroughly well.