Amharic: New Testament

Darby's Translation

Matthew

27

1ሲነጋም የካህናት አለቆችና የሕዝቡ ሽማግሎች ሁሉ ሊገድሉት በኢየሱስ ላይ ተማከሩ፤
1And when it was morning all the chief priests and the elders of the people took counsel against Jesus so that they might put him to death.
2አስረውም ወሰዱት፥ ለገዢው ለጴንጤናዊው ጲላጦስም አሳልፈው ሰጡት።
2And having bound him they led him away, and delivered him up to Pontius Pilate, the governor.
3በዚያን ጊዜ አሳልፎ የሰጠው ይሁዳ እንደ ተፈረደበት አይቶ ተጸጸተ፥ ሠላሳውንም ብር ለካህናት አለቆችና ለሽማግሎች መልሶ።
3Then Judas, who delivered him up, seeing that he had been condemned, filled with remorse, returned the thirty pieces of silver to the chief priests and the elders,
4ንጹሕ ደም አሳልፌ በመስጠቴ በድያለሁ አለ። እነርሱ ግን። እኛስ ምን አግዶን? አንተው ተጠንቀቅ አሉ።
4saying, I have sinned [in] having delivered up guiltless blood. But they said, What is that to us? see *thou* [to that].
5ብሩንም በቤተ መቅደስ ጥሎ ሄደና ታንቆ ሞተ።
5And having cast down the pieces of silver in the temple, he left the place, and went away and hanged himself.
6የካህናት አለቆችም ብሩን አንሥተው። የደም ዋጋ ነውና ወደ መባ ልንጨምረው አልተፈቀደም አሉ።
6And the chief priests took the pieces of silver and said, It is not lawful to cast them into the Corban, since it is [the] price of blood.
7ተማክረውም የሸክላ ሠሪውን መሬት ለእንግዶች መቃብር ገዙበት።
7And having taken counsel, they bought with them the field of the potter for a burying-ground for strangers.
8ስለዚህ ያ መሬት እስከ ዛሬ ድረስ የደም መሬት ተባለ።
8Wherefore that field has been called Blood-field unto this day.
9በዚያን ጊዜ በነቢዩ በኤርምያስ የተባለው። ከእስራኤል ልጆችም አንዳንዶቹ የገመቱትን፥ የተገመተውን ዋጋ ሠላሳ ብር ያዙ፥
9Then was fulfilled that which was spoken through Jeremias the prophet, saying, And I took the thirty pieces of silver, the price of him that was set a price on, whom [they who were] of the sons of Israel had set a price on,
10ጌታም እንዳዘዘኝ ስለ ሸክላ ሠሪ መሬት ሰጡት። የሚል ተፈጸመ።
10and they gave them for the field of the potter, according as [the] Lord commanded me.
11ኢየሱስም በገዢው ፊት ቆመ፤ ገዢውም። የአይሁድ ንጉሥ አንተ ነህን? ብሎ ጠየቀው፤ ኢየሱስም። አንተ አልህ አለው።
11But Jesus stood before the governor. And the governor questioned him, saying, Art *thou* the King of the Jews? And Jesus said to him, Thou sayest.
12የካህናት አለቆችም ሽማግሎችም ሲከሱት ምንም አልመለሰም።
12And when he was accused of the chief priests and the elders, he answered nothing.
13በዚያን ጊዜ ጲላጦስ። ስንት ያህል እንዲመሰክሩብህ አትሰማምን? አለው።
13Then says Pilate to him, Hearest thou not how many things they witness against thee?
14ገዢውም እጅግ እስኪደነቅ ድረስ አንዲት ቃል ስንኳ አልመለሰለትም።
14And he answered him not so much as one word, so that the governor wondered exceedingly.
15በዚያም በዓል ሕዝቡ የወደዱትን አንድ እስረኛ ሊፈታላቸው ለገዢው ልማድ ነበረው።
15Now at [the] feast the governor was accustomed to release one prisoner to the crowd, whom they would.
16በዚያን ጊዜም በርባን የሚባል በጣም የታወቀ እስረኛ ነበራቸው።
16And they had then a notable prisoner, named Barabbas.
17እንግዲህ እነርሱ ተሰብስበው ሳሉ ጲላጦስ። በርባንን ወይስ ክርስቶስ የተባለውን ኢየሱስን ማንኛውን ልፈታላችሁ ትወዳላችሁ? አላቸው፤
17They therefore being gathered together, Pilate said to them, Whom will ye that I release to you, Barabbas, or Jesus who is called Christ?
18በቅንዓት አሳልፈው እንደ ሰጡት ያውቅ ነበርና።
18For he knew that they had delivered him up through envy.
19እርሱም በፍርድ ወንበር ተቀምጦ ሳለ ሚስቱ። ስለ እርሱ ዛሬ በሕልም እጅግ መከራ ተቀብያለሁና በዚያ ጻድቅ ሰው ምንም አታድርግ ብላ ላከችበት።
19But, as he was sitting on the judgment-seat, his wife sent to him, saying, Have thou nothing to do with that righteous [man]; for I have suffered to-day many things in a dream because of him.
20የካህናት አለቆችና ሽማግሎች ግን በርባንን እንዲለምኑ ኢየሱስን ግን እንዲያጠፉ ሕዝቡን አባበሉ።
20But the chief priests and the elders persuaded the crowds that they should beg for Barabbas, and destroy Jesus.
21ገዢውም መልሶ። ከሁለቱ ማንኛውን ልፈታላችሁ ትወዳላችሁ? አላቸው፤ እነርሱም። በርባንን አሉ።
21And the governor answering said to them, Which of the two will ye that I release unto you? And they said, Barabbas.
22ጲላጦስ። ክርስቶስ የተባለውን ኢየሱስን እንግዲህ ምን ላድርገው? አላቸው፤ ሁሉም። ይሰቀል አሉ።
22Pilate says to them, What then shall I do with Jesus, who is called Christ? They all say, Let him be crucified.
23ገዢውም። ምን ነው? ያደረገው ክፋት ምንድር ነው? አለ፤ እነርሱ ግን። ይሰቀል እያሉ ጩኸት አበዙ።
23And the governor said, What evil then has he done? But they cried more than ever, saying, Let him be crucified.
24ጲላጦስም ሁከት እንዲጀመር እንጂ አንዳች እንዳይረባ ባየ ጊዜ፥ ውኃ አንሥቶ። እኔ ከዚህ ጻድቅ ሰው ደም ንጹሕ ነኝ፤ እናንተ ተጠንቀቁ ሲል በሕዝቡ ፊት እጁን ታጠበ።
24And Pilate, seeing that it availed nothing, but that rather a tumult was arising, having taken water, washed his hands before the crowd, saying, I am guiltless of the blood of this righteous one: see *ye* [to it].
25ሕዝቡም ሁሉ መልሰው። ደሙ በእኛና በልጆቻችን ላይ ይሁን አሉ።
25And all the people answering said, His blood [be] on us and on our children.
26በዚያን ጊዜ በርባንን ፈታላቸው፥ ኢየሱስን ግን ገርፎ ሊሰቀል አሳልፎ ሰጠ።
26Then he released to them Barabbas; but Jesus, having scourged [him], he delivered up that he might be crucified.
27በዚያን ጊዜ የገዢው ወታደሮች ኢየሱስን ወደ ገዢው ግቢ ውስጥ ወሰዱት ጭፍራውንም ሁሉ ወደ እርሱ አከማቹ።
27Then the soldiers of the governor, having taken Jesus with [them] to the praetorium, gathered against him the whole band,
28ልብሱንም ገፈው ቀይ ልብስ አለበሱት፥
28and having taken off his garment, put on him a scarlet cloak;
29ከእሾህም አክሊል ጎንጉነው በራሱ ላይ፥ በቀኝ እጁም መቃ አኖሩ፥ በፊቱም ተንበርክከው። የአይሁድ ንጉሥ ሆይ፥ ሰላም ለአንተ ይሁን እያሉ ዘበቱበት፤
29and having woven a crown out of thorns, they put it on his head, and a reed in his right hand; and, bowing the knee before him, they mocked him, saying, Hail, King of the Jews!
30ተፉበትም መቃውንም ይዘው ራሱን መቱት።
30And having spit upon him, they took the reed and beat [him] on his head.
31ከዘበቱበትም በኋላ ቀዩን ልብስ ገፈፉት፥ ልብሱንም አለበሱት ሊሰቅሉትም ወሰዱት።
31And when they had mocked him, they took the cloak off him, and put his own clothes on him, and led him away to crucify.
32ሲወጡም ስምዖን የተባለው የቀሬናን ሰው አገኙ፤ እርሱንም መስቀሉን ይሸከም ዘንድ አስገደዱት።
32And as they went forth they found a man of Cyrene, Simon by name; him they compelled to go [with them] that he might bear his cross.
33ትርጓሜው የራስ ቅል ስፍራ ወደሚሆን ጎልጎታ ወደሚባለው ስፍራ በደረሱ ጊዜም፥
33And having come to a place called Golgotha, which means Place of a skull,
34በሐሞት የተደባለቀ የወይን ጠጅ ሊጠጣ አቀረቡለት፤ ቀምሶም ሊጠጣው አልወደደም።
34they gave to him to drink vinegar mingled with gall; and having tasted [it], he would not drink.
35ከሰቀሉትም በኋላ ልብሱን ዕጣ ጥለው ተካፈሉ፥
35And having crucified him, they parted his clothes amongst [themselves], casting lots.
36በዚያም ተቀምጠው ይጠብቁት ነበር።
36And sitting down, they kept guard over him there.
37ይህ ኢየሱስ የአይሁድ ንጉሥ ነው የሚል የክሱን ጽሕፈት ከራሱ በላይ አኖሩ።
37And they set up over his head his accusation written: This is Jesus, the King of the Jews.
38በዚያን ጊዜ ሁለት ወንበዶች አንዱ በቀኝ አንዱም በግራ ከእርሱ ጋር ተሰቀሉ።
38Then are crucified with him two robbers, one on the right hand and one on the left.
39የሚያልፉትም ራሳቸውን እየነቀነቁ ይሰድቡት ነበርና።
39But the passers-by reviled him, shaking their heads
40ቤተ መቅደስን የምታፈርስ በሦስት ቀንም የምትሠራው፥ ራስህን አድን፤ የእግዚአብሔር ልጅስ ከሆንህ ከመስቀል ውረድ አሉት።
40and saying, Thou that destroyest the temple and buildest it in three days, save thyself. If thou art Son of God, descend from the cross.
41እንዲሁም ደግሞ የካህናት አለቆች ከጻፎችና ከሽማግሎች ጋር እየዘበቱበት እንዲህ አሉ።
41[And] in like manner the chief priests also, mocking, with the scribes and elders, said,
42ሌሎችን አዳነ፥ ራሱን ሊያድን አይችልም፤ የእስራኤል ንጉሥ ከሆነ፥ አሁን ከመስቀል ይውረድ እኛም እናምንበታለን።
42He saved others, himself he cannot save. He is King of Israel: let him descend now from the cross, and we will believe on him.
43በእግዚአብሔር ታምኖአል፤ የእግዚአብሔር ልጅ ነኝ ብሎአልና ከወደደውስ አሁን ያድነው።
43He trusted upon God; let him save him now if he will [have] him. For he said, I am Son of God.
44ከእርሱ ጋር የተሰቀሉት ወንበዶች ደግሞ ያንኑ እያሉ ይነቅፉት ነበር።
44And the robbers also who had been crucified with him cast the same reproaches on him.
45ከስድስት ሰዓትም ጀምሮ እስከ ዘጠኝ ሰዓት ድረስ በምድር ሁሉ ላይ ጨለማ ሆነ።
45Now from [the] sixth hour there was darkness over the whole land until [the] ninth hour;
46በዘጠኝ ሰዓትም ኢየሱስ። ኤሎሄ ኤሎሄ ላማ ሰበቅታኒ? ብሎ በታላቅ ድምፅ ጮኸ። ይህም። አምላኬ አምላኬ፥ ስለ ምን ተውኸኝ? ማለት ነው።
46but about the ninth hour Jesus cried out with a loud voice, saying, Eli, Eli, lama sabachthani? that is, My God, my God, why hast thou forsaken me?
47በዚያም ከቆሙት ሰዎች ሰምተው። ይህስ ኤልያስን ይጠራል አሉ።
47And some of those who stood there, when they heard [it], said, This [man] calls for Elias.
48ወዲያውም ከእነርሱ አንዱ ሮጠ፤ ሰፍነግም ይዞ ሆምጣጤ ሞላበት፥ በመቃም አድርጎ አጠጣው።
48And immediately one of them running and getting a sponge, having filled [it] with vinegar and fixed [it] on a reed, gave him to drink.
49ሌሎቹ ግን። ተው፥ ኤልያስ መጥቶ ያድነው እንደ ሆነ እንይ አሉ።
49But the rest said, Let be; let us see if Elias comes to save him.
50ኢየሱስም ሁለተኛ በታላቅ ድምፅ ጮኾ ነፍሱን ተወ።
50And Jesus, having again cried with a loud voice, gave up the ghost.
51እነሆም፥ የቤተ መቅደስ መጋረጃ ከላይ እስከ ታች ከሁለት ተቀደደ፥ ምድርም ተናወጠች፥ ዓለቶችም ተሰነጠቁ፤
51And lo, the veil of the temple was rent in two from the top to the bottom, and the earth was shaken, and the rocks were rent,
52መቃብሮችም ተከፈቱ፥ ተኝተው ከነበሩትም ከቅዱሳን ብዙ ሥጋዎች ተነሡ፤
52and the tombs were opened; and many bodies of the saints fallen asleep arose,
53ከትንሣኤውም በኋላ ከመቃብሮች ወጥተው ወደ ቅድስት ከተማ ገቡና ለብዙዎች ታዩ።
53and going out of the tombs after his arising, entered into the holy city and appeared unto many.
54የመቶ አለቃም ከእርሱም ጋር ኢየሱስን የሚጠብቁ መናወጡንና የሆነውን ነገር አይተው። ይህ በእውነት የእግዚአብሔር ልጅ ነበረ ብለው እጅግ ፈሩ።
54But the centurion, and they who were with him on guard over Jesus, seeing the earthquake and the things that took place, feared greatly, saying, Truly this [man] was Son of God.
55ኢየሱስን እያገለገሉ ከገሊላ የተከተሉት ብዙ ሴቶች በሩቅ ሆነው ሲመለከቱ በዚያ ነበሩ፤
55And there were there many women beholding from afar off, who had followed Jesus from Galilee ministering to him,
56ከእነርሱም መግደላዊት ማርያምና የያዕቆብና የዮሳ እናት ማርያም የዘብዴዎስም የልጆቹ እናት ነበሩ።
56among whom was Mary of Magdala, and Mary the mother of James and Joses, and the mother of the sons of Zebedee.
57በመሸም ጊዜ ዮሴፍ የተባለው ባለ ጠጋ ሰው ከአርማትያስ መጣ፥ እርሱም ደግሞ የኢየሱስ ደቀ መዝሙር ነበረ፤
57Now when even was come there came a rich man of Arimathaea, his name Joseph, who also himself was a disciple to Jesus.
58ይኸውም ወደ ጲላጦስ ቀርቦ የኢየሱስን ሥጋ ለመነው።
58*He*, going to Pilate, begged the body of Jesus. Then Pilate commanded the body to be given up.
59ጲላጦስም እንዲሰጡት አዘዘ። ዮሴፍም ሥጋውን ይዞ በንጹሕ በፍታ ከፈነው፥
59And Joseph having got the body, wrapped it in a clean linen cloth,
60ከዓለት በወቀረው በአዲሱ መቃብርም አኖረው፥ በመቃብሩም ደጃፍ ታላቅ ድንጋይ አንከባሎ ሄደ።
60and laid it in his new tomb which he had hewn in the rock; and having rolled a great stone to the door of the tomb, went away.
61መግደላዊት ማርያምም ሁለተኛይቱም ማርያም በመቃብሩ አንጻር ተቀምጠው በዚያ ነበሩ።
61But Mary of Magdala was there, and the other Mary, sitting opposite the sepulchre.
62በማግሥቱም ከመዘጋጀት በኋላ በሚሆነው ቀን፥ የካህናት አለቆችና ፈሪሳውያን ወደ ጲላጦስ ተሰበሰቡና።
62Now on the morrow, which is after the preparation, the chief priests and the Pharisees came together to Pilate,
63ጌታ ሆይ፥ ያ አሳች በሕይወቱ ገና ሳለ። ከሦስት ቀን በኋላ እነሣለሁ እንዳለ ትዝ አለን።
63saying, Sir, we have called to mind that that deceiver said when he was still alive, After three days I arise.
64እንግዲህ ደቀ መዛሙርቱ መጥተው በሌሊት እንዳይሰርቁት ለሕዝቡም። ከሙታን ተነሣ እንዳይሉ፥ የኋለኛይቱ ስሕተት ከፊተኛይቱ ይልቅ የከፋች ትሆናለችና መቃብሩ እስከ ሦስተኛ ቀን ድረስ እንዲጠበቅ እዘዝ አሉት።
64Command therefore that the sepulchre be secured until the third day, lest his disciples should come and steal him away, and say to the people, He is risen from the dead; and the last error shall be worse than the first.
65ጲላጦስም። ጠባቆች አሉአችሁ፤ ሄዳችሁ እንዳወቃችሁ አስጠብቁ አላቸው።
65And Pilate said to them, Ye have a watch: go, secure it as well as ye know how.
66እነርሱም ሄደው ከጠባቆች ጋር ድንጋዩን አትመው መቃብሩን አስጠበቁ።
66And they went and secured the sepulchre, having sealed the stone, with the watch [besides].