Amharic: New Testament

Darby's Translation

Revelation

20

1የጥልቁንም መክፈቻና ታላቁን ሰንሰለት በእጁ የያዘ መልአክ ከሰማይ ሲወርድ አየሁ።
1And I saw an angel descending from the heaven, having the key of the abyss, and a great chain in his hand.
2የቀደመውንም እባብ ዘንዶውን እርሱም ዲያብሎስና ሰይጣን የተባለውን ያዘው፥
2And he laid hold of the dragon, the ancient serpent who is [the] devil and Satan, and bound him a thousand years,
3ሺህ ዓመትም አሰረው፥ ወደ ጥልቅም ጣለው አሕዛብንም ወደ ፊት እንዳያስት ሺህ ዓመት እስኪፈጸም ድረስ በእርሱ ላይ ዘግቶ ማኅተም አደረገበት፤ ከዚያም በኋላ ለጥቂት ጊዜ ይፈታ ዘንድ ይገባዋል።
3and cast him into the abyss, and shut [it] and sealed [it] over him, that he should not any more deceive the nations until the thousand years were completed; after these things he must be loosed for a little time.
4ዙፋኖችንም አየሁ፥ በእነርሱም ላይ ለተቀመጡት ዳኝነት ተሰጣቸው፤ ስለ ኢየሱስም ምስክርና ስለ እግዚአብሔር ቃል ራሶቻቸው የተቈረጡባቸውን ሰዎች ነፍሳት፥ ለአውሬውና ለምስሉም ያልሰገዱትን ምልክቱንም በግምባራቸው በእጆቻቸውም ላይ ያልተቀበሉትን አየሁ፤ ከክርስቶስም ጋር ሺህ ዓመት ኖሩና ነገሡ።
4And I saw thrones; and they sat upon them, and judgment was given to them; and the souls of those beheaded on account of the testimony of Jesus, and on account of the word of God; and those who had not done homage to the beast nor to his image, and had not received the mark on their forehead and hand; and they lived and reigned with the Christ a thousand years:
5የቀሩቱ ሙታን ግን ይህ ሺህ ዓመት እስኪፈጸም ድረስ በሕይወት አልኖሩም። ይህ የፊተኛው ትንሣኤ ነው።
5the rest of the dead did not live till the thousand years had been completed. This [is] the first resurrection.
6በፊተኛው ትንሣኤ ዕድል ያለው ብፁዕና ቅዱስ ነው፤ ሁለተኛው ሞት በእነርሱ ላይ ሥልጣን የለውም፥ ዳሩ ግን የእግዚአብሔርና የክርስቶስ ካህናት ይሆናሉ ከእርሱም ጋር ይህን ሺህ ዓመት ይነግሣሉ።
6Blessed and holy he who has part in the first resurrection: over these the second death has no power; but they shall be priests of God and of the Christ, and shall reign with him a thousand years.
7ሺሁም ዓመት ሲፈጸም ሰይጣን ከእስራቱ ይፈታል፥
7And when the thousand years have been completed, Satan shall be loosed from his prison,
8በአራቱም በምድር ማዕዘን ያሉትን አሕዛብ፥ ጎግንና ማጎግን፥ እንዲያስታቸው ለሰልፍም እንዲያስከትታቸው ይወጣል፤ ቍጥራቸውም እንደ ባሕር አሸዋ የሚያህል ነው።
8and shall go out to deceive the nations which [are] in the four corners of the earth, Gog and Magog, to gather them together to the war, whose number [is] as the sand of the sea.
9ወደ ምድርም ስፋት ወጡ የቅዱሳንንም ሰፈርና የተወደደችውን ከተማ ከበቡ፤ እሳትም ከሰማይ ከእግዚአብሔር ዘንድ ወርዳ በላቻቸው።
9And they went up on the breadth of the earth, and surrounded the camp of the saints and the beloved city: and fire came down [from God] out of the heaven and devoured them.
10ያሳታቸውም ዲያብሎስ አውሬውና ሐሰተኛው ነቢይ ወዳሉበት ወደ እሳቱና ወደ ዲኑ ባሕር ተጣለ፥ ለዘላለምም እስከ ዘላለም ቀንና ሌሊት ይሣቀያሉ።
10And the devil who deceived them was cast into the lake of fire and brimstone, where [are] both the beast and the false prophet; and they shall be tormented day and night for the ages of ages.
11ታላቅና ነጭ ዙፋንን በእርሱም ላይ የተቀመጠውን አየሁ፥ ምድርና ሰማይም ከፊቱ ሸሹ ስፍራም አልተገኘላቸውም።
11And I saw a great white throne, and him that sat on it, from whose face the earth and the heaven fled, and place was not found for them.
12ሙታንንም ታናናሾችንና ታላላቆችን በዙፋኑ ፊት ቆመው አየሁ፥ መጻሕፍትም ተከፈቱ፤ ሌላ መጽሐፍም ተከፈተ እርሱም የሕይወት መጽሐፍ ነው፤ ሙታንም በመጻሕፍት ተጽፎ እንደ ነበረ እንደ ሥራቸው መጠን ተከፈሉ።
12And I saw the dead, great and small, standing before the throne, and books were opened; and another book was opened, which is [that] of life. And the dead were judged out of the things written in the books according to their works.
13ባሕርም በእርሱ ውስጥ ያሉትን ሙታን ሰጠ፥ ሞትና ሲኦልም በእነርሱ ዘንድ ያሉትን ሙታን ሰጡ፥ እያንዳንዱም እንደ ሥራው መጠን ተከፈለ።
13And the sea gave up the dead which [were] in it, and death and hades gave up the dead which [were] in them; and they were judged each according to their works:
14ሞትና ሲኦልም በእሳት ባሕር ውስጥ ተጣሉ። ይህም የእሳት ባሕር ሁለተኛው ሞት ነው።
14and death and hades were cast into the lake of fire. This is the second death, [even] the lake of fire.
15በሕይወትም መጽሐፍ ተጽፎ ያልተገኘው ማንኛውም በእሳት ባሕር ውስጥ ተጣለ።
15And if any one was not found written in the book of life, he was cast into the lake of fire.