1ወንድሞች ሆይ፥ የሰበክሁላችሁን ደግሞም የተቀበላችሁትን በእርሱም ደግሞ የቆማችሁበትን በእርሱም ደግሞ የምትድኑበትን ወንጌል አሳስባችኋለሁ፤
1Now I declare to you, brothers, the Good News which I preached to you, which also you received, in which you also stand,
2በከንቱ ካላመናችሁ በቀር፥ ብታስቡት፥ በምን ቃል እንደ ሰበክሁላችሁ አሳስባችኋለሁ።
2by which also you are saved, if you hold firmly the word which I preached to you—unless you believed in vain.
3እኔ ደግሞ የተቀበልሁትን ከሁሉ በፊት አሳልፌ ሰጠኋችሁ እንዲህ ብዬ። መጽሐፍ እንደሚል ክርስቶስ ስለ ኃጢአታችን ሞተ፥ ተቀበረም፥
3For I delivered to you first of all that which I also received: that Christ died for our sins according to the Scriptures,
4መጽሐፍም እንደሚል በሦስተኛው ቀን ተነሣ፥
4that he was buried, that he was raised on the third day according to the Scriptures,
5ለኬፋም ታየ በኋላም ለአሥራ ሁለቱ፤
5and that he appeared to Cephas, then to the twelve.
6ከዚያም በኋላ ከአምስት መቶ ለሚበዙ ወንድሞች በአንድ ጊዜ ታየ፤ ከእነርሱም የሚበዙቱ እስከ አሁን አሉ አንዳንዶች ግን አንቀላፍተዋል፤
6Then he appeared to over five hundred brothers at once, most of whom remain until now, but some have also fallen asleep.
7ከዚያም በኋላ ለያዕቆብ ኋላም ለሐዋርያት ሁሉ ታየ፤
7Then he appeared to James, then to all the apostles,
8ከሁሉም በኋላ እንደ ጭንጋፍ ለምሆን ለእኔ ደግሞ ታየኝ።
8and last of all, as to the child born at the wrong time, he appeared to me also.
9እኔ ከሐዋርያት ሁሉ የማንስ ነኝና፥ የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ስላሳደድሁ ሐዋርያ ተብዬ ልጠራ የማይገባኝ፤
9For I am the least of the apostles, who is not worthy to be called an apostle, because I persecuted the assembly of God.
10ነገር ግን በእግዚአብሔር ጸጋ የሆንሁ እኔ ነኝ፤ ለእኔም የተሰጠኝ ጸጋው ከንቱ አልነበረም ከሁላቸው ይልቅ ግን ደከምሁ፥ ዳሩ ግን ከእኔ ጋር ያለው የእግዚአብሔር ጸጋ ነው እንጂ እኔ አይደለሁም።
10But by the grace of God I am what I am. His grace which was bestowed on me was not futile, but I worked more than all of them; yet not I, but the grace of God which was with me.
11እንግዲህስ እኔ ብሆን እነርሱም ቢሆኑ እንዲሁ እንሰብካለን እንዲሁም አመናችሁ።
11Whether then it is I or they, so we preach, and so you believed.
12ክርስቶስ ከሙታን እንደ ተነሣ የሚሰበክ ከሆነ ግን ከእናንተ አንዳንዶቹ። ትንሣኤ ሙታን የለም እንዴት ይላሉ?
12Now if Christ is preached, that he has been raised from the dead, how do some among you say that there is no resurrection of the dead?
13ትንሣኤ ሙታንስ ከሌለ ክርስቶስ አልተነሣማ፤
13But if there is no resurrection of the dead, neither has Christ been raised.
14ክርስቶስም ካልተነሣ እንግዲያስ ስብከታችን ከንቱ ነው እምነታችሁም ደግሞ ከንቱ ናት፤
14If Christ has not been raised, then our preaching is in vain, and your faith also is in vain.
15ደግሞም። ክርስቶስን አስነሥቶታል ብለን በእግዚአብሔር ላይ ስለ መሰከርን ሐሰተኞች የእግዚአብሔር ምስክሮች ሆነን ተገኝተናል፤ ሙታን ግን የማይነሡ ከሆነ እርሱን አላስነሣውም።
15Yes, we are found false witnesses of God, because we testified about God that he raised up Christ, whom he didn’t raise up, if it is so that the dead are not raised.
16ሙታን የማይነሡ ከሆነ ክርስቶስ አልተነሣማ፤
16For if the dead aren’t raised, neither has Christ been raised.
17ክርስቶስም ካልተነሣ እምነታችሁ ከንቱ ናት፤ እስከ አሁን ድረስ በኃጢአታችሁ አላችሁ።
17If Christ has not been raised, your faith is vain; you are still in your sins.
18እንግዲያስ በክርስቶስ ያንቀላፉት ደግሞ ጠፍተዋላ።
18Then they also who are fallen asleep in Christ have perished.
19በዚች ሕይወት ብቻ ክርስቶስን ተስፋ ያደረግን ከሆነ፥ ከሰው ሁሉ ይልቅ ምስኪኖች ነን።
19If we have only hoped in Christ in this life, we are of all men most pitiable.
20አሁን ግን ክርስቶስ ላንቀላፉት በኩራት ሆኖ ከሙታን ተነሥቶአል።
20But now Christ has been raised from the dead. He became the first fruits of those who are asleep.
21ሞት በሰው በኩል ስለ መጣ ትንሣኤ ሙታን በሰው በኩል ሆኖአልና።
21For since death came by man, the resurrection of the dead also came by man.
22ሁሉ በአዳም እንደሚሞቱ እንዲሁ ሁሉ በክርስቶስ ደግሞ ሕያዋን ይሆናሉና።
22For as in Adam all die, so also in Christ all will be made alive.
23ነገር ግን እያንዳንዱ በራሱ ተራ ይሆናል፤ ክርስቶስ እንደ በኩራት ነው፥ በኋላም በመምጣቱ ለክርስቶስ የሆኑት ናቸው፤
23But each in his own order: Christ the first fruits, then those who are Christ’s, at his coming.
24በኋላም፥ መንግሥቱን ለእግዚአብሔር ለአባቱ አሳልፎ በሰጠ ጊዜ አለቅነትንም ሁሉና ሥልጣንን ሁሉ ኃይልንም በሻረ ጊዜ፥ ፍጻሜ ይሆናል።
24Then the end comes, when he will deliver up the Kingdom to God, even the Father; when he will have abolished all rule and all authority and power.
25ጠላቶቹን ሁሉ ከእግሩ በታች እስኪያደርግ ድረስ ሊነግሥ ይገባዋልና።
25For he must reign until he has put all his enemies under his feet.
26የኋለኛው ጠላት የሚሻረው ሞት ነው፤
26The last enemy that will be abolished is death.
27ሁሉን ከእግሩ በታች አስገዝቶአልና። ነገር ግን። ሁሉ ተገዝቶአል ሲል፥ ሁሉን ካስገዛለት በቀር መሆኑ ግልጥ ነው።
27For, “He put all things in subjection under his feet.” Psalm 8:6 But when he says, “All things are put in subjection,” it is evident that he is excepted who subjected all things to him.
28ሁሉ ከተገዛለት በኋላ ግን እግዚአብሔር ሁሉ በሁሉ ይሆን ዘንድ በዚያን ጊዜ ልጁ ራሱ ደግሞ ሁሉን ላስገዛለት ይገዛል።
28When all things have been subjected to him, then the Son will also himself be subjected to him who subjected all things to him, that God may be all in all.
29እንዲያማ ካልሆነ፥ ስለ ሙታን የሚጠመቁ ምን ያደርጋሉ? ሙታንስ ከቶ የማይነሡ ከሆነ፥ ስለ እነርሱ የሚጠመቁ ስለ ምንድር ነው?
29Or else what will they do who are baptized for the dead? If the dead aren’t raised at all, why then are they baptized for the dead?
30እኛስ ዘወትር በሚያስፈራ ኑሮ የምንኖር ስለ ምንድር ነው?
30Why do we also stand in jeopardy every hour?
31በጌታችን በክርስቶስ ኢየሱስ ባለኝ በእናንተ ትምክህት እየማልሁ፥ ወንድሞች ሆይ፥ ዕለት ዕለት እሞታለሁ።
31I affirm, by the boasting in you which I have in Christ Jesus our Lord, I die daily.
32እንደ ሰው በኤፌሶን ከአውሬ ጋር ከታገልሁ፥ ሙታንስ የማይነሡ ከሆነ፥ ምን ይጠቅመኛል? ነገ እንሞታለንና እንብላና እንጠጣ።
32If I fought with animals at Ephesus for human purposes, what does it profit me? If the dead are not raised, then “let us eat and drink, for tomorrow we die.” Isaiah 22:13
33አትሳቱ፤ ክፉ ባልንጀርነት መልካሙን አመል ያጠፋል።
33Don’t be deceived! “Evil companionships corrupt good morals.”
34በጽድቅ ንቁ ኃጢአትንም አትሥሩ፤ እግዚአብሔርን የማያውቁ አሉና፤ አሳፍራችሁ ዘንድ ይህን እላለሁ።
34Wake up righteously, and don’t sin, for some have no knowledge of God. I say this to your shame.
35ነገር ግን ሰው። ሙታን እንዴት ይነሣሉ? በምንስ ዓይነት አካል ይመጣሉ? የሚል ይኖር ይሆናል።
35But someone will say, “How are the dead raised?” and, “With what kind of body do they come?”
36አንተ ሞኝ፥ አንተ የምትዘራው ካልሞተ ሕያው አይሆንም፤
36You foolish one, that which you yourself sow is not made alive unless it dies.
37የምትዘራውም፥ ስንዴ ቢሆን ከሌላም ዓይነት የአንዱ ቢሆን፥ ቅንጣት ብቻ ነው እንጂ የምትዘራው የሚሆነውን አካል አይደለም፤
37That which you sow, you don’t sow the body that will be, but a bare grain, maybe of wheat, or of some other kind.
38እግዚአብሔር ግን እንደ ወደደ አካልን ይሰጠዋል ከዘሮችም ለእያንዳንዱ የገዛ አካሉን ይሰጠዋል።
38But God gives it a body even as it pleased him, and to each seed a body of its own.
39ሥጋ ሁሉ አንድ አይደለም፥ የሰው ሥጋ ግን አንድ ነው፥ የእንስሳም ሥጋ ሌላ ነው፥ የወፎችም ሥጋ ሌላ ነው፥ የዓሣም ሥጋ ሌላ ነው።
39All flesh is not the same flesh, but there is one flesh of men, another flesh of animals, another of fish, and another of birds.
40ደግሞ ሰማያዊ አካል አለ፥ ምድራዊም አካል አለ፤ ነገር ግን የሰማያዊ አካል ክብር ልዩ ነው፥ የምድራዊም አካል ክብር ልዩ ነው።
40There are also celestial bodies, and terrestrial bodies; but the glory of the celestial differs from that of the terrestrial.
41የፀሐይ ክብር አንድ ነው የጨረቃም ክብር ሌላ ነው የከዋክብትም ክብር ሌላ ነው፤ በክብር አንዱ ኮከብ ከሌላው ኮከብ ይለያልና።
41There is one glory of the sun, another glory of the moon, and another glory of the stars; for one star differs from another star in glory.
42የሙታን ትንሣኤ ደግሞ እንዲሁ ነው። በመበስበስ ይዘራል፥ ባለመበስበስ ይነሣል፤
42So also is the resurrection of the dead. It is sown in corruption; it is raised in incorruption.
43በውርደት ይዘራል፥ በክብር ይነሣል፤ በድካም ይዘራል፥ በኃይል ይነሣል፤
43It is sown in dishonor; it is raised in glory. It is sown in weakness; it is raised in power.
44ፍጥረታዊ አካል ይዘራል፥ መንፈሳዊ አካል ይነሣል። ፍጥረታዊ አካል ካለ መንፈሳዊ አካል ደግሞ አለ።
44It is sown a natural body; it is raised a spiritual body. There is a natural body and there is also a spiritual body.
45እንዲሁ ደግሞ። ፊተኛው ሰው አዳም ሕያው ነፍስ ሆነ ተብሎ ተጽፎአል፤ ኋለኛው አዳም ሕይወትን የሚሰጥ መንፈስ ሆነ።
45So also it is written, “The first man, Adam, became a living soul.” Genesis 2:7 The last Adam became a life-giving spirit.
46ነገር ግን አስቀድሞ ፍጥረታዊው ቀጥሎም መንፈሳዊው ነው እንጂ መንፈሳዊው መጀመሪያ አይደለም።
46However that which is spiritual isn’t first, but that which is natural, then that which is spiritual.
47የፊተኛው ሰው ከመሬት መሬታዊ ነው፤ ሁለተኛው ሰው ከሰማይ ነው።
47The first man is of the earth, made of dust. The second man is the Lord from heaven.
48መሬታዊው እንደ ሆነ መሬታውያን የሆኑት ደግሞ እንዲሁ ናቸው፥ ሰማያዊው እንደ ሆነ ሰማያውያን የሆኑት ደግሞ እንዲሁ ናቸው።
48As is the one made of dust, such are those who are also made of dust; and as is the heavenly, such are they also that are heavenly.
49የዚያንም የመሬታዊውን መልክ እንደ ለበስን የሰማያዊውን መልክ ደግሞ እንለብሳለን።
49As we have borne the image of those made of dust, let’s NU, TR read “we will” instead of “let’s” also bear the image of the heavenly.
50ነገር ግን፥ ወንድሞች ሆይ፥ ይህን እላለሁ። ሥጋና ደም የእግዚአብሔርን መንግሥት ሊወርሱ አይችሉም፥ የሚበሰብሰውም የማይበሰብሰውን አይወርስም።
50Now I say this, brothers, The word for “brothers” here and where context allows may also be correctly translated “brothers and sisters” or “siblings.” that flesh and blood can’t inherit the Kingdom of God; neither does corruption inherit incorruption.
51እነሆ፥ አንድ ምሥጢር እነግራችኋለሁ፤ ሁላችን አናንቀላፋም ነገር ግን የኋለኛው መለከት ሲነፋ ሁላችን በድንገት በቅጽበት ዓይን እንለወጣለን፤ መለከት ይነፋልና ሙታንም የማይበሰብሱ ሆነው ይነሣሉ እኛም እንለወጣለን።
51Behold, I tell you a mystery. We will not all sleep, but we will all be changed,
53ይህ የሚበሰብሰው የማይበሰብሰውን ሊለብስ ይህም የሚሞተው የማይሞተውን ሊለብስ ይገባዋልና።
52in a moment, in the twinkling of an eye, at the last trumpet. For the trumpet will sound, and the dead will be raised incorruptible, and we will be changed.
54ዳሩ ግን ይህ የሚበሰብሰው የማይበሰብሰውን ሲለብስ ይህም የሚሞተው የማይሞተውን ሲለብስ፥ በዚያን ጊዜ። ሞት ድል በመነሣት ተዋጠ ተብሎ የተጻፈው ቃል ይፈጸማል።
53For this corruptible must put on incorruption, and this mortal must put on immortality.
55ሞት ሆይ፥ መውጊያህ የት አለ? ሲኦል ሆይ፥ ድል መንሣትህ የት አለ?
54But when this corruptible will have put on incorruption, and this mortal will have put on immortality, then what is written will happen: “Death is swallowed up in victory.” Isaiah 25:8
56የሞት መውጊያ ኃጢአት ነው የኃጢአትም ኃይል ሕግ ነው፤
55“Death, where is your sting? Hades or, Hell , where is your victory?” Hosea 13:14
57ነገር ግን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ድል መንሣትን ለሚሰጠን ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን።
56The sting of death is sin, and the power of sin is the law.
58ስለዚህ፥ የተወደዳችሁ ወንድሞቼ ሆይ፥ ድካማችሁ በጌታ ከንቱ እንዳይሆን አውቃችኋልና የምትደላደሉ፥ የማትነቃነቁም፥ የጌታም ሥራ ሁልጊዜ የሚበዛላችሁ ሁኑ።
57But thanks be to God, who gives us the victory through our Lord Jesus Christ.
58Therefore, my beloved brothers, be steadfast, immovable, always abounding in the Lord’s work, because you know that your labor is not in vain in the Lord.