Amharic: New Testament

World English Bible

1 Thessalonians

5

1ወንድሞች ሆይ፥ ስለ ዘመናትና ስለ ወራት ምንም እንዲጻፍላችሁ አያስፈልጋችሁም፤
1But concerning the times and the seasons, brothers, you have no need that anything be written to you.
2የጌታ ቀን፥ ሌባ በሌሊት እንደሚመጣ፥ እንዲሁ ይመጣ ዘንድ ራሳችሁ አጥብቃችሁ አውቃችኋልና።
2For you yourselves know well that the day of the Lord comes like a thief in the night.
3ሰላምና ደኅንነት ነው ሲሉ ያን ጊዜ ምጥ እርጕዝን እንደሚይዛት ጥፋት በድንገት ይመጣባቸዋል ከቶም አያመልጡም።
3For when they are saying, “Peace and safety,” then sudden destruction will come on them, like birth pains on a pregnant woman; and they will in no way escape.
4እናንተ ግን፥ ወንድሞች ሆይ፥ ቀኑ እንደ ሌባ ይደርስባችሁ ዘንድ በጨለማ አይደላችሁም፥
4But you, brothers, aren’t in darkness, that the day should overtake you like a thief.
5ሁላችሁ የብርሃን ልጆች የቀንም ልጆች ናችሁና። እኛ ከሌሊት ወይም ከጨለማ አይደለንም፤
5You are all children of light, and children of the day. We don’t belong to the night, nor to darkness,
6እንግዲያስ እንንቃ በመጠንም እንኑር እንጂ እንደ ሌሎች አናንቀላፋ።
6so then let’s not sleep, as the rest do, but let’s watch and be sober.
7የሚያንቀላፉ በሌሊት ያንቀላፋሉና፥ የሚሰክሩም በሌሊት ይሰክራሉና፤
7For those who sleep, sleep in the night, and those who are drunk are drunk in the night.
8እኛ ግን ከቀን ስለ ሆንን፥ የእምነትንና የፍቅርን ጥሩር የመዳንንም ተስፋ እንደ ራስ ቁር እየለበስን በመጠን እንኑር፤
8But let us, since we belong to the day, be sober, putting on the breastplate of faith and love, and, for a helmet, the hope of salvation.
9እግዚአብሔር ለቍጣ አልመረጠንምና፥ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ መዳንን ለማግኘት ነው እንጂ።
9For God didn’t appoint us to wrath, but to the obtaining of salvation through our Lord Jesus Christ,
10የምንነቃም ብንሆን፥ የምናንቀላፋም ብንሆን፥ ከእርሱ ጋር አብረን በሕይወት እንኖር ዘንድ ስለ እኛ ሞተ።
10who died for us, that, whether we wake or sleep, we should live together with him.
11ስለዚህ እናንተ ደግሞ እንደምታደርጉ፥ እርስ በርሳችሁ ተመካከሩ አንዱም አንዱም ሌላውን ያንጸው።
11Therefore exhort one another, and build each other up, even as you also do.
12ወንድሞች ሆይ፥ በመካከላችሁ የሚደክሙትን በጌታም የሚገዙአችሁን የሚገሥጹአችሁንም ታውቁ ዘንድ፥ ስለ ሥራቸውም በፍቅር ከመጠን ይልቅ ታከብሩአቸው ዘንድ እንለምናችኋለን። እርስ በርሳችሁ በሰላም ሁኑ።
12But we beg you, brothers, to know those who labor among you, and are over you in the Lord, and admonish you,
14ወንድሞች ሆይ፥ እንመክራችኋለን፤ ያለ ሥርዓት የሚሄዱትን ገሥጹአቸው፤ ድፍረት የሌላቸውን አጽኑአቸው፤ ለደካሞች ትጉላቸው፤ ሰውን ሁሉ ታገሡ።
13and to respect and honor them in love for their work’s sake. Be at peace among yourselves.
15ማንም ለሌላው በክፉ ፈንታ ክፉ እንዳይመልስ ተጠንቀቁ፥ ነገር ግን ሁልጊዜ እርስ በርሳችሁ ለሁሉም መልካሙን ለማድረግ ትጉ።
14We exhort you, brothers, admonish the disorderly, encourage the fainthearted, support the weak, be patient toward all.
16ሁልጊዜ ደስ ይበላችሁ፤
15See that no one returns evil for evil to anyone, but always follow after that which is good, for one another, and for all.
17ሳታቋርጡ ጸልዩ፤ በሁሉ አመስግኑ፤ ይህ የእግዚአብሔር ፈቃድ በክርስቶስ ኢየሱስ ወደ እናንተ ነውና።
16Rejoice always.
19መንፈስን አታጥፉ፤
17Pray without ceasing.
20ትንቢትን አትናቁ፤ ሁሉን ፈትኑ መልካሙንም ያዙ፤
18In everything give thanks, for this is the will of God in Christ Jesus toward you.
22ከማናቸውም ዓይነት ክፉ ነገር ራቁ።
19Don’t quench the Spirit.
23የሰላምም አምላክ ራሱ ሁለንተናችሁን ይቀድስ፤ መንፈሳችሁም ነፍሳችሁም ሥጋችሁም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመጣ ጊዜ ያለ ነቀፋ ፈጽመው ይጠበቁ።
20Don’t despise prophesies.
24የሚጠራችሁ የታመነ ነው፥ እርሱም ደግሞ ያደርገዋል።
21Test all things, and hold firmly that which is good.
25ወንድሞች ሆይ፥ ስለ እኛ ጸልዩ።
22Abstain from every form of evil.
26ከወንድሞች ሁሉ ጋር በተቀደሰ አሳሳም ሰላምታ ተሰጣጡ።
23May the God of peace himself sanctify you completely. May your whole spirit, soul, and body be preserved blameless at the coming of our Lord Jesus Christ.
27ይህ መልእክት ለቅዱሳን ወንድሞች ሁሉ እንዲነበብ በጌታ አምላችኋለሁ።
24He who calls you is faithful, who will also do it.
28የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ ከእናንተ ጋር ይሁን፤ አሜን።
25Brothers, pray for us.
26Greet all the brothers with a holy kiss.
27I solemnly command you by the Lord that this letter be read to all the holy brothers.
28The grace of our Lord Jesus Christ be with you. Amen.