Amharic: New Testament

World English Bible

Galatians

5

1በነጻነት ልንኖር ክርስቶስ ነጻነት አወጣን፤ እንግዲህ ጸንታችሁ ቁሙ እንደ ገናም በባርነት ቀንበር አትያዙ።
1Stand firm therefore in the liberty by which Christ has made us free, and don’t be entangled again with a yoke of bondage.
2እነሆ፥ እኔ ጳውሎስ እላችኋለሁ። ብትገረዙ ክርስቶስ ምንም አይጠቅማችሁም።
2Behold, I, Paul, tell you that if you receive circumcision, Christ will profit you nothing.
3ሕግንም ሁሉ እንዲፈጽም ግድ አለበት ብዬ ለሚገረዙት ሁሉ ለእያንዳንዶች ደግሜ እመሰክራለሁ።
3Yes, I testify again to every man who receives circumcision, that he is a debtor to do the whole law.
4በሕግ ልትጸድቁ የምትፈልጉ ከክርስቶስ ተለይታችሁ ከጸጋው ወድቃችኋል።
4You are alienated from Christ, you who desire to be justified by the law. You have fallen away from grace.
5እኛ በመንፈስ ከእምነት የጽድቅን ተስፋ እንጠባበቃለንና።
5For we, through the Spirit, by faith wait for the hope of righteousness.
6በክርስቶስ ኢየሱስ ሆኖ፥ በፍቅር የሚሠራ እምነት እንጂ መገረዝ ቢሆን ወይም አለመገረዝ አይጠቅምምና።
6For in Christ Jesus neither circumcision amounts to anything, nor uncircumcision, but faith working through love.
7በመልካም ትሮጡ ነበር፤ ለእውነት እንዳትታዘዙ ማን ከለከላችሁ?
7You were running well! Who interfered with you that you should not obey the truth?
8ይህ ማባበል ከሚጠራችሁ አልወጣም። ጥቂት እርሾ ሊጡን ሁሉ ያቦካል።
8This persuasion is not from him who calls you.
9የተለየ ነገር ከቶ እንዳታስቡ እኔ በጌታ ስለ እናንተ ታምኜአለሁ፤ የሚያናውጣችሁ ማንም ቢኖር ግን ፍርዱን ሊሸከም ነው።
9A little yeast grows through the whole lump.
11ነገር ግን፥ ወንድሞች ሆይ፥ እኔ ገና እስከ አሁን መገረዝን ብሰብክ እስከ አሁን ድረስ ለምን ያሳድዱኛል? እንኪያስ የመስቀል ዕንቅፋት ተወግዶአል።
10I have confidence toward you in the Lord that you will think no other way. But he who troubles you will bear his judgment, whoever he is.
12የሚያውኩአችሁ ይቆረጡ።
11But I, brothers, if I still preach circumcision, why am I still persecuted? Then the stumbling block of the cross has been removed.
13ወንድሞች ሆይ፥ እናንተ ለአርነት ተጠርታችኋልና፤ ብቻ አርነታችሁ ለሥጋ ምክንያትን አይስጥ፥ ነገር ግን በፍቅር እርስ በርሳችሁ እንደ ባሪያዎች ሁኑ።
12I wish that those who disturb you would cut themselves off.
14ሕግ ሁሉ በአንድ ቃል ይፈጸማልና፥ እርሱም። ባልንጀራህን እንደ ራስህ ውደድ የሚል ነው።
13For you, brothers, were called for freedom. Only don’t use your freedom for gain to the flesh, but through love be servants to one another.
15ነገር ግን እርስ በርሳችሁ ብትነካከሱ ብትበላሉ እርስ በርሳችሁ እንዳትጠፋፉ ተጠንቀቁ።
14For the whole law is fulfilled in one word, in this: “You shall love your neighbor as yourself.”
16ነገር ግን እላለሁ፥ በመንፈስ ተመላለሱ፥ የሥጋንም ምኞት ከቶ አትፈጽሙ።
15But if you bite and devour one another, be careful that you don’t consume one another.
17ሥጋ በመንፈስ ላይ መንፈስም በሥጋ ላይ ይመኛልና፥ እነዚህም እርስ በርሳቸው ይቀዋወማሉ፤ ስለዚህም የምትወዱትን ልታደርጉ አትችሉም።
16But I say, walk by the Spirit, and you won’t fulfill the lust of the flesh.
18በመንፈስ ብትመሩ ግን ከሕግ በታች አይደላችሁም።
17For the flesh lusts against the Spirit, and the Spirit against the flesh; and these are contrary to one another, that you may not do the things that you desire.
19የሥጋ ሥራም የተገለጠ ነው እርሱም ዝሙት፥ ርኵሰት፥
18But if you are led by the Spirit, you are not under the law.
20መዳራት፥ ጣዖትን ማምለክ፥ ምዋርት፥ ጥል፥ ክርክር፥ ቅንዓት፥ ቁጣ፥ አድመኛነት፥
19Now the works of the flesh are obvious, which are: adultery, sexual immorality, uncleanness, lustfulness,
21መለያየት፥ መናፍቅነት፥ ምቀኝነት፥ መግደል፥ ስካር፥ ዘፋኝነት፥ ይህንም የሚመስል ነው። አስቀድሜም እንዳልሁ፥ እንደዚህ ያሉትን የሚያደርጉ የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም።
20idolatry, sorcery, hatred, strife, jealousies, outbursts of anger, rivalries, divisions, heresies,
22የመንፈስ ፍሬ ግን ፍቅር፥ ደስታ፥ ሰላም፥ ትዕግሥት፥ ቸርነት፥ በጎነት፥ እምነት፥ የውሃት፥ ራስን መግዛት ነው።
21envyings, murders, drunkenness, orgies, and things like these; of which I forewarn you, even as I also forewarned you, that those who practice such things will not inherit the Kingdom of God.
23እንደዚህ ያሉትን የሚከለክል ሕግ የለም።
22But the fruit of the Spirit is love, joy, peace, patience, kindness, goodness, faith,
24የክርስቶስ ኢየሱስም የሆኑቱ ሥጋን ከክፉ መሻቱና ከምኞቱ ጋር ሰቀሉ።
23gentleness, and self-control. Against such things there is no law.
25በመንፈስ ብንኖር በመንፈስ ደግሞ እንመላለስ።
24Those who belong to Christ have crucified the flesh with its passions and lusts.
26እርስ በርሳችን እየተነሣሣንና እየተቀናናን በከንቱ አንመካ።
25If we live by the Spirit, let’s also walk by the Spirit.
26Let’s not become conceited, provoking one another, and envying one another.