Amharic: New Testament

World English Bible

Luke

22

1ፋሲካም የሚባለው የቂጣ በዓል ቀረበ።
1Now the feast of unleavened bread, which is called the Passover, drew near.
2የካህናት አለቆችና ጻፎችም እንዴት እንዲያጠፉት ይፈልጉ ነበር፤ ሕዝቡን ይፈሩ ነበርና።
2The chief priests and the scribes sought how they might put him to death, for they feared the people.
3ሰይጣንም ከአሥራ ሁለቱ ቍጥር አንዱ በነበረው የአስቆሮቱ በሚባለው በይሁዳ ገባ፤
3Satan entered into Judas, who was surnamed Iscariot, who was numbered with the twelve.
4ሄዶም እንዴት አሳልፎ እንዲሰጣቸው ከካህናት አለቆችና ከመቅደስ አዛዦች ጋር ተነጋገረ።
4He went away, and talked with the chief priests and captains about how he might deliver him to them.
5እነርሱም ደስ አላቸው፥ ገንዘብም ሊሰጡት ተዋዋሉ።
5They were glad, and agreed to give him money.
6እሺም አለ፥ ሕዝብም በሌለበት አሳልፎ እንዲሰጣቸው ምቹ ጊዜ ይፈልግ ነበር።
6He consented, and sought an opportunity to deliver him to them in the absence of the multitude.
7ፋሲካንም ሊያርዱበት የሚገባው የቂጣ በዓል ደረሰ፤
7The day of unleavened bread came, on which the Passover must be sacrificed.
8ጴጥሮስንና ዮሐንስንም። ፋሲካን እንድንበላ ሄዳችሁ አዘጋጁልን ብሎ ላካቸው።
8He sent Peter and John, saying, “Go and prepare the Passover for us, that we may eat.”
9እነርሱም። ወዴት እናዘጋጅ ዘንድ ትወዳለህ? አሉት።
9They said to him, “Where do you want us to prepare?”
10እርሱም አላቸው። እነሆ፥ ወደ ከተማ ስትገቡ ማድጋ ውኃ የተሸከመ ሰው ይገናኛችኋል፤ ወደ ሚገባበት ቤት ተከተሉት፤
10He said to them, “Behold, when you have entered into the city, a man carrying a pitcher of water will meet you. Follow him into the house which he enters.
11ለባለቤቱም። መምህሩ። ከደቀ መዛሙርቴ ጋር ፋሲካን የምበላበት የእንግዳ ቤት ክፍል ወዴት ነው? ይልሃል በሉት፤
11 Tell the master of the house, ‘The Teacher says to you, “Where is the guest room, where I may eat the Passover with my disciples?”’
12ያም በደርብ ላይ ያለውን የተነጠፈ ታላቅ አዳራሽ ያሳያችኋል፤ በዚያም አሰናዱልን።
12 He will show you a large, furnished upper room. Make preparations there.”
13ሄደውም እንዳላቸው አገኙና ፋሲካን አሰናዱ።
13They went, found things as he had told them, and they prepared the Passover.
14ሰዓቱም በደረሰ ጊዜ ከአሥራ ሁለቱ ሐዋርያት ጋር በማዕድ ተቀመጠ።
14When the hour had come, he sat down with the twelve apostles.
15እርሱም። ከመከራዬ በፊት ከእናንተ ጋር ይህን ፋሲካ ልበላ እጅግ እመኝ ነበር፤
15He said to them, “I have earnestly desired to eat this Passover with you before I suffer,
16እላችኋለሁና፥ በእግዚአብሔር መንግሥት እስኪፈጸም ድረስ፥ ወደ ፊት ከዚህ አልበላም አላቸው።
16 for I tell you, I will no longer by any means eat of it until it is fulfilled in the Kingdom of God.”
17ጽዋንም ተቀበለ አመስግኖም። ይህን እንካችሁ በመካከላችሁም ተካፈሉት፤
17He received a cup, and when he had given thanks, he said, “Take this, and share it among yourselves,
18እላችኋለሁና፥ የእግዚአብሔር መንግሥት እስክትመጣ ድረስ ከአሁን ጀምሮ ከወይኑ ፍሬ አልጠጣም አለ።
18 for I tell you, I will not drink at all again from the fruit of the vine, until the Kingdom of God comes.”
19እንጀራንም አንሥቶ አመሰገነ ቆርሶም ሰጣቸውና። ስለ እናንተ የሚሰጠው ሥጋዬ ይህ ነው፤ ይህን ለመታሰቢያዬ አድርጉት አለ።
19He took bread, and when he had given thanks, he broke it, and gave to them, saying, “This is my body which is given for you. Do this in memory of me.”
20እንዲሁም ከእራት በኋላ ጽዋውን አንሥቶ እንዲህ አለ። ይህ ጽዋ ስለ እናንተ በሚፈሰው በደሜ የሚሆን አዲስ ኪዳን ነው።
20Likewise, he took the cup after supper, saying, “This cup is the new covenant in my blood, which is poured out for you.
21ነገር ግን አሳልፎ የሚሰጠኝ እጅ እነሆ በማዕድ ከእኔ ጋር ናት።
21 But behold, the hand of him who betrays me is with me on the table.
22የሰው ልጅስ እንደ ተወሰነው ይሄዳል፥ ነገር ግን አልፎ ለሚሰጥበት ለዚያ ሰው ወዮለት።
22 The Son of Man indeed goes, as it has been determined, but woe to that man through whom he is betrayed!”
23ከእነርሱም ይህን ሊያደርግ ያለው ማን እንደ ሆነ እርስ በርሳቸው ይጠያየቁ ጀመር።
23They began to question among themselves, which of them it was who would do this thing.
24ደግሞም ማናቸውም ታላቅ ሆኖ እንዲቈጠር በመካከላቸው ክርክር ሆነ።
24There arose also a contention among them, which of them was considered to be greatest.
25እንዲህም አላቸው። የአሕዛብ ነገሥታት ይገዙአቸዋል፥ በላያቸውም የሚሠለጥኑት ቸርነት አድራጊዎች ይባላሉ።
25He said to them, “The kings of the nations lord it over them, and those who have authority over them are called ‘benefactors.’
26እናንተ ግን እንዲህ አትሁኑ፤ ነገር ግን ከእናንተ ታላቅ የሆነ በመካከላችሁ እንደ ታናሽ፥ የሚገዛም እንደሚያገለግል ይሁን።
26 But not so with you. But one who is the greater among you, let him become as the younger, and one who is governing, as one who serves.
27በማዕድ የተቀመጠ ወይስ የሚያገለግል ማናቸው ታላቅ ነው? የተቀመጠው አይደለምን? እኔ ግን በመካከላችሁ እንደሚያገለግል ነኝ።
27 For who is greater, one who sits at the table, or one who serves? Isn’t it he who sits at the table? But I am in the midst of you as one who serves.
28ነገር ግን እናንተ በፈተናዎቼ ከእኔ ጋር ጸንታችሁ የኖራችሁ ናችሁ፤
28 But you are those who have continued with me in my trials.
29አባቴ እኔን እንደ ሾመኝ እኔ ደግሞ በመንግሥቴ ከማዕዴ ትበሉና ትጠጡ ዘንድ፥ በአሥራ ሁለቱ በእስራኤል ነገድ ስትፈርዱ በዙፋኖች ትቀመጡ ዘንድ ለመንግሥት እሾማችኋለሁ።
29 I confer on you a kingdom, even as my Father conferred on me,
31ጌታም። ስምዖን ስምዖን ሆይ፥ እነሆ፥ ሰይጣን እንደ ስንዴ ሊያበጥራችሁ ለመነ፤
30 that you may eat and drink at my table in my Kingdom. You will sit on thrones, judging the twelve tribes of Israel.”
32እኔ ግን እምነትህ እንዳይጠፋ ስለ አንተ አማለድሁ፤ አንተም በተመለስህ ጊዜ ወንድሞችህን አጽና አለ።
31The Lord said, “Simon, Simon, behold, Satan asked to have you, that he might sift you as wheat,
33እርሱም። ጌታ ሆይ፥ ወደ ወኅኒም ወደ ሞትም ከአንተ ጋር ለመሄድ የተዘጋጀሁ ነኝ አለው።
32 but I prayed for you, that your faith wouldn’t fail. You, when once you have turned again, establish your brothers .”
34እርሱ ግን። ጴጥሮስ ሆይ፥ እልሃለሁ፥ እንዳታውቀኝ ሦስት ጊዜ እስክትክደኝ ድረስ ዛሬ ዶሮ አይጮኽም አለው።
33He said to him, “Lord, I am ready to go with you both to prison and to death!”
35ደግሞም። ያለ ኮረጆና ያለ ከረጢት ያለ ጫማም በላክኋችሁ ጊዜ፥ አንዳች ጐደለባችሁን? አላቸው። እነርሱም። አንዳች እንኳ አሉ።
34He said, “I tell you, Peter, the rooster will by no means crow today until you deny that you know me three times.”
36እርሱም። አሁን ግን ኮረጆ ያለው ከእርሱ ጋር ይውሰድ፥ ከረጢትም ያለው እንዲሁ፤ የሌለውም ልብሱን ሽጦ ሰይፍ ይግዛ።
35He said to them, “When I sent you out without purse, and wallet, and shoes, did you lack anything?” They said, “Nothing.”
37እላችኋለሁና፥ ይህ። ከዓመፀኞች ጋር ተቈጠረ ተብሎ የተጻፈው በእኔ ሊፈጸም ግድ ነው፤ አዎን፥ ስለ እኔ የሚሆነው አሁን ይፈጸማልና አላቸው።
36Then he said to them, “But now, whoever has a purse, let him take it, and likewise a wallet. Whoever has none, let him sell his cloak, and buy a sword.
38እነርሱም። ጌታ ሆይ፥ እነሆ፥ በዚህ ሁለት ሰይፎች አሉ አሉት። እርሱም። ይበቃል አላቸው።
37 For I tell you that this which is written must still be fulfilled in me: ‘He was counted with transgressors.’ For that which concerns me has an end.”
39ወጥቶም እንደ ልማዱ ወደ ደብረ ዘይት ሄደ፤ ደቀ መዛሙርቱም ደግሞ ተከተሉት።
38They said, “Lord, behold, here are two swords.” He said to them, “That is enough.”
40ወደ ስፍራውም ደርሶ። ወደ ፈተና እንዳትገቡ ጸልዩ አላቸው።
39He came out, and went, as his custom was, to the Mount of Olives. His disciples also followed him.
41ከእነርሱም የድንጋይ ውርወራ የሚያህል ራቀ፥ ተንበርክኮም። አባት ሆይ፥
40When he was at the place, he said to them, “Pray that you don’t enter into temptation.”
42ብትፈቅድ ይህችን ጽዋ ከእኔ ውሰድ፤ ነገር ግን የእኔ ፈቃድ አይሁን የአንተ እንጂ እያለ ይጸልይ ነበር።
41He was withdrawn from them about a stone’s throw, and he knelt down and prayed,
43ከሰማይም መጥቶ የሚያበረታ መልአክ ታየው።
42saying, “Father, if you are willing, remove this cup from me. Nevertheless, not my will, but yours, be done.”
44በፍርሃትም ሲጣጣር አጽንቶ ይጸልይ ነበር፤ ወዙም በምድር ላይ እንደሚወርድ እንደ ደም ነጠብጣብ ነበረ።
43An angel from heaven appeared to him, strengthening him.
45ከጸሎትም ተነሥቶ ወደ ደቀ መዛሙርቱ መጣና ከኀዘን የተነሣ ተኝተው ሲያገኛቸው።
44Being in agony he prayed more earnestly. His sweat became like great drops of blood falling down on the ground.
46ስለ ምን ትተኛላችሁ? ወደ ፈተና እንዳትገቡ ተነሥታችሁ ጸልዩ አላቸው።
45When he rose up from his prayer, he came to the disciples, and found them sleeping because of grief,
47ገናም ሲናገር እነሆ፥ ሰዎች መጡ፤ ከአሥራ ሁለቱ አንዱም ይሁዳ የሚባለው ይቀድማቸው ነበር፥ ሊስመውም ወደ ኢየሱስ ቀረበ።
46and said to them, “Why do you sleep? Rise and pray that you may not enter into temptation.”
48ኢየሱስ ግን። ይሁዳ ሆይ፥ በመሳም የሰውን ልጅ አሳልፈህ ትሰጣለህን? አለው።
47While he was still speaking, behold, a multitude, and he who was called Judas, one of the twelve, was leading them. He came near to Jesus to kiss him.
49በዙሪያውም የነበሩት የሚሆነውን ባዩ ጊዜ። ጌታ ሆይ፥ በሰይፍ እንምታቸውን? አሉት።
48But Jesus said to him, “Judas, do you betray the Son of Man with a kiss?”
50ከእነርሱም አንዱ የሊቀ ካህናቱን ባሪያ መትቶ ቀኝ ጆሮውን ቈረጠው።
49When those who were around him saw what was about to happen, they said to him, “Lord, shall we strike with the sword?”
51ኢየሱስ ግን መልሶ። ይህንስ ፍቀዱ አለ፤ ጆሮውንም ዳስሶ ፈወሰው።
50A certain one of them struck the servant of the high priest, and cut off his right ear.
52ኢየሱስም ወደ እርሱ ለመጡበት ለካህናት አለቆችና ለመቅደስ አዛዦች ለሽማግሌዎችም። ወንበዴን እንደምትይዙ ሰይፍና ጐመድ ይዛችሁ ወጣችሁን?
51But Jesus answered, “Let me at least do this” —and he touched his ear, and healed him.
53በመቅደስ ዕለት ዕለት ከእናንተ ጋር ስሆን እጆቻችሁን አልዘረጋችሁብኝም፤ ይህ ግን ጊዜያችሁና የጨለማው ሥልጣን ነው አላቸው።
52Jesus said to the chief priests, captains of the temple, and elders, who had come against him, “Have you come out as against a robber, with swords and clubs?
54ይዘውም ወሰዱት ወደ ሊቀ ካህናት ቤትም አገቡት፤ ጴጥሮስም ርቆ ይከተለው ነበር።
53 When I was with you in the temple daily, you didn’t stretch out your hands against me. But this is your hour, and the power of darkness.”
55በግቢ መካከልም እሳት አንድደው በአንድነት ተቀምጠው ሳሉ ጴጥሮስ በመካከላቸው ተቀመጠ።
54They seized him, and led him away, and brought him into the high priest’s house. But Peter followed from a distance.
56በብርሃኑም በኩል ተቀምጦ ሳለ አንዲት ገረድ አየችውና ትኵር ብላ። ይህ ደግሞ ከእርሱ ጋር ነበረ አለች።
55When they had kindled a fire in the middle of the courtyard, and had sat down together, Peter sat among them.
57እርሱ ግን። አንቺ ሴት፥ አላውቀውም ብሎ ካደ።
56A certain servant girl saw him as he sat in the light, and looking intently at him, said, “This man also was with him.”
58ከጥቂት ጊዜም በኋላ ሌላው አይቶት። አንተ ደግሞ ከእነርሱ ወገን ነህ አለው። ጴጥሮስ ግን። አንተ ሰው፥ እኔ አይደለሁም አለ።
57He denied Jesus, saying, “Woman, I don’t know him.”
59አንድ ሰዓትም የሚያህል ቆይቶ ሌላው አስረግጦ። እርሱ የገሊላ ሰው ነውና በእውነት ይህ ደግሞ ከእርሱ ጋር ነበረ አለ።
58After a little while someone else saw him, and said, “You also are one of them!” But Peter answered, “Man, I am not!”
60ጴጥሮስ ግን። አንተ ሰው፥ የምትለውን አላውቅም አለ። ያን ጊዜም ገና ሲናገር ዶሮ ጮኸ።
59After about one hour passed, another confidently affirmed, saying, “Truly this man also was with him, for he is a Galilean!”
61ጌታም ዘወር ብሎ ጴጥሮስን ተመለከተው፤ ጴጥሮስም። ዛሬ ዶሮ ሳይጮኽ ሦስት ጊዜ ትክደኛለህ እንዳለው የጌታ ቃል ትዝ አለው።
60But Peter said, “Man, I don’t know what you are talking about!” Immediately, while he was still speaking, a rooster crowed.
62ጴጥሮስም ወደ ውጭ ወጥቶ ምርር ብሎ አለቀሰ።
61The Lord turned, and looked at Peter. Then Peter remembered the Lord’s word, how he said to him, “Before the rooster crows you will deny me three times.”
63ኢየሱስንም የያዙት ሰዎች ይዘብቱበትና ይደበድቡት ነበር፤
62He went out, and wept bitterly.
64ሸፍነውም ፊቱን ይመቱት ነበርና። በጥፊ የመታህ ማን ነው? ትንቢት ተናገር እያሉ ይጠይቁት ነበር።
63The men who held Jesus mocked him and beat him.
65ሌላም ብዙ ነገር እየተሳደቡ በእርሱ ላይ ይናገሩ ነበር።
64Having blindfolded him, they struck him on the face and asked him, “Prophesy! Who is the one who struck you?”
66በነጋም ጊዜ የሕዝቡ ሽማግሌዎችና የካህናት አለቆች ጻፎችም ተሰብስበው ወደ ሸንጎአቸው ወሰዱትና
65They spoke many other things against him, insulting him.
67ክርስቶስ አንተ ነህን? ንገረን አሉት። እርሱ ግን እንዲህ አላቸው። ብነግራችሁ አታምኑም፤
66As soon as it was day, the assembly of the elders of the people was gathered together, both chief priests and scribes, and they led him away into their council, saying,
68ብጠይቅም አትመልሱልኝም አትፈቱኝምም።
67“If you are the Christ, tell us.” But he said to them, “If I tell you, you won’t believe,
69ነገር ግን ከአሁን ጀምሮ የሰው ልጅ በእግዚአብሔር ኃይል ቀኝ ይቀመጣል።
68 and if I ask, you will in no way answer me or let me go.
70ሁላቸውም። እንግዲያስ አንተ የእግዚአብሔር ልጅ ነህን? አሉት። እርሱም። እኔ እንደ ሆንሁ እናንተ ትላላችሁ አላቸው።
69 From now on, the Son of Man will be seated at the right hand of the power of God.”
71እነርሱም። ራሳችን ከአፉ ሰምተናልና ከእንግዲህ ወዲህ ምን ምስክር ያስፈልገናል? አሉ።
70They all said, “Are you then the Son of God?” He said to them, “You say it, because I am.”
71They said, “Why do we need any more witness? For we ourselves have heard from his own mouth!”