1ደግሞም ወደ ምኵራብ ገባ፥ በዚያም እጁ የሰለለች ሰው ነበር፤
1He entered again into the synagogue, and there was a man there who had his hand withered.
2ሊከሱትም፥ በሰንበት ይፈውሰው እንደ ሆነ ይጠባበቁት ነበር።
2They watched him, whether he would heal him on the Sabbath day, that they might accuse him.
3እጁ የሰለለችውንም ሰው። ተነሥተህ ወደ መካከል ና አለው።
3He said to the man who had his hand withered, “Stand up.”
4በሰንበት በጎ ማድረግ ተፈቅዶአልን? ወይስ ክፉ? ነፍስ ማዳን ወይስ መግደል? አላቸው፤ እነርሱም ዝም አሉ።
4He said to them, “Is it lawful on the Sabbath day to do good, or to do harm? To save a life, or to kill?” But they were silent.
5ስለ ልባቸውም ድንዛዜ አዝኖ ዙሪያውን እየተመለከተ በቍጣ አያቸው፥ ሰውየውንም። እጅህን ዘርጋ አለው።
5When he had looked around at them with anger, being grieved at the hardening of their hearts, he said to the man, “Stretch out your hand.” He stretched it out, and his hand was restored as healthy as the other.
6ዘረጋትም፥ እጁም ዳነች። ፈሪሳውያንም ወጥተው ወዲያው እንዴት አድርገው እንዲያጠፉት ከሄሮድስ ወገን ጋር ተማከሩበት።
6The Pharisees went out, and immediately conspired with the Herodians against him, how they might destroy him.
7ኢየሱስም ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ወደ ባህር ፈቀቅ አለ፤ ከገሊላ የመጡም ብዙ ሰዎች ተከተሉት፤
7Jesus withdrew to the sea with his disciples, and a great multitude followed him from Galilee, from Judea,
8እንዴት ትልቅ ነገርም እንዳደረገው ሰምተው ብዙ ሰዎች ከይሁዳ ከኢየሩሳሌምም ከኤዶምያስም ከዮርዳኖስ ማዶም ከጢሮስና ከሲዶና ምድርም ወደ እርሱ መጡ።
8from Jerusalem, from Idumaea, beyond the Jordan, and those from around Tyre and Sidon. A great multitude, hearing what great things he did, came to him.
9ሰዎቹም እንዳያጋፉት ታንኳን ያቆዩለት ዘንድ ደቀ መዛሙርቱን አዘዛቸው፤
9He spoke to his disciples that a little boat should stay near him because of the crowd, so that they wouldn’t press on him.
10ብዙ ሰዎችን አድኖ ነበርና፥ ስለዚህም ሥቃይ ያለባቸው ሁሉ እንዲዳስሱት ይወድቁበት ነበር።
10For he had healed many, so that as many as had diseases pressed on him that they might touch him.
11ርኵሳን መናፍስትም ባዩት ጊዜ በፊቱ ተደፍተው። አንተ የእግዚአብሔር ልጅ ነህ እያሉ ጮኹ።
11The unclean spirits, whenever they saw him, fell down before him, and cried, “You are the Son of God!”
12እንዳይገልጡትም በጣም አዘዛቸው።
12He sternly warned them that they should not make him known.
13ወደ ተራራም ወጣ፥ ራሱም የወደዳቸውን ወደ እርሱ ጠራ፥ ወደ እርሱም ሄዱ።
13He went up into the mountain, and called to himself those whom he wanted, and they went to him.
14ከእርሱም ጋር እንዲኖሩና ለመስበክ እንዲልካቸው፥
14He appointed twelve, that they might be with him, and that he might send them out to preach,
15ድውዮችንም ሊፈውሱ አጋንንትንም ሊያወጡ ሥልጣን ይሆንላቸው ዘንድ አሥራ ሁለት አደረገ፤
15and to have authority to heal sicknesses and to cast out demons:
16ስምዖንንም ጴጥሮስ ብሎ ሰየመው፤
16Simon, to whom he gave the name Peter;
17የዘብዴዎስንም ልጅ ያዕቆብን የያዕቆብንም ወንድም ዮሐንስን ቦአኔርጌስ ብሎ ሰየማቸው፥ የነጎድጓድ ልጆች ማለት ነው፤
17James the son of Zebedee; John, the brother of James, and he surnamed them Boanerges, which means, Sons of Thunder;
18እንድርያስንም ፊልጶስንም በርተሎሜውስንም ማቴዎስንም ቶማስንም የእልፍዮስን ልጅ ያዕቆብንም ታዴዎስንም ቀነናዊውንም ስምዖንን፥
18Andrew; Philip; Bartholomew; Matthew; Thomas; James, the son of Alphaeus; Thaddaeus; Simon the Zealot;
19አሳልፎ የሰጠውንም የአስቆሮቱን ይሁዳን።
19and Judas Iscariot, who also betrayed him. He came into a house.
20ወደ ቤትም መጡ፤ እንጀራም መብላት ስንኳ እስኪሳናቸው ድረስ እንደ ገና ብዙ ሰዎች ተሰበሰቡ።
20The multitude came together again, so that they could not so much as eat bread.
21ዘመዶቹም ሰምተው። አበደ ብለዋልና ሊይዙት ወጡ።
21When his friends heard it, they went out to seize him: for they said, “He is insane.”
22ከኢየሩሳሌም የወረዱ ጻፎችም። ብዔል ዜቡል አለበት፤ ደግሞ። በአጋንንት አለቃ አጋንንትን ያወጣል ብለው ተናገሩ።
22The scribes who came down from Jerusalem said, “He has Beelzebul,” and, “By the prince of the demons he casts out the demons.”
23እነርሱንም ወደ እርሱ ጠርቶ በምሳሌ አላቸው። ሰይጣን ሰይጣንን ሊያወጣው እንዴት ይችላል?
23He summoned them, and said to them in parables, “How can Satan cast out Satan?
24መንግሥትም እርስ በርስዋ ከተለያየች ያች መንግሥት ልትቆም አትችልም፤
24 If a kingdom is divided against itself, that kingdom cannot stand.
25ቤትም እርስ በርሱ ከተለያየ ያ ቤት ሊቆም አይችልም።
25 If a house is divided against itself, that house cannot stand.
26ሰይጣንም ራሱን ተቃውሞ ከተለያየ፥ መጨረሻ ይሆንበታል እንጂ ሊቆም አይችልም።
26 If Satan has risen up against himself, and is divided, he can’t stand, but has an end.
27ነገር ግን አስቀድሞ ኃይለኛውን ሳያስር ወደ ኃይለኛው ቤት ገብቶ ዕቃውን ሊበዘብዝ የሚችል የለም፥ ከዚያም ወዲያ ቤቱን ይበዘብዛል።
27 But no one can enter into the house of the strong man to plunder, unless he first binds the strong man; and then he will plunder his house.
28እውነት እላችኋለሁ፥ ለሰው ልጆች ኃጢአት ሁሉ የሚሳደቡትም ስድብ ሁሉ ይሰረይላቸዋል፤
28 Most certainly I tell you, all sins of the descendants of man will be forgiven, including their blasphemies with which they may blaspheme;
29በመንፈስ ቅዱስ ላይ የሚሳደብ ሁሉ ግን የዘላለም ኃጢአት ዕዳ ይሆንበታል እንጂ ለዘላለም አይሰረይለትም።
29 but whoever may blaspheme against the Holy Spirit never has forgiveness, but is guilty of an eternal sin”
30ርኵስ መንፈስ አለበት ይሉ ነበርና።
30—because they said, “He has an unclean spirit.”
31እናቱና ወንድሞቹም መጡ በውጭም ቆመው ወደ እርሱ ልከው አስጠሩት።
31His mother and his brothers came, and standing outside, they sent to him, calling him.
32ብዙ ሰዎችም በዙሪያው ተቀምጠው ነበሩና። እነሆ፥ እናትህ ወንድሞችህም በውጭ ቆመው ይፈልጉሃል አሉት።
32A multitude was sitting around him, and they told him, “Behold, your mother, your brothers, and your sisters TR omits “your sisters” are outside looking for you.”
33መልሶም። እናቴ ማን ናት? ወንድሞቼስ እነ ማን ናቸው? አላቸው።
33He answered them, “Who are my mother and my brothers?”
34በዙሪያው ተቀምጠው ወደ ነበሩትም ተመለከተና። እነሆ እናቴ ወንድሞቼም።
34Looking around at those who sat around him, he said, “Behold, my mother and my brothers!
35የእግዚአብሔርን ፈቃድ የሚያደርግ ሁሉ፥ እርሱ ወንድሜ ነው እኅቴም እናቴም አለ።
35 For whoever does the will of God, the same is my brother, and my sister, and mother.”