1ኢየሱስም መለሰ ደግሞም በምሳሌ ነገራቸው እንዲህም አለ።
1Jesus answered and spoke again in parables to them, saying,
2መንግሥተ ሰማያት ለልጁ ሰርግ ያደረገ ንጉሥን ትመስላለች።
2 “The Kingdom of Heaven is like a certain king, who made a marriage feast for his son,
3የታደሙትንም ወደ ሰርጉ ይጠሩ ዘንድ ባሮቹን ላከ ሊመጡም አልወደዱም።
3 and sent out his servants to call those who were invited to the marriage feast, but they would not come.
4ደግሞ ሌሎችን ባሮች ልኮ። የታደሙትን። እነሆ፥ ድግሴን አዘጋጀሁ፥ ኮርማዎቼና የሰቡት ከብቶቼ ታርደዋል፥ ሁሉም ተዘጋጅቶአል፤ ወደ ሰርጉ ኑ በሉአቸው አለ።
4 Again he sent out other servants, saying, ‘Tell those who are invited, “Behold, I have prepared my dinner. My cattle and my fatlings are killed, and all things are ready. Come to the marriage feast!”’
5እነርሱ ግን ቸል ብለው አንዱ ወደ እርሻው፥ ሌላውም ወደ ንግዱ ሄደ፤
5 But they made light of it, and went their ways, one to his own farm, another to his merchandise,
6የቀሩትም ባሮቹን ይዘው አንገላቱአቸው ገደሉአቸውም።
6 and the rest grabbed his servants, and treated them shamefully, and killed them.
7ንጉሡም ተቈጣ፥ ጭፍሮቹንም ልኮ እነዚያን ገዳዮች አጠፋ፤ ከተማቸውንም አቃጠለ።
7 When the king heard that, he was angry, and sent his armies, destroyed those murderers, and burned their city.
8በዚያን ጊዜ ባሮቹን። ሰርጉስ ተዘጋጅቶአል፥ ነገር ግን የታደሙት የማይገባቸው ሆኑ፤
8 “Then he said to his servants, ‘The wedding is ready, but those who were invited weren’t worthy.
9እንግዲህ ወደ መንገድ መተላለፊያ ሄዳችሁ ያገኛችሁትን ሁሉ ወደ ሰርጉ ጥሩ አለ።
9 Go therefore to the intersections of the highways, and as many as you may find, invite to the marriage feast.’
10እነዚያም ባሮች ወደ መንገድ ወጥተው ያገኙትን ሁሉ ክፉዎችንም በጎዎችንም ሰበሰቡ፤ የሰርጉንም ቤት ተቀማጮች ሞሉት።
10 Those servants went out into the highways, and gathered together as many as they found, both bad and good. The wedding was filled with guests.
11ንጉሡም የተቀመጡትን ለማየት በገባ ጊዜ በዚያ የሰርግ ልብስ ያለበሰ አንድ ሰው አየና። ወዳጄ ሆይ፥
11 But when the king came in to see the guests, he saw there a man who didn’t have on wedding clothing,
12የሰርግ ልብስ ሳትለብስ እንዴት ወደዚህ ገባህ? አለው እርሱም ዝም አለ።
12 and he said to him, ‘Friend, how did you come in here not wearing wedding clothing?’ He was speechless.
13በዚያን ጊዜ ንጉሡ አገልጋዮቹን። እጁንና እግሩን አስራችሁ በውጭ ወዳለው ጨለማ አውጡት፤ በዚያ ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ይሆናል አለ።
13 Then the king said to the servants, ‘Bind him hand and foot, take him away, and throw him into the outer darkness; there is where the weeping and grinding of teeth will be.’
14የተጠሩ ብዙዎች፥ የተመረጡ ግን ጥቂቶች ናቸውና።
14 For many are called, but few chosen.”
15ስለዚህ ፈሪሳውያን ሄዱና እንዴት አድርገው በነገር እንዲያጠምዱት ተማከሩ።
15Then the Pharisees went and took counsel how they might entrap him in his talk.
16ደቀ መዛሙርታቸውንም ከሄሮድስ ወገን ጋር ላኩበት፥ እነርሱም። መምህር ሆይ፥ እውነተኛ እንደ ሆንህ በእውነትም የእግዚአብሔርን መንገድ እንድታስተምር እናውቃለን፥ ለማንምም አታደላም፥ የሰውን ፊት አትመለከትምና፤
16They sent their disciples to him, along with the Herodians, saying, “Teacher, we know that you are honest, and teach the way of God in truth, no matter whom you teach, for you aren’t partial to anyone.
17እንግዲህ ምን ይመስልሃል? ንገረን ለቄሣር ግብር መስጠት ተፈቅዶአልን ወይስ አልተፈቀደም? አሉት።
17Tell us therefore, what do you think? Is it lawful to pay taxes to Caesar, or not?”
18ኢየሱስም ክፋታቸውን አውቆ። እናንተ ግብዞች፥ ስለ ምን ትፈትኑኛላችሁ?
18But Jesus perceived their wickedness, and said, “Why do you test me, you hypocrites?
19የግብሩን ብር አሳዩኝ አለ። እነርሱም ዲናር አመጡለት።
19 Show me the tax money.” They brought to him a denarius.
20እርሱም። ይህች መልክ ጽሕፈቲቱስ የማን ናት? አላቸው።
20He asked them, “Whose is this image and inscription?”
21የቄሣር ነው አሉት። በዚያን ጊዜ። እንኪያስ የቄሣርን ለቄሣር የእግዚአብሔርንም ለእግዚአብሔር አስረክቡ አላቸው።
21They said to him, “Caesar’s.” Then he said to them, “Give therefore to Caesar the things that are Caesar’s, and to God the things that are God’s.”
22ይህንም ሰምተው ተደነቁ፥ ትተውትም ሄዱ።
22When they heard it, they marveled, and left him, and went away.
23በዚያን ቀን። ትንሣኤ ሙታን የለም የሚሉ ሰዱቃውያን ወደ እርሱ ቀረቡ፥
23On that day Sadducees (those who say that there is no resurrection) came to him. They asked him,
24እንዲህም ብለው ጠየቁት። መምህር ሆይ፥ ሙሴ አንድ ሰው ልጅ ሳይወልድ ሲሞት ወንድሙ ሚስቱን አግብቶ ለወንድሙ ዘር ይተካ አለ።
24saying, “Teacher, Moses said, ‘If a man dies, having no children, his brother shall marry his wife, and raise up seed for his brother.’
25ሰባት ወንድማማች በእኛ ዘንድ ነበሩ፤ ፊተኛውም ሚስት አግብቶ ሞተ፥ ዘርም ስለሌለው ሚስቱን ለወንድሙ ተወለት፤
25Now there were with us seven brothers. The first married and died, and having no seed left his wife to his brother.
26እንዲሁ ደግሞ ሁለተኛው ሦስተኛውም፥ እስከ ሰባተኛው ድረስ።
26In the same way, the second also, and the third, to the seventh.
27ከሁሉም በኋላ ሴቲቱ ሞተች።
27After them all, the woman died.
28ሁሉ አግብተዋታልና በትንሣኤ ቀንስ፥ ከሰባቱ ለማናቸው ሚስት ትሆናለች?
28In the resurrection therefore, whose wife will she be of the seven? For they all had her.”
29ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አላቸው። መጻሕፍትንና የእግዚአብሔርን ኃይል አታውቁምና ትስታላችሁ።
29But Jesus answered them, “You are mistaken, not knowing the Scriptures, nor the power of God.
30በትንሣኤስ እንደ እግዚአብሔር መላእክት በሰማይ ይሆናሉ እንጂ አያገቡም አይጋቡምም።
30 For in the resurrection they neither marry, nor are given in marriage, but are like God’s angels in heaven.
31ስለ ትንሣኤ ሙታን ግን። እኔ የአብርሃም አምላክ፥ የይስሐቅም አምላክ የያዕቆብም አምላክ ነኝ የሚል ከእግዚአብሔር ዘንድ ወደ እናንተ የተባለውን አላነበባችሁምን? የሕያዋን አምላክ ነው እንጂ የሙታን አይደለም።
31 But concerning the resurrection of the dead, haven’t you read that which was spoken to you by God, saying,
33ሕዝቡም ይህን ሰምተው በትምህርቱ ተገረሙ።
32 ‘I am the God of Abraham, and the God of Isaac, and the God of Jacob?’ Exodus 3:6 God is not the God of the dead, but of the living.”
34ፈሪሳውያንም ሰዱቃውያንን ዝም እንዳሰኛቸው በሰሙ ጊዜ አብረው ተሰበሰቡ።
33When the multitudes heard it, they were astonished at his teaching.
35ከእነርሱም አንድ ሕግ አዋቂ ሊፈትነው።
34But the Pharisees, when they heard that he had silenced the Sadducees, gathered themselves together.
36መምህር ሆይ፥ ከሕግ ማናቸይቱ ትእዛዝ ታላቅ ናት? ብሎ ጠየቀው።
35One of them, a lawyer, asked him a question, testing him.
37ኢየሱስም እንዲህ አለው። ጌታ አምላክህን በፍጹም ልብህ በፍጹም ነፍስህም በፍጹም አሳብህም ውደድ።
36“Teacher, which is the greatest commandment in the law?”
38ታላቂቱና ፊተኛይቱ ትእዛዝ ይህች ናት።
37Jesus said to him, “‘You shall love the Lord your God with all your heart, with all your soul, and with all your mind.’ Deuteronomy 6:5
39ሁለተኛይቱም ይህችን ትመስላለች፥ እርስዋም። ባልንጀራህን እንደ ነፍስህ ውደድ የምትለው ናት።
38 This is the first and great commandment.
40በእነዚህ በሁለቱ ትእዛዛት ሕጉም ሁሉ ነቢያትም ተሰቅለዋል።
39 A second likewise is this, ‘You shall love your neighbor as yourself.’ Leviticus 19:18
41ፈሪሳውያንም ተሰብስበው ሳሉ፥ ኢየሱስ። ስለ ክርስቶስ ምን ይመስላችኋል? የማንስ ልጅ ነው? ብሎ ጠየቃቸው። የዳዊት ልጅ ነው አሉት።
40 The whole law and the prophets depend on these two commandments.”
43እርሱም። እንኪያስ ዳዊት። ጌታ ጌታዬን። ጠላቶችህን የእግርህ መረገጫ እስካደርግልህ ድረስ በቀኜ ተቀመጥ አለው ሲል እንዴት በመንፈስ ጌታ ብሎ ይጠራዋል?
41Now while the Pharisees were gathered together, Jesus asked them a question,
45ዳዊትስ ጌታ ብሎ ከጠራው፥ እንዴት ልጁ ይሆናል? አላቸው።
42saying, “What do you think of the Christ? Whose son is he?” They said to him, “Of David.”
46አንድም ቃል ስንኳ ይመልስለት ዘንድ የተቻለው የለም፥ ከዚያ ቀንም ጀምሮ ወደ ፊት ማንም ሊጠይቀው አልደፈረም።
43He said to them, “How then does David in the Spirit call him Lord, saying,
44 ‘The Lord said to my Lord, sit on my right hand, until I make your enemies a footstool for your feet?’ Psalm 110:1
45 “If then David calls him Lord, how is he his son?”
46No one was able to answer him a word, neither did any man dare ask him any more questions from that day forth.