1Sīmanis Pēteris, Jēzus Kristus kalps un apustulis, tiem, kas mūsu Dieva un Pestītāja Jēzus Kristus taisnībā ieguvuši to pašu dārgo ticību kā mēs.
1የኢየሱስ ክርስቶስ ባሪያና ሐዋርያ የሆነ ስምዖን ጴጥሮስ፥ በአምላካችንና በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ጽድቅ ካገኘነው ጋር የተካከለ የክብር እምነትን ላገኙ፤
2Žēlastība un miers lai jūsos pavairojas Dieva un mūsu Kunga Jēzus Kristus atzīšanā.
2የመለኮቱ ኃይል፥ በገዛ ክብሩና በበጎነቱ የጠራንን በማወቅ፥ ለሕይወትና እግዚአብሔርን ለመምሰል የሚሆነውን ነገር ሁሉ ስለ ሰጠን፥ በእግዚአብሔርና በጌታችን በኢየሱስ እውቀት ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ።
3Mums Viņa dievišķā vara dāvinājusi visu vajadzīgo dzīvei un dievbijībai caur Viņa atzīšanu, kas mūs aicinājis ar savu godu un spēku,
4ስለ ክፉ ምኞት በዓለም ካለው ጥፋት አምልጣችሁ ከመለኮት ባሕርይ ተካፋዮች በተስፋ ቃል እንድትሆኑ፥ በእነዚያ ክብርና በጎነት የተከበረና እጅግ ታላቅ የሆነ ተስፋን ሰጠን።
4Dāvinādams mums ļoti lielus un dārgus apsolījumus, lai jūs caur tiem kļūtu dievišķās dabas līdzdalībnieki, bēgdami no kārības posta, kas valda pasaulē.
5ስለዚህም ምክንያት ትጋትን ሁሉ እያሳያችሁ በእምነታችሁ በጎነትን ጨምሩ፥
5Tāpēc pielieciet visas pūles un parādiet savā ticībā tikumu, bet tikumā atzīšanu,
6በበጎነትም እውቀትን፥ በእውቀትም ራስን መግዛት፥ ራስንም በመግዛት መጽናትን፥ በመጽናትም እግዚአብሔርን መምሰል፥
6Atzīšanā atturību, atturībā pacietību, pacietībā dievbijību,
7እግዚአብሔርንም በመምሰል የወንድማማችን መዋደድ፥ በወንድማማችም መዋደድ ፍቅርን ጨምሩ።
7Dievbijībā brāļu mīlestību, mīlestībā tuvākmīlestību!
8እነዚህ ነገሮች ለእናንተ ሆነው ቢበዙ፥ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ እውቀት ሥራ ፈቶችና ፍሬ ቢሶች እንዳትሆኑ ያደርጉአችኋልና፤
8Ja jums tas ir un bagātīgi ir, tad jūs nepaliksiet tukši un neauglīgi mūsu Kunga Jēzus Kristus atzīšanā.
9እነዚህ ነገሮች የሌሉት ዕውር ነውና፥ በቅርብም ያለውን ብቻ ያያል፥ የቀደመውንም ኃጢአቱን መንጻት ረስቶአል።
9Kam tā nav, tas akls un taustās ar roku, aizmirstot, ka viņš šķīstīts no visiem vecajiem grēkiem.
10ስለዚህ፥ ወንድሞች ሆይ፥ መጠራታችሁንና መመረጣችሁን ታጸኑ ዘንድ ከፊት ይልቅ ትጉ፤ እነዚህን ብታደርጉ ከቶ አትሰናከሉምና።
10Tādēļ, brāļi, centieties ar labiem darbiem nodrošināt savu aicinājumu un izvēlēšanu, jo, to darot, jūs nekad negrēkosiet.
11እንዲሁ ወደ ዘላለሙ ወደ ጌታችንና መድኃኒታችን ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ መንግሥት መግባት በሙላት ይሰጣችኋልና።
11Tas bagātīgi veicinās jūsu ieiešanu mūsu Kunga un Pestītāja Jēzus Kristus mūžīgajā valstībā.
12ስለዚህ እነዚህን ነገሮች ምንም ብታውቁ በእናንተም ዘንድ ባለ እውነት ምንም ብትጸኑ፥ ስለ እነዚህ ዘወትር እንዳሳስባችሁ ቸል አልልም።
12Tādēļ es nekad nerimšos jums to atgādināt, kaut gan jūs to zināt un esat nostiprinājušies šinī patiesībā.
13ሁልጊዜም በዚህ ማደሪያ ሳለሁ በማሳሰቤ ላነቃችሁ የሚገባኝ ይመስለኛል።
13Jo kamēr esmu šinī mājoklī, es turu par savu pienākumu uzturēt jūs modrus ar atgādinājumiem,
14ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንዳመለከተኝ ከዚህ ማደሪያዬ መለየቴ ፈጥኖ እንዲሆን አውቃለሁና።
14Jo zinu, ka drīz man šis mājoklis būs jāatstāj, kā jau to arī mūsu Kungs Jēzus Kristus man atklājis.
15ከመውጣቴም በኋላ እነዚህን ነገሮች እንድታስቡ በየጊዜው ትችሉ ዘንድ እተጋለሁ።
15Bet es rūpēšos, lai jūs arī pēc manas nāves varētu bieži to pieminēt.
16የእርሱን ግርማ አይተን እንጂ በብልሃት የተፈጠረውን ተረት ሳንከተል የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ኃይልና መምጣት አስታወቅናችሁ።
16Mēs pasludinājām jums mūsu Kunga Jēzus Kristus spēku un atnākšanu, nesekodami izgudrotajām pasakām, bet būdami aculiecinieki Viņa varenībai.
17ከገናናው ክብር። በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው የሚል ያ ድምፅ በመጣለት ጊዜ ከእግዚአብሔር አብ ክብርንና ምስጋናን ተቀብሎአልና፤
17Jo Viņš saņēma no Dieva Tēva godu un cildinājumu, kad Viņam atskanēja no augsti cēlās godības šāda balss: Šis ir mans mīļais Dēls, pie kā man labpatikšana, Viņu klausiet!
18እኛም በቅዱሱ ተራራ ከእርሱ ጋር ሳለን ይህን ድምፅ ከሰማይ ሲወርድ ሰማን።
18Un šo balsi, kas atskanēja no debesīm, mēs dzirdējām, kad bijām kopā ar Viņu svētajā kalnā.
19ከእርሱም ይልቅ እጅግ የጸና የትንቢት ቃል አለን፤ ምድርም እስኪጠባ ድረስ የንጋትም ኮከብ በልባችሁ እስኪወጣ ድረስ፥ ሰው በጨለማ ስፍራ የሚበራን መብራት እንደሚጠነቀቅ ይህን ቃል እየጠነቀቃችሁ መልካም ታደርጋላችሁ።
19Un pravieša vārds ir mums jo stiprāks, un jūs labi darāt, ievērodami to kā sveci, kas spīd tumšā vietā, kamēr uzausīs diena un rīta zvaigzne uzlēks jūsu sirdīs.
20ይህን በመጀመሪያ እወቁ፤ በመጽሐፍ ያለውን ትንቢት ሁሉ ማንም ለገዛ ራሱ ሊተረጉም አልተፈቀደም፤
20Vispirms to saprotiet, ka neviena pravieša mācība Rakstos nav iztulkojama patvaļīgi,
21ትንቢት ከቶ በሰው ፈቃድ አልመጣምና፥ ዳሩ ግን በእግዚአብሔር ተልከው ቅዱሳን ሰዎች በመንፈስ ቅዱስ ተነድተው ተናገሩ።
21Jo pravietojumi nekad nav cēlušies no cilvēku gribas, bet svētie Dieva cilvēki runājuši, Svētā Gara iedvesmoti.