Latvian: New Testament

Amharic: New Testament

Acts

10

1Bet Cēzarejā bija kāds vīrs, vārdā Kornēlijs. Viņš bija simtnieks tā sauktajā itāliešu karaspēka daļā;
1በቂሣርያም ኢጣሊቄ ለሚሉት ጭፍራ የመቶ አለቃ የሆነ ቆርኔሌዎስ የሚሉት አንድ ሰው ነበረ።
2Viņš ar visu savu namu bija reliģiozs un dievbijīgs; tas deva daudz dāvanu ļaudīm un vienmēr lūdza Dievu.
2እርሱም ከቤተ ሰዎቹ ሁሉ ጋር እግዚአብሔርን የሚያመልክና የሚፈራ ለሕዝብም እጅግ ምጽዋት የሚያደርግ ወደ እግዚአብሔርም ሁልጊዜ የሚጸልይ ነበረ።
3Ap devīto dienas stundu viņš parādībā skaidri redzēja Dieva eņģeli, kas ienāca pie viņa un sacīja: Kornēlij!
3ከቀኑም ዘጠኝ ሰዓት ያህል። ቆርኔሌዎስ ሆይ የሚለው የእግዚአብሔር መልአክ ወደ እርሱ ሲገባ በራእይ በግልጥ አየው።
4Bet viņš, to uzlūkojis un baiļu pārņemts, sacīja: Kas ir, Kungs? Bet tas viņam sacīja: Tavas lūgšanas un tavas nabagu dāvanas pacēlušās Dieva priekšā, lai tevi pieminētu.
4እርሱም ትኵር ብሎ ሲመለከተው ደንግጦ። ጌታ ሆይ፥ ምንድር ነው? አለ። መልአኩም አለው። ጸሎትህና ምጽዋትህ በእግዚአብሔር ፊት ለመታሰቢያ እንዲሆን አረገ።
5Un tagad sūti vīrus uz Jopi un liec ataicināt zināmo Sīmani, kas tiek saukts Pēteris.
5አሁንም ወደ ኢዮጴ ሰዎችን ልከህ ጴጥሮስ የሚባለውን ስምዖንን አስመጣ።
6Viņš viesojas pie viena ādmiņa Sīmaņa, kā māja atrodas pie jūras. Viņš tev pateiks, kas tev jādara.
6እርሱ ቤቱ በባሕር አጠገብ ባለው በቍርበት ፋቂው በስምዖን ዘንድ እንግድነት ተቀምጦአል፤ ልታደርገው የሚገባህን እርሱ ይነግርሃል።
7Kad eņģelis, kas viņam to teica, aizgāja, viņš pasauca savus divus kalpus un vienu dievbijīgu kareivi no tiem, kas bija pie viņa;
7የተናገረውም መልአክ በሄደ ጊዜ፥ ከሎሎዎቹ ሁለቱን፥ ከማይለዩትም ጭፍሮቹ እግዚአብሔርን የሚያመልክ አንዱን ወታደር ጠርቶ፥
8Tiem viņš visu izstāstīja un aizsūtīja tos uz Jopi.
8ነገሩን ሁሉ ተረከላቸው ወደ ኢዮጴም ላካቸው።
9Bet nākošajā dienā, kad tie vēl bija ceļā un tuvojās pilsētai, Pēteris ap sesto stundu uzkāpa mājas augšā lūgt Dievu.
9እነርሱም በነገው ሲሄዱ ወደ ከተማም ሲቀርቡ፥ ጴጥሮስ በስድስት ሰዓት ያህል ይጸልይ ዘንድ ወደ ጣራው ወጣ።
10Un viņš izsalka un gribēja ēst. Kamēr tie sagatavoja, viņš tika garā aizrauts.
10ተርቦም ሊበላ ወደደ፤ ሲያዘጋጁለት ሳሉም ተመስጦ መጣበት፤
11Un viņš redzēja atvērtas debesis un kādu trauku nolaižamies, it kā lielu palagu aiz četriem stūriem no debesīm nolaistu zemē;
11ሰማይም ተከፍቶ በአራት ማዕዘን የተያዘ ታላቅ ሸማ የሚመስል ዕቃ ወደ ምድር ሲወርድ አየ፤
12Tanī bija visādi četrkājaiņi un zemes rāpuļi, un debess putni.
12በዚያውም አራት እግር ያላቸው ሁሉ አራዊትም በምድርም የሚንቀሳቀሱት የሰማይ ወፎችም ነበሩበት።
13Un balss vēstīja viņam: Pēteri, celies, nokauj un ēd!
13ጴጥሮስ ሆይ፥ ተነሣና አርደህ ብላ የሚልም ድምፅ ወደ እርሱ መጣ።
14Bet Pēteris sacīja: Nē, Kungs, es nekad neesmu ēdis neko nešķīstu un netīru.
14ጴጥሮስ ግን። ጌታ ሆይ፥ አይሆንም፤ አንዳች ርኵስ የሚያስጸይፍም ከቶ በልቼ አላውቅምና አለ።
15Tad otrreiz balss uz viņu: Ko Dievs šķīstījis, to nesauc par nešķīstu!
15ደግሞም ሁለተኛ። እግዚአብሔር ያነጻውን አንተ አታርክሰው የሚል ድምፅ ወደ እርሱ መጣ።
16Tas notika trīs reizes; un trauks tūdaļ tika uzņemts debesīs.
16ይህም ሦስት ጊዜ ሆነ፥ ወዲያውም ዕቃው ወደ ሰማይ ተወሰደ።
17Un kamēr Pēteris sevī nodomāja, ko nozīmē redzētā parādība, lūk, Kornēlija sūtītie vīri, meklēdami Sīmaņa namu, stāvēja pie durvīm.
17ጴጥሮስም ስላየው ራእይ። ምን ይሆን? ብሎ በልቡ ሲያመነታ፥ እነሆ፥ ቆርኔሌዎስ የላካቸው ሰዎች ስለ ስምዖን ቤት ጠይቀው ወደ ደጁ ቀረቡ፤
18Un tie sauca, jautādami: Vai te viesojas Sīmanis, kas tiek saukts Pēteris?
18ድምፃቸውንም ከፍ አድርገው። ጴጥሮስ የተባለው ስምዖን በዚህ እንግድነት ተቀምጦአልን? ብለው ይጠይቁ ነበር።
19Bet kamēr Pēteris domāja par parādību, Gars viņam sacīja: Lūk, trīs vīri tevi meklē.
19ጴጥሮስም ስለ ራእዩ ሲያወጣ ሲያወርድ ሳለ፥ መንፈስ። እነሆ፥ ሦስት ሰዎች ይፈልጉሃል፤
20Tāpēc celies, nokāp un nemaz nešaubīdamies, ej viņiem līdz, jo es tos sūtīju!
20ተነሥተህ ውረድ፥ እኔም ልኬአቸዋለሁና ሳትጠራጠር ከእነርሱ ጋር ሂድ አለው።
21Bet Pēteris, nokāpis pie vīriem, sacīja: Lūk, es esmu tas, ko jūs meklējat. Kāda iemesla dēļ jūs atnācāt?
21ጴጥሮስም ወደ ሰዎቹ ወርዶ። እነሆ፥ የምትፈልጉኝ እኔ ነኝ፤ የመጣችሁበትስ ምክንያት ምንድር ነው? አላቸው።
22Tie sacīja: Simtnieks Kornēlijs, taisnīgs un dievbijīgs vīrs, ko godina visa jūdu tauta, saņēma pamācību no svētā eņģeļa, lai aicinātu tevi savā namā un uzklausītu tavus vārdus.
22እነርሱም። ጻድቅ ሰው እግዚአብሔርንም የሚፈራ በአይሁድም ሕዝብ ሁሉ የተመሰከረለት የመቶ አለቃ ቆርኔሌዎስ ወደ ቤቱ ያስመጣህ ዘንድ ከአንተም ቃልን ይሰማ ዘንድ ከቅዱስ መልአክ ተረዳ አሉት።
23Tad viņš ieveda tos iekšā un uzņēma mājvietā; bet nākošajā dienā viņš cēlies gāja tiem līdz; arī daži brāļi no Jopes pavadīja viņu.
23እርሱም ወደ ውስጥ ጠርቶ እንድግድነት ተቀበላቸው። በነገውም ተነሥቶ ከእነርሱ ጋር ወጣ፥ በኢዮጴም ከነበሩት ወንድሞች አንዳንዶቹ ከእርሱ ጋር አብረው ሄዱ።
24Otrā dienā viņš nonāca Cēzarejā. Bet Kornēlijs, saaicinājis savus radus un tuvākos draugus, gaidīja viņus.
24በነገውም ወደ ቂሣርያ ገቡ፤ ቆርኔሌዎስም ዘመዶቹንና የቅርብ ወዳጆቹን በአንድነት ጠርቶ ይጠባበቃቸው ነበር።
25Un notika, ka, Pēterim ienākot, Kornēlijs nāca viņam pretim un, nometies pie tā kājām, pagodināja viņu.
25ጴጥሮስም በገባ ጊዜ ቆርኔሌዎስ ተገናኝቶ ከእግሩ በታች ወደቀና ሰገደለት።
26Bet Pēteris pacēla viņu, sacīdams: Celies, arī es esmu cilvēks.
26ጴጥሮስ ግን። ተነሣ፤ እኔ ራሴ ደግሞ ሰው ነኝ ብሎ አስነሣው።
27Un viņš, sarunādamies ar to, iegāja iekšā un atrada daudz atnācēju.
27ከእርሱም ጋር እየተነጋገረ ገባ፥ ብዙዎችም ተከማችተው አግኝቶ።
28Un viņš tiem sacīja: Jūs zināt, ka jūdu cilvēkiem nav atļauts biedroties un satikties ar svešinieku; bet man Dievs atklāja, ka nevienu cilvēku nevajag uzskatīt par nešķīstu vai netīru.
28አይሁዳዊ ሰው ከሌላ ወገን ጋር ይተባበር ወይም ይቃረብ ዘንድ እንዳልተፈቀደ እናንተ ታውቃላችሁ፤ ለእኔ ግን እግዚአብሔር ማንንም ሰው ርኵስና የሚያስጸይፍ ነው እንዳልል አሳየኝ፤
29Tāpēc uzaicināts es atnācu bez šaubīšanās. Es jautāju, kādā iemesla dēļ jūs mani aicinājāt?
29ስለዚህም ደግሞ ብትጠሩኝ ሳልከራከር መጣሁ። አሁንም በምን ምክንያት አስመጣችሁኝ? ብዬ እጠይቃችኋለሁ አላቸው።
30Tad Kornēlijs sacīja: Pirms četrām dienām ap šo laiku, devītajā stundā, es lūdzu Dievu savā namā un, lūk, nostājās manā priekšā vīrs spožās drēbēs un sacīja:
30ቆርኔሌዎስም እንዲህ አለው። በዚች ሰዓት የዛሬ አራት ቀን የዘጠኝ ሰዓት ጸሎት በቤቴ እጸልይ ነበር፤ እነሆም፥ የሚያንጸባርቅ ልብስ የለበሰ ሰው በፊቴ ቆመና።
31Kornēlij, tava lūgšana uzklausīta, un Dievs tavas labdarības dāvanas atminējies sava vaiga priekšā.
31ቆርኔሌዎስ ሆይ፥ በእግዚአብሔር ፊት ጸሎትህ ተሰማ ምጽዋትህም ታሰበ።
32Tāpēc sūti uz Jopi un liec ataicināt Sīmani, kas tiek saukts Pēteris; viņš viesojas ādmiņa Sīmaņa namā pie jūras.
32እንግዲህ ወደ ኢዮጴ ልከህ ጴጥሮስ የተባለውን ስምዖንን አስጠራ፤ እርሱ በቍርበት ፋቂው በስምዖን ቤት በባሕር አጠገብ እንግድነት ተቀምጦአል አለኝ።
33Tad es tūdaļ sūtīju pie tevis, un labi tu darīji atnākdams. Tagad mēs visi stāvam tavā priekšā, lai uzklausītu visu, ko Kungs tev pavēlējis.
33ስለዚህ ያን ጊዜ ወደ አንተ ላክሁ፥ አንተም በመምጣትህ መልካም አድርገሃል። እንግዲህ አንተ ከእግዚአብሔር ዘንድ የታዘዝኸውን ሁሉ እንድንሰማ እኛ ሁላችን አሁን በእግዚአብሔር ፊት በዚህ አለን።
34Bet Pēteris, atvēris savu muti, sacīja: Patiesi, es atzīstu ka Dievs nešķiro personas (5.Moz.10,17; Īj.34,19; Gudr.6,8; Rom.2,11; Gal.2,6; Ef.6,9; Kol.3,25; 1.Pēt.1,17)
34ጴጥሮስም አፉን ከፍቶ እንዲህ አለ። እግዚአብሔር ለሰው ፊት እንዳያደላ ነገር ግን በአሕዛብ ሁሉ እርሱን የሚፈራና ጽድቅን የሚያደርግ በእርሱ የተወደደ እንደ ሆነ በእውነት አስተዋልሁ።
35Bet ikvienā tautā tas, kas Viņa bīstas un taisnīgi dzīvo, ir Viņam patīkams.
36የሁሉ ጌታ በሚሆን በኢየሱስ ክርስቶስ ሰላምን እየሰበከ ይህን ቃል ወደ እስራኤል ልጆች ላከ።
36Dievs sūtīja vārdu Izraēļa bērniem, pasludinādams mieru caur Jēzu Kristu. (Viņš ir Kungs pār visiem.)
37ዮሐንስ ከሰበከው ጥምቀት በኋላ ከገሊላ ጀምሮ በይሁዳ ሁሉ የሆነውን ነገር እናንተ ታውቃላችሁ።
37Jūs zināt, kādi notikumi norisinājās visā Jūdejā, sākot ar Galileju, pēc kristības, ko sludināja Jānis.
38እግዚአብሔር የናዝሬቱን ኢየሱስን በመንፈስ ቅዱስ በኃይልም ቀባው፥ እርሱም መልካም እያደረገ ለዲያብሎስም የተገዙትን ሁሉ እየፈወሰ ዞረ፥ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ነበረና፤
38Kā Dievs ar Svēto Garu un spēku svaidīja Nācarieti Jēzu, kas staigāja, labu darīdams un dziedinādams visus velna nomāktos, jo Dievs bija ar Viņu.
39እኛም በአይሁድ አገርና በኢየሩሳሌም ባደረገው ነገር ሁሉ ምስክሮች ነን፤ እርሱንም በእንጨት ላይ ሰቅለው ገደሉት።
39Mēs esam liecinieki visam tam, ko Viņš darīja Jūdu zemē un Jeruzalemē. Viņu tie nonāvēja, piesitot krustā.
40እርሱን እግዚአብሔር በሦስተኛው ቀን አስነሣው ይገለጥም ዘንድ ሰጠው፤
40Dievs Viņu uzmodināja trešajā dienā un atļāva Viņam parādīties.
41ይኸውም ለሕዝብ ሁሉ አይደለም ነገር ግን በእግዚአብሔር አስቀድሞ የተመረጡ ምስክሮች ለሆንን ለእኛ ነው እንጂ፤ ከሙታንም ከተነሣ በኋላ ከእርሱ ጋር የበላን የጠጣንም እኛ ነን።
41Ne visai tautai, bet Dieva izredzētajiem lieciniekiem, mums, kas kopā ar Viņu ēdām un dzērām pēc augšāmcelšanās no miroņiem.
42ለሕዝብም እንድንሰብክና በሕያዋንና በሙታን ሊፈርድ በእግዚአብሔር የተወሰነ እርሱ እንደ ሆነ እንመሰክር ዘንድ አዘዘን።
42Viņš mums pavēlēja sludināt tautai un apliecināt, ka Viņš ir Dieva ieceltais soģis pār dzīvajiem un mirušajiem.
43በእርሱ የሚያምን ሁሉ በስሙ የኃጢአቱን ስርየት እንዲቀበል ነቢያት ሁሉ ይመሰክሩለታል።
43Par Viņu liecina visi pravieši, ka visi, kas uz Viņu tic, Viņa vārdā saņem grēku piedošanu.
44ጴጥሮስ ይህን ነገር ገና ሲናገር ቃሉን በሰሙት ሁሉ ላይ መንፈስ ቅዱስ ወረደ።
44Kamēr Pēteris šos vārdus runāja, nāca Svētais Gars pār visiem, kas vārdos klausījās.
45ከጴጥሮስም ጋር የመጡት ሁሉ ከተገረዙት ወገን የሆኑ ምዕመናን በአሕዛብ ላይ ደግሞ የመንፈስ ቅዱስ ስጦታ ስለ ፈሰሰ ተገረሙ፤
45Un apgraizītie ticīgie, kas atnāca kopā ar Pēteri, bija pārsteigti, ka Svētā Gara žēlastība tika izlieta arī uz pagāniem.
46በልሳኖች ሲናገሩ እግዚአብሔርንም ሲያከብሩ ሰምተዋቸዋልና።
46Jo tie dzirdēja viņus valodās runājam un Dievu augsti teicam.
47በዚያን ጊዜ ጴጥሮስ መልሶ። እነዚህ እንደ እኛ ደግሞ መንፈስ ቅዱስን የተቀበሉ እንዳይጠመቁ ውኃን ይከለክላቸው ዘንድ የሚችል ማን ነው? አለ።
47Tad Pēteris sacīja: Kas var liegt ūdeni viņu kristīšanai, kas, tāpat kā mēs, saņēmuši Svēto Garu?
48በኢየሱስ ክርስቶስ ስምም ይጠመቁ ዘንድ አዘዛቸው። ከዚህ በኋላ ጥቂት ቀን እንዲቀመጥ ለመኑት።
48Un viņš pavēlēja tos kristīt Kunga Jēzus vārdā. Tad tie lūdza viņu dažas dienas palikt pie tiem.