Latvian: New Testament

Amharic: New Testament

Acts

27

1Kad bija nolemts, ka Pāvilam jāpārceļas uz Itāliju, viņu kopā ar citiem cietumniekiem nodeva ķeizara karaspēka vienības simtniekam, vārdā Jūlijam.
1ወደ ኢጣሊያም በመርከብ እንሄድ ዘንድ በተቈረጠ ጊዜ፥ ጳውሎስንና ሌሎችን እስረኞች ከአውግስጦስ ጭፍራ ለነበረ ዩልዮስ ለሚሉት ለመቶ አለቃ አሳልፈው ሰጡአቸው።
2Iekāpuši kādā Andrumetijas kuģī, mēs aizbraucām, sākdami ceļojumu gar Āzijas piekrasti. Maķedonietis Aristarhs no Tesalonīkes bija pie mums.
2በእስያም ዳርቻ ወዳሉ ስፍራዎች ይሄድ ዘንድ ባለው በአድራሚጢስ መርከብ ገብተን ተነሣን፤ የመቄዶንያም ሰው የሆነ የተሰሎንቄው አርስጥሮኮስ ከእኛ ጋር ነበረ።
3Nākošajā dienā mēs nonācām Sidonā. Jūlijs apgājās ar Pāvilu cilvēcīgi un atļāva aiziet pie draugiem, lai tie viņu apgādātu.
3በነገውም ወደ ሲዶና ስንደርስ ዩልዮስ ለጳውሎስ ቸርነት አድርጎ እርዳታቸውን ይቀበል ዘንድ ወደ ወዳጆቹ እንዲሄድ ፈቀደለት።
4No turienes aizbraukuši, mēs braucām lejpus Kiprai, jo bija pretvējš.
4ከዚያም ተነሥተን ነፋሱ ፊት ለፊት ነበረና በቆጵሮስ ተተግነን ሄድን፤
5Pārbraukuši jūru gar Kilikiju un Pamfīliju, mēs nonācām Listrā, kas atrodas Likijā.
5በኪልቅያና በጵንፍልያም አጠገብ ያለውን ባሕር ከተሻገርን በኋላ በሉቅያ ወዳለ ወደ ሙራ ደረስን።
6Tur simtnieks, atradis kādu kuģi no Aleksandrijas, kas brauca uz Itāliju, pārvietoja mūs tanī.
6የመቶ አለቃውም በዚያ ወደ ኢጣሊያ የሚሄድ የእስክንድርያውን መርከብ አግኝቶ ወደ እርሱ አገባን።
7Daudzas dienas lēni braukdami, mēs tikko nonācām iepretim Knidai, tāpēc ka vējš mums traucēja, un braucām gar Krētu netālu no Salmones.
7ብዙ ቀንም እያዘገምን ሄደን በጭንቅ ወደ ቀኒዶስ አንጻር ደረስን፤ ነፋስም ስለ ከለከለን በቀርጤስ ተተግነን በሰልሙና አንጻር ሄድን፤
8Ar grūtībām, garām braukdami, mēs nonācām kādā vieta, ko sauc par Labo ostu. Tās tuvumā atradās Talasas pilsēta.
8በጭንቅም ጥግ ጥጉን አልፈን ለላሲያ ከተማ ወደ ቀረበች መልካም ወደብ ወደሚሉአት ስፍራ መጣን።
9Bet bija pagājis ilgs laiks, un kuģošana vairs nebija droša, jo arī gavēnis jau bija pagājis, un Pāvils brīdinājā tos,
9ብዙ ጊዜም ካለፈ በኋላ፥ የጦም ወራት አሁን አልፎ ስለ ነበረ በመርከብ ለመሄድ አሁን የሚያስፈራ ነበርና ጳውሎስ።
10Sacīdams viņiem: Vīri, es redzu, ka kuģošana sāk izvērsties briesmās un lielā postā ne tikai kravai un kuģim, bet arī mūsu dzīvībām.
10እናንተ ሰዎች ሆይ፥ ይህ ጕዞ በጥፋትና በብዙ ጕዳት እንዲሆን አያለሁ፤ ጥፋቱም በገዛ ሕይወታችን ነው እንጂ በጭነቱና በመርከቡ ብቻ አይደለም ብሎ መከራቸው።
11Bet virsnieks vairāk ticēja stūrmanim un kuģa īpašniekam nekā tam, ko sacīja Pāvils.
11የመቶ አለቃው ግን ጳውሎስ ከተናገረው ይልቅ የመርከብ መሪውንና የመርከቡን ባለቤት ያምን ነበር።
12Tā kā osta nebija piemērota pārziemošanai, daudzi nāca pie atziņas aizbraukt no turienes un, ja iespējams, nokļūt Foinīkā, lai tur pārziemotu. Tā ir Krētas osta, kas atvērta pret dienvidvakariem un ziemeļvakariem.
12ያም ወደብ ይከርሙበት ዘንድ የማይመች ስለ ሆነ፥ የሚበዙቱ ቢቻላቸው በሰሜንና በደቡብ ምዕራብ ትይዩ ወዳለው ፍንቄ ወደሚሉት ወደ ቀርጤስ ወደብ ደርሰው ይከርሙ ዘንድ ከዚያ እንዲነሡ መከሩ።
13Dienvidu vējam pūšot, viņi domāja sasniegt savu nodomu, un pacēluši enkurus, brauca gar Krētu.
13ልከኛም የደቡብ ነፋስ በነፈሰ ጊዜ፥ እንዳሰቡት የሆነላቸው መስሎአቸው ተነሡ በቀርጤስም አጠገብ ጥግ ጥጉን አለፉ።
14Bet neilgi pēc tam sacēlās pret to viesuļvētra, ko sauc par ziemeļrīteni.
14ነገር ግን እጅግ ሳይዘገይ አውራቂስ የሚሉት ዓውሎ ነፋስ ከዚያ ወረደባቸው፤
15Kuģis tika aizrauts, un tas nespēja pretoties vējam. Nododot kuģi vētras varā, mēs tikām aiznesti.
15መርከቡም ተነጥቆ ነፋሱን ሲቃወም መሄድ ስላልቻለ ለቀነው ተነዳን።
16Mēs braucām gar kādu salu, kas saucās Kauda, un mēs tikko spējām valdīt laivu.
16ቄዳ በሚሉአትም ደሴት በተተገንን ጊዜ ታንኳይቱን ለመግዛት በጭንቅ ቻልን፤
17To izvilkuši, viņi pielietoja glābšanas līdzekļus un apsēja kuģi. Bīdamies nokļūt Sirtē, viņi nolaida buras un ļāvās nest.
17ወደ ላይም ካወጡአት በኋላ መርከቡን በገመድ አስታጥቀው አጸኑ፤ ስርቲስም ወደሚሉት ወደ አሸዋ እንዳይወድቁ ፈርተው ሸራውን አውርደው እንዲሁ ተነዱ።
18Kad mūs vētra ļoti svaidīja, otrā dienā viņi nometa daļu kravas.
18ነፋሱም በርትቶ ሲያስጨንቀን በማንግሥቱ ከጭነቱ ወደ ባሕር ይጥሉ ነበር፥
19Bet trešajā dienā viņi savām rokām izmeta kuģa rīkus.
19በሦስተኛውም ቀን የመርከቡን ዕቃ በእጃችን ወረወርን።
20Kad vairākas dienas nebija redzama ne saule, ne zvaigznes un trakoja liela vētra, mums zuda katra cerība izglābties.
20ብዙ ቀንም ፀሐይን ከዋክብትንም ሳናይ ትልቅ ነፋስም ሲበረታብን ጊዜ፥ ወደ ፊት እንድናለን የማለት ተስፋ ሁሉ ተቈረጠ።
21Tā kā viņi ilgi nebija ēduši, Pāvils nostājās viņu vidū un sacīja: Vīri, jums vajadzēja mani paklausīt un neatstāt Krētu. Tad jūs izsargātos no šīm grūtībām un zaudējumiem.
21ሳይበሉም ብዙ ቀን ከቆዩ በኋላ፥ ያን ጊዜ ጳውሎስ በመካከላቸው ቆሞ እንዲህ አለ። እናንተ ሰዎች ሆይ፥ ሰምታችሁኝ በሆነ ኖሮ ከቀርጤስ እንዳትነሡ ይህንም ጥፋትና ጕዳት እንዳታገኙ ይገባችሁ ነበር።
22Tagad es jums atgādinu: nezaudējiet drosmi, jo neviens no jums bojā neies, tikai kuģis.
22አሁንም። አይዞአችሁ ብዬ እመክራችኋለሁ፤ ይህ መርከብ እንጂ ከእናንተ አንድ ነፍስ እንኳ አይጠፋምና።
23Jo šinī naktī man piestājās Dieva eņģelis, kam es piederu un kam kalpoju,
23የእርሱ የምሆንና ደግሞ የማመልከው የእግዚአብሔር መልአክ በዚች ሌሊት በአጠገቤ ቆሞ ነበርና፥ እርሱም።
24Sacīdams: Nebīsties, Pāvil, tev jāstājas ķeizara priekšā un, lūk, Dievs tev dāvājis visus, kas kopā ar tevi brauc.
24ጳውሎስ ሆይ፥ አትፍራ፤ በቄሣር ፊት ልትቆም ይገባሃል፤ እነሆም፥ እግዚአብሔር ከአንተ ጋር የሚሄዱትን ሁሉ ሰጥቶሃል አለኝ።
25Tāpēc, vīri, nezaudējiet drosmi, jo es ticu Dievam, ka tā notiks, kā man tika sacīts.
25ስለዚህ እናንተ ሰዎች ሆይ፥ አይዞአችሁ፤ እንደ ተናገረኝ እንዲሁ እንዲሆን እግዚአብሔርን አምናለሁና።
26Bet mums jānokļūst kādā salā.
26ነገር ግን ወደ አንዲት ደሴት እንድንወድቅ ያስፈልገናል።
27Bet pēc tam iestājās četrpadsmitā nakts, un mēs ap pusnakti braucām pa Adrijas jūru. Tad jūrnieki nojauta, ka tuvojamies zemei.
27በአሥራ አራተኛውም ሌሊት በአድርያ ባሕር ወዲህና ወዲያ ስንነዳ፥ መርከበኞች በእኩለ ሌሊት ወደ አንድ ምድር የቀረቡ መሰላቸው።
28Nolaiduši lodi, tie atrada divdesmit asis, bet nedaudz tālāk tie izmērīja piecpadsmit.
28መለኪያ ገመድም ቢጥሉ ሀያ በሰው ቁመት አገኙ ጥቂትም ቆይተው ሁለተኛ ቢጥሉ አሥራ አምስት በሰው ቁመት አገኙ፤
29Baidīdamies uzskriet klintīm, tie kuģa pakaļgalā izmeta četrus enkurus un gaidīja dienu austam.
29ድንጋያማም ወደ ሆነ ስፍራ እንዳይወድቁ ፈርተው፥ ከመርከቡ በስተኋላ አራት መልሕቅ አወረዱ፥ ቀንም እንዲሆን ተመኙ።
30Bet jūrnieki, nolaižot laivu jūrā, mēģināja aizbēgt no kuģa, izlikdamies, it kā viņi gribētu priekšgalā nolaist enkurus.
30መርከበኞቹም ከመርከቡ ይሸሹ ዘንድ ፈልገው ከመርከቡ በስተ ፊት መልሕቅ መጣል እንዳላቸው አመካኝተው ታንኳይቱን ወደ ባሕር ባወረዱ ጊዜ፥
31Tad Pāvils sacīja virsniekiem un kareivjiem: Ja šie kuģī nepaliek, jūs nevarat tikt izglābti.
31ጳውሎስ ለመቶ አለቃውና ለወታደሮቹ። እነዚህ በመርከቡ ካልቆዩ እናንተ ትድኑ ዘንድ አትችሉም አላቸው።
32Tad kareivji pārcirta laivas virves un ļāva tai nokrist.
32ያን ጊዜ ወታደሮቹ የታንኳይቱን ገመድ ቈርጠው ትወድቅ ዘንድ ተዉአት።
33Gaismai austot, Pāvils lūdza visus pieņemt barību, sacīdams: Šodien ir četrpadsmitā diena, kamēr jūs, nekā neēduši, gaidāt un neko neesat baudījušī.
33ቀንም ሲነጋ ጳውሎስ ምግብ ይበሉ ዘንድ ሁሉን ይለምን ነበር፥ እንዲህም አላቸው። እየጠበቃችሁ ምንም ሳትቀበሉ ጦማችሁን ከሰነበታችሁ ዛሬ አሥራ አራተኛ ቀናችሁ ነው።
34Tāpēc es jūs lūdzu pieņemt barību jūsu veselības dēļ, jo nevienam no jums ne mats no galvas nezudīs.
34ሰለዚህ ምግብ ትበሉ ዘንድ እለምናችኋለሁ፤ ይህ ለደኅንነታችሁ ይሆናልና፤ ከእናንተ ከአንዱ የራስ ጠጕር እንኳ አትጠፋምና።
35To pateicis, viņš paņēma maizi, visu priekšā pateicās Dievam un, to pārlauzis, sāka ēst.
35ይህንም ብሎ እንጀራን ይዞ በሁሉ ፊት እግዚአብሔርን አመሰገነ ቈርሶም ይበላ ዘንድ ጀመረ።
36Tad visi kļuva drošāki un sāka ēst.
36ሁለም ተጽናንተው ራሳቸው ደግሞ ምግብ ተቀበሉ።
37Pavisam kuģī mēs bijām divsimt septiņdesmit sešas dvēseles.
37በመርከቡም ያለን ሁላችን ሁለት መቶ ሰባ ስድስት ነፍስ ነበርን።
38Paēduši līdz sātam, viņi izmeta kviešus jūrā, lai atvieglotu kuģi.
38በልተውም በጠገቡ ጊዜ ስንዴውን ወደ ባሕር እየጣሉ መርከቡን አቃለሉት።
39Kad iestājās diena, viņi zemi nepazina, bet saskatīja kādu līci ar lēzenu krastu. Tanī viņi domāja, ja tas iespējams, izmest kuģi.
39በነጋም ጊዜ ምድሩን አላወቁትም፥ ነገር ግን የአሸዋ ዳር ያለውን የባሕር ስርጥ ተመለከቱ፥ ቢቻላቸውም መርከቡን ወደዚያ ይገፉ ዘንድ ቈረጡ።
40Atbrīvojuši enkurus, viņi ļāvās jūrai. Tad tie, atraisījuši stūres un pacēluši priekšējās buras pa vējam, stūrēja uz krastu.
40መልሕቆቹንም ፈትተው በባሕር ተዉአቸው፥ ያን ጊዜም የመቅዘፊያውን ማሠሪያ ፈቱት፤ ታናሹንም ሸራ ለነፋስ ከፍ አድርገው ወደ ዳር አቅንተው ይሄዱ ዘንድ ጀመሩ።
41Mēs nokļuvām joslā starp jūras ietekām, un viņi tur uzvadīja kuģi. Tā priekšgals palika nekustīgs, bet pakaļgalu jūras viļņi sadauzīja.
41ነገር ግን ሁለት ባሕር በተገናኙበት ስፍራ ወድቀው መርከቡን በዲብ ላይ ነዱ፤ በስተ ፊቱም ተተክሎ የማይነቃነቅ ሆነ፥ በስተ ኋላው ግን ከማዕበሉ ግፊያ የተነሣ ይሰበር ነበር።
42Tad kareivjiem radās nodoms apcietinātos nonāvēt, lai kāds neaizpeldētu un neizbēgtu.
42ወታደሮቹም ከእስረኞች አንድ ስንኳ ዋኝቶ እንዳያመልጥ ይገድሉአቸው ዘንድ ተማከሩ።
43Bet virsnieks, gribēdams glābt Pāvilu, neļāva tam notikt. Viņš pavēlēja tiem, kas prata peldēt, pirmajiem mesties ārā un, zemi sasniedzot, glābties.
43የመቶ አለቃው ግን ጳውሎስን ያድነው ዘንድ አስቦ ምክራቸውን ከለከለ፤ ዋና የሚያውቁትም ከመርከብ ራሳቸውን እየወረወሩ አስቀድመው ወደ ምድር ይወጡ ዘንድ፥
44Pārējos viņi novietoja: citus uz dēļiem, citus uz kuģa atliekām. Un tā notika, ka visi ļaudis nokļuva uz sauzemes.
44የቀሩትም እኵሌቶቹ በሳንቃዎች ላይ እኵሌቶቹም በመርከቡ ስባሪ ይወጡ ዘንድ አዘዘ። እንዲሁም ሁሉ በደኅና ወደ ምድር ደረሱ።