Latvian: New Testament

Amharic: New Testament

Acts

7

1Tad augstais priesteris sacīja: Vai tas tā ir?
1ሊቀ ካህናቱም። ይህ ነገር እንዲህ ነውን? አለው፤
2Viņš teica: Brāļi un tēvi, klausieties! Godības Dievs parādījās mūsu tēvam Ābrahamam, kad tas bija Mezopotāmijā, pirms viņš pārcēlās dzīvot Hāranā.
2እርሱም እንዲህ አለ። ወንድሞችና አባቶች ሆይ፥ ስሙ። የክብር አምላክ ለአባታችን ለአብርሃም በካራን ሳይቀመጥ ገና በሁለት ወንዝ መካከል ሳለ ታየና።
3Un sacīja viņam: Aizej no savas zemes un saviem radiem un ej uz zemi, ko es tev rādīšu.
3ከአገርህና ከዘመዶችህም ወጥተህ ወደማሳይህ ወደ ማንኛውም ምድር ና አለው።
4Tad viņš aizgāja no kaldejiešu zemes un dzīvoja Hāranā. No turienes, kad tā tēvs nomira, Viņš to pārcēla šinī zemē, kurā jūs tagad dzīvojat;
4በዚያን ጊዜ ከከለዳውያን አገር ወጥቶ በካራን ተቀመጠ። ከዚያም አባቱ ከሞተ በኋላ እናንተ ዛሬ ወደምትኖሩባት ወደዚች አገር አወጣው።
5Un te Viņš tam nedeva mantojumā ne pēdas platuma, bet apsolīja to dot īpašumā viņam un pēc viņa - tā pēcnācējiem, kad viņam dēla vēl nebija.
5በዚችም የእግር ጫማ ስንኳ የሚያህል ርስት አልሰጠውም፤ ነገር ግን ልጅ ሳይኖረው ለእርሱ ከእርሱም በኋላ ለዘሩ ርስት አድርጎ ይሰጠው ዘንድ ተስፋ ሰጠው።
6Tad Dievs viņam sacīja: Tavi pēcnācēji būs piedzīvotāji svešā zemē, un tos verdzinās un slikti ar tiem apiesies četri simti gadu;
6እግዚአብሔርም ዘሩ በሌላ አገር መጻተኞች እንዲሆኑ አራት መቶ ዓመትም ባሪያዎች እንዲያደርጉአቸው እንዲያስጨንቁአቸውም እንዲህ ተናገረ፤
7Un Kungs sacīja: Tautu, kurai tie vergos, es tiesāšu; un pēc tam tie izies un kalpos man šinī vietā.
7ደግሞም እግዚአብሔር። እንደ ባሪያዎች በሚገዙአቸው ሕዝብ ላይ እኔ እፈርድባቸዋለሁ፥ ከዚህም በኋላ ይወጣሉ በዚህም ስፍራ ያመልኩኛል አለ።
8Un Viņš tam deva apgraizīšanas derību; un viņš dzemdināja Īzāku un to apgraizīja astotajā dienā; un Īzāks - Jēkabu un Jēkabs - divpadsmit ciltstēvus;
8የመገረዝንም ኪዳን ሰጠው፤ እንዲሁም ይስሐቅን ወለደ በስምንተኛውም ቀን ገረዘው ይስሐቅም ያዕቆብን ያዕቆብም አሥራ ሁለቱን የአባቶችን አለቆች።
9Un ciltstēvi skaudības dēļ pārdeva Jāzepu uz Ēģipti, bet Dievs bija ar viņu.
9የአባቶችም አለቆች በዮሴፍ ቀንተው ወደ ግብፅ ሸጡት፤ እግዚአብሔርም ከእርሱ ጋር ነበረ፥
10Un Viņš to izglāba no visām tā bēdām, un deva viņam žēlastību un gudrību faraona, Ēģiptes ķēniņa, priekšā, un tas iecēla viņu par Ēģiptes un visa sava nama valdnieku.
10ከመከራውም ሁሉ አወጣው፥ በግብፅ ንጉሥ በፈርዖንም ፊት ሞገስንና ጥበብን ሰጠው፥ በግብፅና በቤቱ ሁሉ ላይም ቢትወደድ አድርጎ ሾመው።
11Tad nāca bads un lielas ciešanas pār visu Ēģipti un Kanaanu, un mūsu tēvi neatrada vairs pārtiku.
11በግብፅና በከነዓንም አገር ሁሉ ራብና ብዙ ጭንቅ መጣ፥ አባቶቻችንም ምግብን አላገኙም።
12Kad Jēkabs dzirdēja, ka Ēģiptē ir labība, viņš sūtīja mūsu tēvus pirmo reizi.
12ያዕቆብም በግብፅ እህል መኖሩን በሰማ ጊዜ በመጀመሪያ አባቶቻችንን ሰደዳቸው፤
13Bet otrreiz brāļi pazina Jāzepu, un faraonam kļuva viņa cilts zināma.
13በሁለተኛውም ዮሴፍ ለወንድሞቹ ታወቀ፥ የዮሴፍም ትውልድ በፈርዖን ዘንድ ተገለጠ።
14Tad Jāzeps sūtīja un aicināja pie sevis savu tēvu Jēkabu un visus savus radus, septiņdesmit piecas dvēseles.
14ዮሴፍም አባቱን ያዕቆብንና ሰባ አምስት ነፍስ የነበረውን ቤተ ዘመድ ሁሉ ልኮ አስጠራ።
15Un Jēkabs pārgāja uz Ēģipti, un nomira viņš un mūsu tēvi.
15ያዕቆብም ወደ ግብፅ ወረደ እርሱም ሞተ አባቶቻችንም፤
16Un tos pārveda Sihemā un guldīja kapā, ko Ābrahams, maksājot sudrabā, nopirka Sihema dēla Emmora bērniem.
16ወደ ሴኬምም አፍልሰው አብርሃም ከሴኬም አባት ከኤሞር ልጆች በብር በገዛው መቃብር ቀበሩአቸው።
17Bet kad tuvojās apsolījuma laiks, ko Dievs Ābrahamam bija solījis, tauta auga un vairojās Ēģiptē,
17እግዚአብሔርም ለአብርሃም የማለለት የተስፋው ዘመን ሲቀርብ፥ ዮሴፍን የማያውቀው ሌላ ንጉሥ በግብፅ ላይ እስኪነሣ ድረስ፥ ሕዝቡ እየተጨመሩ በግብፅ በዙ።
18Iekams Ēģiptē necēlās cits ķēniņš, kas Jāzepu nepazina.
19እርሱም ወገናችንን ተተንኵሎ ሕፃናትን በሕይወት እንዳይጠብቁ ወደ ውጭ ይጥሉ ዘንድ አድርጎ አባቶቻችንን አስጨነቀ።
19Viņš pievīla mūsu tautu un apspieda mūsu tēvus, lai tie pamestu savus bērnus, lai tie nedzīvotu.
20በዚያን ጊዜ ሙሴ ተወለደ በእግዚአብሔርም ፊት ያማረ ነበር፤ በአባቱ ቤትም ሦስት ወር አደገ፤
20Tanī laikā piedzima Mozus. Viņš bija Dievam patīkams un tika trīs mēnešus audzināts sava tēva namā.
21በተጣለም ጊዜ የፈርዖን ልጅ አነሣችው ልጅም ይሆናት ዘንድ አሳደገችው።
21Bet kad tas bija izlikts, faraona meita paņēma to un audzināja viņu sev par dēlu.
22ሙሴም የግብፆችን ጥበብ ሁሉ ተማረ፥ በቃሉና በሥራውም የበረታ ሆነ።
22Un Mozu mācīja visās ēģiptiešu gudrībās, un tas bija varens savos vārdos un darbos.
23ነገር ግን አርባ ዓመት ሲሞላው ወንድሞቹን የእስራኤልን ልጆች ይጐበኝ ዘንድ በልቡ አሰበ።
23Kad viņš kļuva četrdesmit gadus vecs, viņam ienāca prātā apmeklēt savus brāļus, Izraēļa bērnus.
24አንዱም ሲበደል አይቶ ረዳው፥ የግብፅን ሰውም መትቶ ለተገፋው ተበቀለ።
24Un viņš, ieraudzījis kādu netaisnīgi ciešam, aizstāvēja to; un viņš to, kas netaisnīgi cieta, atrieba, nosizdams ēģiptieti.
25ወንድሞቹም እግዚአብሔር በእጁ መዳንን እንዲሰጣቸው የሚያስተውሉ ይመስለው ነበር፥ እነርሱ ግን አላስተዋሉም።
25Viņš domāja, ka brāļi sapratīs, ka Dievs tos izglābis ar viņa roku; bet tie to nesaprata.
26በማግሥቱም እርስ በርሳቸው ሲጣሉ አገኛቸው፥ ሊያስታርቃቸውም ወዶ። ሰዎች ሆይ፥ እናንተስ ወንድማማች ናችሁ፤ ስለ ምን እርስ በርሳችሁ ትበዳደላላችሁ? አላቸው።
26Nākošajā dienā, kad tie ķildojās, viņš ieradās pie tiem un uzaicināja tos samierināties, sacīdams: Vīri, jūs esat brāļi, kāpēc jūs kaitējat viens otram?
27ያም ባልንጀራውን የሚበድል ግን። አንተን በእኛ ላይ ሹምና ፈራጅ እንድትሆን የሾመህ ማን ነው?
27Bet tas, kas savam tuvākajam darīja pārestību, atgrūda viņu, sacīdams: Kas tevi iecēlis mums par priekšnieku un tiesnesi?
28ወይስ ትናንትና የግብፁን ሰው እንደ ገደልኸው ልትገድለኝ ትወዳለህን? ብሎ ገፋው።
28Vai tu gribi nonāvēt tāpat, kā tu vakar nonāvēji ēģiptieti?
29ሙሴም ከዚህ ነገር የተነሣ ሸሽቶ በምድያም አገር መጻተኛ ሆኖ ኖረ፤ በዚያም ሁለት ልጆች ወለደ።
29Šo vārdu dēļ Mozus aizbēga un kļuva ienācējs Madijana zemē, kur no viņa dzima divi dēli.
30አርባ ዓመትም ሲሞላ የጌታ መልአክ በሲና ተራራ ምድረ በዳ በቍጥቋጦ መካከል በእሳት ነበልባል ታየው።
30Kad četrdesmit gadu bija pagājis, Sinaja kalna tuksnesī viņam parādījās eņģelis degošā ērkšķu krūma liesmā.
31ሙሴም አይቶ ባየው ተደነቀ፤ ሊመለከትም ሲቀርብ የጌታ ቃል። እኔ የአባቶችህ አምላክ የአብርሃም አምላክ የይስሐቅም አምላክ የያዕቆብም አምላክ ነኝ ብሎ ወደ እርሱ መጣ። ሙሴም ተንቀጥቅጦ ሊመለከት አልደፈረም።
31To redzēdams, Mozus brīnījās par šo parādību. Un kad viņš piegāja to apskatīt, Kunga balss atskanēja uz viņu, sacīdama:
33ጌታም። የቆምህባት ስፍራ የተቀደሰች ምድር ናትና የእግርህን ጫማ አውልቅ።
32Es esmu tavu tēvu Dievs, Ābrahama Dievs, Īzāka Dievs un Jēkaba Dievs. Tad Mozus, baiļu pārņemts, neuzdrošinājās vairs to uzlūkot.
34በግብፅ ያሉትን የሕዝቤን መከራ ፈጽሜ አይቼ መቃተታቸውንም ሰምቼ ላድናቸው ወረድሁ፤ አሁንም ና፥ ወደ ግብፅ እልክሃለሁ አለው።
33Bet Kungs viņam sacīja: Noauj kurpes no savām kājām, jo tā vieta, kur tu stāvi, ir svēta zeme!
35ሹምና ፈራጅ እንድትሆን የሾመህ ማን ነው? ብለው የካዱትን፥ ይህን ሙሴን በቍጥቋጦው በታየው በመልአኩ እጅ እግዚአብሔር ሹምና ቤዛ አድርጎ ላከው።
34Es redzēdams redzēju savas tautas apspiešanu Ēģiptē un dzirdēju viņas vaimanas, un atnācu to atbrīvot; bet tagad nāc, es tevi sūtīšu uz Ēģipti!
36ይህ ሰው በግብፅ ምድርና በኤርትራ ባሕር በምድረ በዳም አርባ ዓመት ድንቅና ምልክት እያደረገ አወጣቸው።
35Šo Mozu, ko tie noliedza, sacīdami: Kas tevi iecēlis mums par priekšnieku un tiesnesi? Šo Dievs sūtīja par priekšnieku un atbrīvotāju ar eņģeļa roku, kas viņam parādījās ērkšķu krūmā.
37ይህ ሰው ለእስራኤል ልጆች። እግዚአብሔር ከወንድሞቻችሁ እንደ እኔ ያለ ነቢይ ያስነሣላችኋል፤ እርሱን ስሙት ያላቸው ሙሴ ነው።
36Viņš tos izveda, darīdams brīnumus un zīmes Ēģiptes zemē, Sarkanajā jūrā un četrdesmit gadus tuksnesī.
38ይህ ሰው በሲና ተራራ ከተናገረው መልአክና ከአባቶቻችን ጋር በምድረ በዳ በማኅበሩ ውስጥ የነበረው ነው፤ ይሰጠንም ዘንድ ሕይወት ያላቸውን ቃላት ተቀበለ፤
37Šis ir tas Mozus, kas sacīja Izraēļa bērniem: Dievs cēla jums pravieti no jūsu brāļiem, tāpat kā mani. Viņu klausiet!
39ለእርሱም አባቶቻችን ሊታዘዙት አልወደዱም፤ ነገር ግን ገፉት በልባቸውም ወደ ግብፅ ተመለሱ፤
38Viņš ir tas, kas draudzes vidū tuksnesī bija kopā ar eņģeli, kas runāja viņam Sinaja kalnā, un bija pie mūsu tēviem, un saņēma dzīvības vārdus, lai tos nodotu mums.
40አሮንንም። በፊታችን የሚሄዱ አማልክት ሥራልን፤ ይህ ከግብፅ ምድር ያወጣን ሙሴ ምን እንደ ሆነ አናውቅምና አሉት።
39Mūsu tēvi negribēja viņam paklausīt, bet tie atmeta viņu un savās sirdīs atgriezās Ēģiptē,
41በዚያም ወራት ጥጃ አደረጉ ለጣዖቱም መሥዋዕት አቀረቡ፥ በእጃቸውም ሥራ ደስ አላቸው።
40Sacīdami Āronam: Darini mums dievus, kas mūs vadītu, jo mēs nezinām, kas noticis ar šo Mozu, kas izveda mūs no Ēģiptes zemes.
42እግዚአብሔር ግን ዘወር አለ የሰማይንም ጭፍራ ያመልኩ ዘንድ አሳልፎ ሰጣቸው፥ በነቢያትም መጽሐፍ። እናንተ የእስራኤል ቤት፥ አርባ ዓመት በምድረ በዳ የታረደውን ከብትና መሥዋዕትን አቀረባችሁልኝን?
41Un tanīs dienās viņi darināja teļu, nesa elkam upuri un priecājās par savu roku darbu.
43ትሰግዱላቸውም ዘንድ የሠራችኋቸውን ምስሎች እነርሱንም የሞሎክን ድንኳንና ሬምፉም የሚሉትን የአምላካችሁን ኮከብ አነሣችሁ፤ እኔም ከባቢሎን ወዲያ እሰዳችኋለሁ ተብሎ እንዲህ ተጽፎአል።
42Bet Dievs novērsās un atdeva tos debess karaspēka kalpībai, kā tas rakstīts pravieša grāmatā: Vai tu, Izraēļa nams, šajos četrdesmit gados tuksnesī man upurēji dzīvniekus un upura dāvanas? (Am.5,25)
44እንዳየው ምስል አድርጎ ይሠራት ዘንድ ሙሴን ተናግሮ እንዳዘዘው፥ የምስክር ድንኳን ከአባቶቻችን ዘንድ በምድረ በዳ ነበረች፤
43Jūs pieņēmāt Moloha telti un sava dieva Remfana zvaigzni, tēlus, ko darinājāt to pielūgšanai; un es jūs pārcelšu viņpus Babilonas. (Am.5,25-27)
45አባቶቻችንም ደግሞ በተራ ተቀብለው እግዚአብሔር በፊታቸው ያወጣቸውን የአሕዛብን አገር በያዙት ጊዜ ከኢያሱ ጋር አገቡአት፥ እስከ ዳዊት ዘመንም ድረስ ኖረች።
44Derības telts bija ar mūsu tēviem tuksnesī, kā to pavēlēja Dievs, sacīdams Mozum, lai viņš to uztaisa pēc parauga, kādu tas redzēja.
46እርሱም በእግዚአብሔር ፊት ሞገስ አግኝቶ ለያዕቆብ አምላክ ማደሪያን ያገኝ ዘንድ ለመነ።
45Mūsu tēvi, to paņēmuši, ar Jēzu ienesa pagānu daļā. Dievs tos izdzina mūsu tēvu vaiga priekšā līdz pat Dāvida dienām.
47ነገር ግን ሰሎሞን ቤት ሠራለት።
46Tas iemantoja žēlastību pie Dieva un lūdza, lai viņš atrastu mājokli Jēkaba Dievam.
48ነገር ግን ነቢዩ። ሰማይ ዙፋኔ ነው ምድርም የእግሬ መረገጫ ናት፤ ለእኔ ምን ዓይነት ቤት ትሠራላችሁ? ይላል ጌታ፥ ወይስ የማርፍበት ስፍራ ምንድር ነው? ይህንስ ሁሉ እጄ የሠራችው አይደለምን? እንዳለ፥ ልዑል የሰው እጅ በሠራችው አይኖርም።
47Tad Salomons uzcēla Viņam namu.
51እናንተ አንገተ ደንዳኖች ልባችሁና ጆሮአችሁም ያልተገረዘ፥ እናንተ ሁልጊዜ መንፈስ ቅዱስን ትቃወማላችሁ፤ አባቶቻችሁ እንደ ተቃወሙት እናንተ ደግሞ።
48Bet Visaugstākais nemājo rokām darinātos, kā to pravietis saka:
52ከነቢያትስ አባቶቻችሁ ያላሳደዱት ማን ነው? የጻድቁንም መምጣት አስቀድሞ የተናገሩትን ገደሉአቸው፤ በመላእክት ሥርዓት ሕግን ተቀብላችሁ ያልጠበቃችሁት እናንተም አሁን እርሱን አሳልፋችሁ ሰጣችሁት ገደላችሁትም።
49Debess ir mans sēdeklis, bet zeme manu kāju paklājs. Kādu namu jūs man uzcelsiet, saka Kungs, vai kur ir mana atdusas vieta?
54ይህንም በሰሙ ጊዜ በልባቸው በጣም ተቈጡ ጥርሳቸውንም አፋጩበት።
50Vai ne mana roka visu to darījusi? (Is.66,1-2)
55መንፈስ ቅዱስንም ተሞልቶ ወደ ሰማይ ትኵር ብሎ ሲመለከት የእግዚአብሔርን ክብር ኢየሱስንም በእግዚአብሔር ቀኝ ቆሞ አየና።
51Jūs, stūrgalvji, ar neapgraizītajām sirdīm un ausīm! Jūs vienmēr pretojaties Svētajam Garam: kā jūsu tēvi, tā arī jūs.
56እነሆ፥ ሰማያት ተከፍተው የሰው ልጅም በእግዚአብሔር ቀኝ ቆሞ አያለሁ አለ።
52Kuru no praviešiem jūsu tēvi nav vajājuši? Viņi nonāvēja tos, kas iepriekš pasludināja Taisnīgā atnākšanu. Viņa nodevēji un slepkavas jūs esat tagad kļuvuši;
57በታላቅ ድምፅም እየጮኹ ጆሮአቸውን ደፈኑ፥ በአንድ ልብ ሆነውም ወደ እርሱ ሮጡ፥
53Ar eņģeļu rīkojumu jūs esat bauslību saņēmuši, bet nepildījāt.
58ከከተማም ወደ ውጭ አውጥተው ወገሩት። ምስክሮችም ልብሳቸውን ሳውል በሚሉት በአንድ ጎበዝ እግር አጠገብ አኖሩ።
54To dzirdot, tie saskaitās savās sirdīs un grieza zobus uz viņu.
59እስጢፋኖስም። ጌታ ኢየሱስ ሆይ፥ ነፍሴን ተቀበል ብሎ ሲጠራ ይወግሩት ነበር።
55Bet viņš, Svētā Gara pilns, uzlūkodams debesis, redzēja Dieva godību un Jēzu stāvam pie Dieva labās rokas,
60ተንበርክኮም። ጌታ ሆይ፥ ይህን ኃጢአት አትቍጠርባቸው ብሎ በታላቅ ድምፅ ጮኸ። ይህንም ብሎ አንቀላፋ። ሳውልም በእርሱ መገደል ተስማምቶ ነበር።
56Un sacīja: Lūk, es redzu debesis atvērtas un Cilvēka Dēlu stāvam pie Dieva labās rokas.
57Bet tie, stiprā balsī kliegdami, aizbāza savas ausis un vienprātīgi uzbruka viņam.
58Un viņi akmeņiem nomētāja Stefanu, kas sauca un sacīja: Kungs Jēzu, pieņem manu garu!
60Un viņš, ceļos nometies, skaļā balsī sauca, sacīdams: Kungs, nepieskaiti tiem šo grēku! To sacījis, viņš aizmiga Kungā. Un Sauls piekrita viņa nonāvēšanai.