1Ak jūs, neprātīgie galatieši, kas jūs apmājis nepaklausīt patiesībai, jo jūsu acu priekšā ir attēlots Jēzus Kristus, it kā Viņš starp jums būtu krustā sists.
1የማታስተውሉ የገላትያ ሰዎች ሆይ፥ በዓይናችሁ ፊት ኢየሱስ ክርስቶስ እንደ ተሰቀለ ሆኖ ተሥሎ ነበር፤ ለእውነት እንዳትታዘዙ አዚም ያደረገባችሁ ማን ነው?
2Vienīgi to es gribētu no jums dabūt zināt: vai jūs Garu saņēmāt ar likuma darbiem vai ar ticības atzīšanu?
2ይህን ብቻ ከእናንተ እንድማር እወዳለሁ፤ በሕግ ሥራ ወይም ከእምነት ጋር በሆነ መስማት መንፈስን ተቀበላችሁን?
3Vai jūs esat tik neprātīgi, ka iesākuši ar Garu, tagad miesā gribat pabeigt?
3እንዲህን የማታስተውሉ ናችሁ? በመንፈስ ጀምራችሁ አሁን በሥጋ ትፈጽማላችሁን?
4Vai tik daudz jūs veltīgi esat cietuši? Taču ne veltīgi!
4በውኑ ከንቱ እንደ ሆነስ እንደዚህ ያለ መከራ በከንቱ ተቀበላችሁን?
5Vai tas, kas devis jums Garu un dara jūsos brīnumus, dara to likuma darbu dēļ, vai ticības dēļ, ko pieņēmāt?
5እንግዲህ መንፈስን የሚሰጣችሁ በእናንተም ዘንድ ተአምራት የሚያደርግ፥ በሕግ ሥራ ነውን ወይስ ከእምነት ጋር በሆነ መስማት ነው?
6Ir rakstīts: Ābrahams ticēja Dievam, un viņam to pieskaitīja attaisnošanai.
6እንዲሁ አብርሃም በእግዚአብሔር አመነና ጽድቅ ሆኖ ተቆጠረለት።
7Tātad atzīstiet, ka tie, kas ticībā dzīvo, ir Ābrahama bērni.
7እንኪያስ ከእምነት የሆኑት እነዚህ የአብርሃም ልጆች እንደ ሆኑ እወቁ።
8Bet Raksti, paredzēdami, ka Dievs ticībā attaisno tautas, Ābrahamam ir iepriekš pasludinājuši: Tevī tiks svētītas visas tautas.
8መጽሐፍም እግዚአብሔር አሕዛብን በእምነት እንዲያጸድቅ አስቀድሞ አይቶ። በአንተ አሕዛብ ሁሉ ይባረካሉ ብሎ ወንጌልን ለአብርሃም አስቀድሞ ሰበከ።
9Tātad ticīgie tiks svētīti līdz ar ticīgo Ābrahamu.
9እንደዚህ ከእምነት የሆኑት ካመነው ከአብርሃም ጋር ይባረካሉ።
10Jo visi, kas balstās uz likuma darbiem, ir zem lāsta. Jo ir rakstīts: Lai nolādēts katrs, kas nepastāv un nedara visu to, kas rakstīts likuma grāmatā.
10ከሕግ ሥራ የሆኑት ሁሉ በእርግማን በታች ናቸውና፤ በሕግ መጽሐፍ በተጻፉት ሁሉ ጸንቶ የማይኖር የማያደርግም ሁሉ የተረገመ ነው ተብሎ ተጽፎአልና።
11Bet ka likums nevienu Dieva priekšā neattaisno, par to teikts: Taisnīgais dzīvo no ticības.
11ጻድቅ በእምነት ይኖራል ተብሎአልና ማንም በእግዚአብሔር ፊት በሕግ እንዳይጸድቅ ግልጥ ነው።
12Bet likums nav no ticības, bet kas ko dara, tas tanī dzīvo. (3 Moz 18,5)
12ሕግም ከእምነት አይደለም ነገር ግን። የሚያደርገው ይኖርበታል ተብሎአል።
13Kristus mūs atpirka no likuma lāsta, pats mūsu dēļ palikdams par lāstu, jo rakstīts: Lai nolādēts katrs, kas pakārts pie koka,
13በእንጨት የሚሰቀል ሁሉ የተረገመ ነው ተብሎ ተጽፎአልና ክርስቶስ ስለ እኛ እርግማን ሆኖ ከሕግ እርግማን ዋጀን፤
14Lai Ābrahama svētība, nāktu pār tautām Kristū Jēzū, tā ka ticībā mēs saņemam Gara apsolījumu.
14የመንፈስን ተስፋ በእምነት እንድንቀበል፥ የአብርሃም በረከት ወደ አሕዛብ በኢየሱስ ክርስቶስ ይደርስላቸው ዘንድ።
15Brāļi, (runājot cilvēcīgi) taču apstiprinātu cilvēka testamentu neviens neatceļ un nepapildina.
15ወንድሞች ሆይ፥ እንደ ሰው ልማድ እላለሁ። የሰው ስንኳ ቢሆን እርግጠኛውን ኪዳን ማንም አይንቅም ወይም አይጨምርበትም።
16Ābrahamam un viņa pēcnācējam ir doti solījumi. Nav sacīts: Un pēcnācējiem, it kā daudziem, bet kā vienam: Un tavā pēcnācējā, kas ir Kristus.
16ለአብርሃምና ለዘሩም የተስፋው ቃል ተነገረ። ስለ ብዙዎች እንደሚነገር። ለዘሮቹም አይልም፤ ስለ አንድ እንደሚነገር ግን። ለዘርህም ይላል፥ እርሱም ክርስቶስ።
17Bet to es saku, ka likums, kas izdots četri simti trīsdesmit gadus vēlāk, nevar atcelt Dieva apstiprināto gribas izpausmi un iznīcināt solījumus.
17ይህንም እላለሁ፤ ከአራት መቶ ሠላሳ ዓመት በኋላ የተሰጠው ሕግ አስቀድሞ በእግዚአብሔር የተረጋገጠውን ኪዳን የተስፋውን ቃል እስኪሽር ድረስ አያፈርስም።
18Ja mantojums nāk ar likumu, tad jau ne ar solījumu, bet Ābrahamam Dievs to dāvināja ar apsolījumu.
18ርስቱ በሕግ ቢሆንስ እንግዲያስ በተስፋ ቃል አይሆንም፤ በተስፋ ቃል ግን እግዚአብሔር ለአብርሃም ሰጥቶአል።
19Kāda tad nozīme likumam? To eņģeli pavēlējuši ar starpnieka roku, tas izdots pārkāpuma dēļ, kamēr nāks Atvase, uz kuru attiecas solījumi.
19እንግዲህ ሕግ ምንድር ነው? ተስፋው የተሰጠው ዘር እስኪመጣ ድረስ በመካከለኛ እጅ በመላእክት በኩል ስለ ሕግ መተላለፍ ተጨመረ።
20Kur viens, tur starpnieka nav. Bet Dievs ir viens.
20መካከለኛውም ለአንድ ብቻ አይደለም እግዚአብሔር ግን አንድ ነው።
21Vai tad likums ir pret Dieva apsolījumiem? Nekādā ziņā! Jo ja būtu dots likums, kas spēj darīt dzīvu, tad patiesi attaisnošana nāktu ar likumu.
21እንግዲህ ሕግ የእግዚአብሔርን የተስፋ ቃል የሚቃወም ነውን? አይደለም። ሕያው ሊያደርግ የሚቻለው ሕግ ተሰጥቶ ቢሆንስ በእውነት ጽድቅ ከሕግ በሆነ ነበር፤
22Bet Raksti ir visu ieslēguši grēkā, lai apsolījums tiktu dots ticīgajiem ticībā uz Jēzu Kristu.
22ነገር ግን በኢየሱስ ክርስቶስ ከማመን የሆነው የተስፋ ቃል ለሚያምኑ ይሰጥ ዘንድ መጽሐፍ ከኃጢአት በታች ሁሉን ዘግቶታል።
23Bet pirms nāca ticība, mēs, ieslēgti zem likuma, tikām uzglabāti ticībai, kura bija jāpasludina.
23እምነትም ሳይመጣ ሊገለጥ ላለው እምነት ተዘግተን ከሕግ በታች እንጠበቅ ነበር።
24Tātad likums bija mūsu audzinātājs Kristum, lai mēs ticībā tiktu attaisnoti.
24እንደዚህ በእምነት እንጸድቅ ዘንድ ሕግ ወደ ክርስቶስ የሚያመጣ ሞግዚታችን ሆኖአል፤
25Bet mēs, atnākot ticībai, audzinātājam neesam vairs padoti.
25እምነት ግን መጥቶአልና ከእንግዲህ ወዲህ ከሞግዚት በታች አይደለንም።
26Jūs visi esat Dieva bērni ticībā uz Jēzu Kristu,
26በእምነት በኩል ሁላችሁ በክርስቶስ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጆች ናችሁና፤
27Jo visi, kas esat kristīti Kristus vārdā, esat tērpušies Kristū.
27ከክርስቶስ ጋር አንድ ትሆኑ ዘንድ የተጠመቃችሁ ሁሉ ክርስቶስን ለብሳችኋልና።
28Nav ne jūda, ne grieķa, nav verga, ne brīvā, nav ne vīrieša, ne sievietes, jo jūs visi esat viens Kristū Jēzū.
28አይሁዳዊ ወይም የግሪክ ሰው የለም፥ ባሪያ ወይም ጨዋ ሰው የለም፥ ወንድም ሴትም የለም፤ ሁላችሁ በክርስቶስ ኢየሱስ አንድ ሰው ናችሁና።
29Bet ja jūs piederat Kristum, tad jūs esat Ābrahama pēcnācēji, mantinieki saskaņā ar apsolījumu.
29እናንተም የክርስቶስ ከሆናችሁ እንኪያስ የአብርሃም ዘር እንደ ተስፋውም ቃል ወራሾች ናችሁ።