Latvian: New Testament

Amharic: New Testament

Hebrews

4

1Tā kā apsolījums ieiet Viņa mierā vēl pastāv, bīsimies, lai kāds no jums neizrādītos to nokavējis.
1እንግዲህ ወደ ዕረፍቱ ለመግባት ተስፋ ገና ቀርቶልን ከሆነ፥ ምናልባት ከእናንተ ማንም የማይበቃ መስሎ እንዳይታይ እንፍራ።
2Jo arī mums tika pasludināts tāpat kā viņiem: bet dzirdētais vārds tiem nekā nelīdzēja, tāpēc ka tie, kas dzirdēja, nesavienoja to ar ticību.
2ለእነዚያ ደግሞ እንደ ተነገረ ለእኛ የምስራች ተሰብኮልናልና፤ ዳሩ ግን የሰሙት ቃል ከሰሚዎቹ ጋር በእምነት ስላልተዋሐደ አልጠቀማቸውም።
3Jo mēs, kas esam ticējuši, ieiesim mierā, kā Viņš to teicis: Tā es zvērēju savās dusmās: tiem manā mierā neieiet, lai gan darbi pabeigti no pasaules radīšanas.
3ሥራው ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ ምንም እንኳ ቢፈጸም። እንዲህ። ወደ ዕረፍቴ አይገቡም ብዬ በቁጣዬ ማልሁ እንዳለ፥ እኛስ ያመንን ወደ ዕረፍቱ እንገባለን።
4Jo Viņš ar septīto dienu kādā vietā teicis: Un Dievs septītajā dienā atdusējās no visiem saviem darbiem.
4ስለ ሰባተኛው ቀን በአንድ ስፍራ። እግዚአብሔርም በሰባተኛው ቀን ከሥራው ሁሉ ዐረፈ ብሎአልና፤
5Bet šeit atkal: Tiem nebūs ieiet manā mierā!
5በዚህ ስፍራም ደግሞ። ወደ ዕረፍቴ አይገቡም።
6Tā kā dažiem atliek tanī vēl ieiet, bet tie, kuriem pirmajiem tas tika pasludināts, neticības dēļ neiegāja.
6እንግዲህ አንዳንዶች በዚያ እንዲገቡ ስለ ቀሩ፥ ቀድሞም የምስራች የተሰበከላቸው ባለመታዘዝ ጠንቅ ስላልገቡ።
7Viņš atkal nozīmē vienu dienu, šodien, pēc tik ilga laika caur Dāvidu runādams, kā jau iepriekš sacīts: Šodien, ja jūs Viņa balsi dzirdēsiet, nenocietiniet savas sirdis!
7ዛሬ ድምፁን ብትሰሙት ልባችሁን እልከኛ አታድርጉ በፊት እንደ ተባለ፥ ይህን ከሚያህል ዘመን በኋላ በዳዊት ሲናገር። ዛሬ ብሎ አንድ ቀን እንደ ገና ይቀጥራል።
8Jo ja Jēzus būtu ievedis tos mierā, tad Viņš nekad vairs nebūtu runājis par kādu vēlāku dienu.
8ኢያሱ አሳርፎአቸው ኖሮ ቢሆንስ፥ ከዚያ በኋላ ስለ ሌላ ቀን ባልተናገረ ነበር።
9Tātad Dieva tautai atliek vēl viena sabata atpūta.
9እንግዲያስ የሰንበት ዕረፍት ለእግዚአብሔር ሕዝብ ቀርቶላቸዋል።
10Jo kas Viņa mierā iegājis, tas arī pats atdusēsies no saviem darbiem kā Dievs no savējiem.
10ወደ ዕረፍቱ የገባ፥ እግዚአብሔር ከሥራው እንዳረፈ፥ እርሱ ደግሞ ከሥራው አርፎአልና።
11Centīsimies tāpēc ieiet šinī mierā, lai kāds neiekristu neticībā pēc tā paša parauga!
11እንግዲህ እንደዚያ እንደ አለመታዘዝ ምሳሌ ማንም እንዳይወድቅ ወደዚያ ዕረፍት ለመግባት እንትጋ።
12Jo Dieva vārds ir dzīvs un darbīgs, un asāks par katru divasmeņu zobenu. Tas spiežas cauri, kamēr pāršķir dvēseli un garu, tāpat locekļus un smadzenes. Tas ir domu un sirdsapziņas tiesnesis.
12የእግዚአብሔር ቃል ሕያው ነውና፥ የሚሠራም፥ ሁለትም አፍ ካለው ሰይፍ ሁሉ ይልቅ የተሳለ ነው፥ ነፍስንና መንፈስንም ጅማትንና ቅልጥምንም እስኪለይ ድረስ ይወጋል፥ የልብንም ስሜትና አሳብ ይመረምራል፤
13Un Viņa vaiga priekšā nav apslēpts neviens radījums, bet Viņa acīm viss ir kails un atklāts; mums jādod Viņam norēķins.
13እኛን በሚቆጣጠር በእርሱ ዓይኖቹ ፊት ሁሉ ነገር የተራቆተና የተገለጠ ነው እንጂ፥ በእርሱ ፊት የተሰወረ ፍጥረት የለም።
14Bet mums ir augstais priesteris Jēzus, Dieva Dēls, kas debesis caurstaigājis, tad turēsimies pie apliecināšanas.
14እንግዲህ በሰማያት ያለፈ ትልቅ ሊቀ ካህናት የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ስላለን፥ ጸንተን ሃይማኖታችንን እንጠብቅ።
15Jo mums nav augstā priestera, kas nespētu līdzjust mūsu vājībām, bet kas tāpat kārdināts visās lietās, tikai bez grēka.
15ከኃጢአት በቀር በነገር ሁሉ እንደ እኛ የተፈተነ ነው እንጂ፥ በድካማችን ሊራራልን የማይችል ሊቀ ካህናት የለንም።
16Tāpēc iesim ar uzticību pie želastības troņa, lai saņemtu žēlsirdību un atrastu žēlastību palīdzībai īstā laikā!
16እንግዲህ ምሕረትን እንድንቀበል በሚያስፈልገንም ጊዜ የሚረዳንን ጸጋ እንድናገኝ ወደ ጸጋው ዙፋን በእምነት እንቅረብ።