Lithuanian

Amharic: New Testament

1 Corinthians

6

1Kaip kai kurie iš jūsų, turėdami ginčų, drįsta bylinėtis vieni su kitais pas neteisiuosius, o ne pas šventuosius?
1ከእናንተ አንዱ ከባልንጀራው ጋር ሙግት ቢኖረው በቅዱሳን ፊት በመፋረድ ፋንታ በዓመፀኞች ፊት ሊፋረድ ይደፍራልን?
2Ar nežinote, kad šventieji teis pasaulį? O jeigu teisite pasaulį, tai nejaugi esate neverti išspręsti menkų bylų?
2ቅዱሳን በዓለም ላይ እንዲፈርዱ አታውቁምን? በዓለምስ ላይ ብትፈርዱ ከሁሉ ይልቅ ትንሽ ስለሚሆን ነገር ልትፈርዱ አትበቁምን?
3Ar nežinote, kad mes teisime angelus, tad juo labiau­kasdieninius dalykus?
3የትዳር ጉዳይ ይቅርና በመላእክት እንኳ እንድንፈርድ አታውቁምን?
4Taigi, kai turite bylų kasdieniais reikalais, negi savo teisėjais paskirsite neturinčius balso bažnyčioje?
4እንግዲህ ስለ ትዳር ጉዳይ የፍርድ ቤት ቢያስፈልጋችሁ በቤተ ክርስቲያን የተናቁትን ሰዎች ፈራጆች አድርጋችሁ ታስቀምጣላችሁን?
5Tai sakau, norėdamas jus sugėdinti. Nejaugi pas jus nėra nė vieno išmintingo, kuris sugebėtų išspręsti tarp brolių iškilusią bylą?
5አሳፍራችሁ ዘንድ ይህን እላለሁ። እንደዚህ ነውን? በወንድሞች መካከል ሽማግሌ ሊሆን የሚችል አንድ አስተዋይ ሰው በእናንተ ዘንድ አይገኝምን?
6Bet brolis bylinėjasi su broliu ir tai daro pas netikinčius.
6ነገር ግን ወንድም ወንድሙን ይከሳል፥ ይህም በማያምኑ ፊት ይደረጋልን?
7Ir iš viso jums didelis pažeminimas, kad tarpusavyje bylinėjatės. Ar ne geriau pakęsti skriaudą? Ar ne geriau pakęsti apgaulę?
7እንግዲህ ፈጽሞ የእርስ በርስ ሙግት እንዳለባችሁ በእናንተ ጉድለት ነው። ብትበደሉ አይሻልምን? ብትታለሉስ አይሻልምን?
8Deja, jūs patys skriaudžiate ir apgaudinėjate, ir dar brolius!
8ነገር ግን እናንተ ትበድላላችሁ ታታልሉማላችሁ፥ ያውም ወንድሞቻችሁን።
9Ar nežinote, kad neteisieji nepaveldės Dievo karalystės? Neapsigaukite! Nei ištvirkėliai, nei stabmeldžiai, nei svetimautojai, nei homoseksualistai,
9ወይስ ዓመፀኞች የእግዚአብሔርን መንግሥት እንዳይወርሱ አታውቁምን? አትሳቱ፤ ሴሰኞች ቢሆን ወይም ጣዖትን የሚያመልኩ ወይም አመንዝሮች ወይም ቀላጮች ወይም ከወንድ ጋር ዝሙት የሚሠሩ
10nei vagys, nei gobšai, nei girtuokliai, nei keikūnai, nei plėšikai nepaveldės Dievo karalystės.
10ወይም ሌቦች ወይም ገንዘብን የሚመኙ ወይም ሰካሮች ወይም ተሳዳቢዎች ወይም ነጣቂዎች የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም።
11Kai kurie iš jūsų buvote tokie, bet dabar esate nuplauti, pašventinti, išteisinti Viešpaties Jėzaus Kristaus vardu ir mūsų Dievo Dvasia.
11ከእናንተም አንዳንዶቹ እንደ እነዚህ ነበራችሁ፤ ነገር ግን በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም በአምላካችንም መንፈስ ታጥባችኋል፥ ተቀድሳችኋል፥ ጸድቃችኋል።
12Viskas man leistina, bet ne viskas naudinga. Viskas man leistina, bet aš nesiduosiu niekieno pavergiamas!
12ሁሉ ተፈቅዶልኛል፥ ሁሉ ግን አይጠቅምም። ሁሉ ተፈቅዶልኛል፥ በእኔ ላይ ግን አንድ ነገር እንኳ አይሠለጥንብኝም።
13Valgis yra pilvui ir pilvas­valgiui, bet Dievas sunaikins ir vieną, ir kitą. Tačiau kūnas skirtas ne ištvirkavimui, bet Viešpačiui, o Viešpats­kūnui.
13መብል ለሆድ ነው፥ ሆድም ለመብል ነው፤ እግዚአብሔር ግን ይህንም ያንም ያጠፋቸዋል። ሥጋ ግን ለጌታ ነው እንጂ ለዝሙት አይደለም፤ ጌታም ለሥጋ ነው፤
14Kaip Dievas prikėlė Viešpatį­prikels ir mus savo jėga.
14እግዚአብሔርም ጌታንም አስነሣ እኛንም በኃይሉ ያስነሣናል።
15Argi nežinote, kad jūsų kūnai yra Kristaus nariai? Tad nejaugi aš, ėmęs Kristaus narius, paversiu juos paleistuvės nariais? Jokiu būdu!
15ሥጋችሁ የክርስቶስ ብልቶች እንደ ሆነ አታውቁምን? እንግዲህ የክርስቶስን ብልቶች ወስጄ የጋለሞታ ብልቶች ላድርጋቸውን? አይገባም።
16Ar nežinote, kad tas, kuris susijungia su paleistuve, tampa vienas kūnas su ja? Nes “du taps,­sako Raštas,­vienu kūnu”.
16ወይስ ከጋለሞታ ጋር የሚተባበር አንድ ሥጋ እንዲሆን አታውቁምን? ሁለቱ አንድ ሥጋ ይሆናሉ ተብሎአልና።
17Taip pat, kas susijungia su Viešpačiu, tampa viena dvasia su Juo.
17ከጌታ ጋር የሚተባበር ግን አንድ መንፈስ ነው።
18Saugokitės ištvirkimo! Bet kokia kita žmogaus daroma nuodėmė nepaliečia kūno, o ištvirkėlis nusideda savo kūnui.
18ከዝሙት ሽሹ። ሰው የሚያደርገው ኃጢአት ሁሉ ከሥጋ ውጭ ነው፤ ዝሙትን የሚሠራ ግን በገዛ ሥጋው ላይ ኃጢአትን ይሠራል።
19Ar nežinote, kad jūsų kūnas yra šventykla jumyse gyvenančios Šventosios Dvasios, kurią gavote iš Dievo, ir kad jūs nebepriklausote patys sau?
19ወይስ ሥጋችሁ ከእግዚአብሔር የተቀበላችሁት በእናንተ የሚኖረው የመንፈስ ቅዱስ ቤተ መቅደስ እንደ ሆነ አታውቁምን? በዋጋ ተገዝታችኋልና ለራሳችሁ አይደላችሁም፤ ስለዚህ በሥጋችሁ እግዚአብሔርን አክብሩ።
20Jūs esate nupirkti už didelę kainą. Tad šlovinkite Dievą savo kūnu ir savo dvasia, kurie yra Dievo.