Lithuanian

Amharic: New Testament

1 Timothy

3

1Štai tikras žodis: jei kas siekia vyskupauti, trokšta gero darbo.
1ማንም ኤጲስ ቆጶስነትን ቢፈልግ መልካምን ሥራ ይመኛል የሚለው ቃል የታመነ ነው።
2O vyskupas privalo būti nepeiktinas, vienos žmonos vyras, santūrus, protingas, padorus, svetingas, sugebantis mokyti;
2እንግዲህ ኤጲስ ቆጶስ እንዲህ ሊሆን ይገባዋል፤ የማይነቀፍ፥ የአንዲት ሚስት ባል፥ ልከኛ፥ ራሱን የሚገዛ፥ እንደሚገባው የሚሰራ፥ እንግዳ ተቀባይ፥ ለማስተማር የሚበቃ፥
3ne girtuoklis, ne kivirčius, ne geidžiantis nešvaraus pelno, bet švelnus, nemėgstantis vaidytis, negodus pinigų,
3የማይሰክር፥ የማይጨቃጨቅ ነገር ግን ገር የሆነ፥ የማይከራከር፥ ገንዘብን የማይወድ፥
4geras savo namų šeimininkas, turintis klusnius ir tikrai dorus vaikus.
4ልጆቹን በጭምትነት ሁሉ እየገዛ የራሱን ቤት በመልካም የሚያስተዳድር፤
5Jei kas nesugeba šeimininkauti savo namuose, kaipgi jis rūpinsis Dievo bažnyčia?
5ሰው ግን የራሱን ቤት እንዲያስተዳድር ባያውቅ፥ የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን እንዴት ይጠብቃታል?
6Vyskupas neturi būti naujatikis, kad nepasididžiuotų ir nepakliūtų į pasmerkimą kaip velnias.
6በትዕቢት ተነፍቶ በዲያቢሎስ ፍርድ እንዳይወድቅ፥ አዲስ ክርስቲያን አይሁን።
7Be to, jam privalu turėti gerą liudijimą tarp pašalinių, kad nebūtų jam priekaištaujama ir neįkliūtų į velnio pinkles.
7በዲያቢሎስ ነቀፋና ወጥመድም እንዳይወድቅ፥ በውጭ ካሉት ሰዎች ደግሞ መልካም ምስክር ሊኖረው ይገባዋል።
8Taip pat ir diakonai privalo būti garbingi, ne dviliežuviai, ne besaikiai vyno gėrėjai, ne geidžiantys nešvaraus pelno,
8እንዲሁም ዲያቆናት ጭምቶች፥ በሁለት ቃል የማይናገሩ፥ ለብዙ ወይን ጠጅ የማይጎመጁ፥
9saugantys tikėjimo paslaptį tyroje sąžinėje.
9ነውረኛ ረብ የማይወዱ፥ በንጹሕ ሕሊና የሃይማኖትን ምሥጢር የሚይዙ ሊሆኑ ይገባቸዋል።
10Ir pirmiausia jie turi būti išbandyti, o paskui, jei pasirodys esą be kaltės, tegul diakonauja.
10እነዚህም ደግሞ አስቀድሞ ይፈተኑ፥ ከዚያም በኋላ ያለ ነቀፋ ቢሆኑ በዲቁና ሥራ ያገልግሉ።
11Jų žmonos taip pat privalo būti garbingos, ne šmeižikės, santūrios ir ištikimos visame kame.
11እንዲሁም ሴቶች ጭምቶች፥ የማያሙ፥ ልከኞች፥ በነገር ሁሉ የታመኑ ሊሆኑ ይገባቸዋል።
12Diakonai tebūna vienos žmonos vyrai, gerai prižiūrintys vaikus ir savo pačių namus.
12ዲያቆናት ልጆቻቸውንና የራሳቸውን ቤቶች በመልካም እየገዙ እያንዳንዳቸው የአንዲት ሴት ባሎች ይሁኑ።
13Gerai diakonaujantys įgyja garbingą laipsnį ir didelę tikėjimo drąsą Kristuje Jėzuje.
13በዲቁና ሥራ በመልካም ያገለገሉ ለራሳቸው ትልቅ ማዕርግና በክርስቶስ ኢየሱስ ባለው እምነት ብዙ ድፍረት ያገኛሉ።
14Aš tau rašau apie šiuos dalykus, nors tikiuosi greit atvykti pas tave.
14ፈጥኜ ወደ አንተ እንድመጣ ተስፋ አድርጌ ይህን እጽፍልሃለሁ።
15Bet jeigu užtrukčiau, noriu, kad žinotum, kaip reikia elgtis Dievo namuose, kurie yra gyvojo Dievo bažnyčia, tiesos ramstis ir pamatas.
15ብዘገይ ግን፥ በእግዚአብሔር ማደሪያ ቤት መኖር እንዴት እንደሚገባ ታውቅ ዘንድ እጽፍልሃለሁ፤ ቤቱም የእውነት ዓምድና መሠረት፥ የሕያው እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን ነው።
16Ir neginčijamai yra didelė dievotumo paslaptis: Dievas buvo apreikštas kūne, išteisintas Dvasioje, matomas angelų, paskelbtas pagonims, įtikėtas pasaulyje ir paimtas į šlovę.
16እግዚአብሔርንም የመምሰል ምሥጢር ያለ ጥርጥር ታላቅ ነው፤ በሥጋ የተገለጠ፥ በመንፈስ የጸደቀ፥ ለመላእክት የታየ፥ በአሕዛብ የተሰበከ፥ በዓለም የታመነ፥ በክብር ያረገ።