1Antiochijos bažnyčioje buvo pranašų ir mokytojų: Barnabas, Simeonas, pravarde Juodasis, Lucijus Kirėnietis, Manaenas, augęs kartu su tetrarchu Erodu, ir Saulius.
1በአንጾኪያም ባለችው ቤተ ክርስቲያን ነቢያትና መምህራን ነበሩ፤ እነርሱም በርናባስ፥ ኔጌር የተባለው ስምዖንም፥ የቀሬናው ሉክዮስም፥ የአራተኛው ክፍል ገዥ የሄሮድስም ባለምዋል ምናሔ፥ ሳውልም ነበሩ።
2Kartą, kai jie tarnavo Viešpačiui ir pasninkavo, Šventoji Dvasia pasakė: “Išskirkite man Barnabą ir Saulių darbui, kuriam Aš juos pašaukiau”.
2እነዚህም ጌታን ሲያመልኩና ሲጦሙ መንፈስ ቅዱስ። በርናባስንና ሳውልን ለጠራኋቸው ሥራ ለዩልኝ አለ።
3Tuomet jie pasninkavo ir meldėsi, ir, uždėję ant jų rankas, išleido.
3በዚያን ጊዜም ከጦሙ ከጸለዩም እጃቸውንም ከጫኑ በኋላ አሰናበቱአቸው።
4Šventosios Dvasios pasiųsti, jie nukeliavo į Seleukiją, o iš ten laivu pasiekė Kiprą.
4እነርሱም በመንፈስ ቅዱስ ተልከው ወደ ሴሌውቅያ ወረዱ፤ ከዚያም በመርከብ ወደ ቆጵሮስ ሄዱ።
5Atvykę į Salaminą, jie pamokslavo Dievo žodį žydų sinagogose. Jiems talkino Jonas.
5በስልማናም በነበሩ ጊዜ በአይሁድ ምኵራቦች የእግዚአብሔርን ቃል ሰበኩ፤ አገልጋይም ዮሐንስ ነበራቸው።
6Perėję visą salą iki Pafo, jie susitiko vieną magą, netikrą pranašą žydą, vardu Barjėzų,
6ደሴቲቱንም ሁሉ እስከ ጳፉ በዞሩ ጊዜ፥ በርያሱስ የሚሉትን ጠንቋይና ሐሰተኛ ነቢይ የሆነውን አንድ አይሁዳዊ ሰው አገኙ፤
7kuris buvo su prokonsulu Sergijumi Pauliumi, išmintingu vyru. Šis, pasikvietęs Barnabą ir Saulių, norėjo pasiklausyti Dievo žodžio.
7እርሱም አስተዋይ ሰው ከሆነው ሰርግዮስ ጳውሎስ ከሚባለው አገረ ገዥ ጋር ነበረ። ይህም በርናባስንና ሳውልን ወደ እርሱ ጠርቶ የእግዚአብሔርን ቃል ሊሰማ ፈለገ።
8Bet Elimasmagas (toks šito žodžio vertimas)jiems priešinosi, stengdamasis atitraukti prokonsulą nuo tikėjimo.
8ጠንቋዩ ግን ኤልማስ፥ ስሙ እንዲሁ ይተረጐማልና፥ አገረ ገዡን ከማመን ሊያጣምም ፈልጎ ተቃወማቸው።
9Tada Saulius, kitaip vadinamas Pauliumi, Šventosios Dvasios kupinas, įdėmiai pažvelgė į jį
9ጳውሎስ የተባለው ሳውል ግን መንፈስ ቅዱስን ተሞልቶ ትኵር ብሎ ሲመለከተው።
10ir tarė: “Ak tu, visokių klastų bei piktybių pilnas velnio vaike! Tu, teisumo prieše! Ar nesiliausi kraipęs tiesių Viešpaties kelių?
10አንተ ተንኰል ሁሉ ክፋትም ሁሉ የሞላብህ፥ የዲያብሎስ ልጅ፥ የጽድቅም ሁሉ ጠላት፥ የቀናውን የጌታን መንገድ ከማጣመም አታርፍምን?
11Dabar štai tave ištiks Viešpaties ranka: tu tapsi aklas ir kurį laiką neregėsi saulės”. Ir tučtuojau užgulė jį migla ir tamsa, ir jis ėmė graibytis aplink, ieškodamas, kas jam ištiestų ranką.
11አሁንም፥ እነሆ፥ የጌታ እጅ በአንተ ላይ ናት፥ ዕውርም ትሆናለህ እስከ ጊዜውም ፀሐይን አታይም አለው። ያን ጊዜም ጭጋግና ጨለማ ወደቀበት፥ በእጁም የሚመራውን እየዞረ ፈለገ።
12Tai pamatęs, prokonsulas įtikėjo, apstulbintas Viešpaties mokslo.
12በዚያን ጊዜ አገረ ገዡ የተደረገውን ባየ ጊዜ ከጌታ ትምህርት የተነሣ ተገርሞ አመነ።
13Išplaukę iš Pafo, Paulius ir jo palydovai atvyko į Pergę, Pamfilijoje. Čia Jonas pasitraukė nuo jų ir sugrįžo į Jeruzalę.
13ጳውሎስም ከጓደኞቹ ጋር ከጳፉ ተነሥቶ የጵንፍልያ ወደምትሆን ወደ ጴርጌን መጣ፤ ዮሐንስም ከእነርሱ ተለይቶ ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሰ።
14O jie, išvykę iš Pergės, atkeliavo į Pisidijos Antiochiją. Sabato dieną nuėjo į sinagogą ir ten susėdo.
14እነርሱ ግን ከጴርጌን አልፈው የጲስድያ ወደምትሆን ወደ አንጾኪያ ደረሱ፤ በሰንበትም ቀን ወደ ምኵራብ ገብተው ተቀመጡ።
15Po Įstatymo ir Pranašų skaitymo sinagogos vadovai kreipėsi į juos: “Vyrai broliai, jei turite paskatinimo žodį tautiečiams, tarkite!”
15ሕግና ነቢያትም ከተነበቡ በኋላ የምኵራቡ አለቆች። ወንድሞች ሆይ፥ ሕዝብን የሚመክር ቃል እንዳላችሁ ተናገሩ ብለው ላኩባቸው።
16Tada Paulius atsistojo ir, davęs ranka ženklą nutilti, prabilo: “Izraelio vyrai ir Dievo bijantys žmonės, paklausykite!
16ጳውሎስም ተነሣና በእጁ ጠቅሶ እንዲህ አለ። የእስራኤል ሰዎችና እግዚአብሔርን የምትፈሩት ሆይ፥ ስሙ።
17Šios Izraelio tautos Dievas išsirinko mūsų tėvus, išaukštino juos, gyvenančius kaip ateivius Egipto šalyje, ir iškelta ranka išvedė juos iš Egipto.
17የዚህ የእስራኤል ሕዝብ አምላክ አባቶቻችንን መርጦ በግብፅ አገር በእንግድነት ሳሉ ሕዝቡን ከፍ ከፍ አደረጋቸው፥ ከፍ ባለችውም ክንዱ ከዚያ አወጣቸው።
18Apie keturiasdešimt metų Jis pakentė jų elgesį dykumoje,
18በበረሀም አርባ ዓመት ያህል መገባቸው።
19paskui, išnaikinęs septynias tautas Kanaane, išdalino jiems anų žemę.
19በከነዓንም አገር ሰባት አሕዛብን አጥፍቶ ምድራቸውን አወረሳቸው።
20Po to per keturis šimtus penkiasdešimt metų davė teisėjus iki pranašo Samuelio.
20ከዚህም በኋላ እስከ ነቢዩ እስከ ሳሙኤል ድረስ አራት መቶ አምሳ ዓመት ያህል መሳፍንትን ሰጣቸው።
21Tuo laiku jie ėmė prašyti karaliaus, ir Dievas jiems davė Saulių, Kišo sūnų, Benjamino giminės vyrą, keturiasdešimčiai metų.
21ከዚያም ወዲያ ንጉሥን ያነግሥላቸው ዘንድ ለመኑ፥ እግዚአብሔርም ከብንያም ወገን የሚሆን ሰው የቂስን ልጅ ሳኦልን አርባ ዓመት ሰጣቸው፤
22Pašalinęs jį, Jis pakėlė jiems karaliumi Dovydą, apie kurį liudydamas pasakė: ‘Radau Dovydą, Jesės sūnų, vyrą pagal savo širdį, kuris įvykdys visus mano norus’.
22እርሱንም ከሻረው በኋላ ዳዊትን በእነርሱ ላይ እንዲነግሥ አስነሣው፥ ሲመሰክርለትም። እንደ ልቤ የሆነ ሰው ፈቃዴንም ሁሉ የሚያደርግ የእሴይን ልጅ ዳዊትን አገኘሁ አለ።
23Iš jo palikuonių, kaip buvo žadėjęs, Dievas iškėlė Izraeliui Gelbėtoją Jėzų.
23ከዚህም ሰው ዘር እግዚአብሔር እንደ ተስፋው ቃል ለእስራኤል መድኃኒትን እርሱም ኢየሱስን አመጣ።
24Prieš Jam ateinant, Jonas skelbė atgailos krikštą visai Izraelio tautai.
24ከመምጣቱ በፊት ዮሐንስ አስቀድሞ ለእስራኤል ሕዝብ ሁሉ የንስሐን ጥምቀት ሰብኮ ነበር።
25Baigdamas gyvenimo kelią, Jonas pasakė: ‘Kuo jūs mane laikote? Aš nesu Jis. Bet štai po manęs ateina Tas, kuriam aš nevertas atrišti kojų apavo’.
25ዮሐንስም ሩጫውን ሲፈጽም ሳለ። እኔ ማን እንደ ሆንሁ ታስባላችሁ? እኔስ እርሱን አይደለሁም፤ ነገር ግን እነሆ፥ የእግሩን ጫማ እፈታ ዘንድ ከማይገባኝ ከእኔ በኋላ ይመጣል ይል ነበር።
26Vyrai broliai, Abraomo giminės sūnūs ir čia esantys Dievo bijantys žmonės! Tai jums atsiųstas šis išgelbėjimo žodis.
26እናንተ ወንድሞቻችን፥ የአብርሃም ዘር ልጆች ከእናንተ መካከልም እግዚአብሔርን የምትፈሩ ሆይ፥ ለእናንተ የዚህ የመዳን ቃል ተላከ።
27Nes Jeruzalės gyventojai ir jų vyresnieji nepažino Jo ir pasmerkdami įvykdė pranašų žodžius, skaitomus kiekvieną sabatą.
27በኢየሩሳሌም የሚኖሩ ሰዎችና አለቆቻቸው እርሱንና በየሰንበቱ የሚነበቡትን የነቢያትን ድምፆች ስላላወቁ በፍርዳቸው ፈጽመዋልና፤
28Nors nerado Jame jokios mirties vertos kaltės, jie reikalavo iš Piloto, kad Jis būtų nužudytas.
28ለሞትም የሚያደርስ ምክንያት አንድ ስንኳ ባያገኙበት፥ ይገድለው ዘንድ ጲላጦስን ለመኑት፤
29Išpildę visa, kas buvo apie Jį parašyta, nuėmė Jį nuo medžio ir paguldė į kapą.
29ስለ እርሱም የተጻፈውን ሁሉ በፈጸሙ ጊዜ ከእንጨት አውርደው በመቃብር አኖሩት።
30Bet Dievas Jį prikėlė iš numirusių.
30እግዚአብሔር ግን ከሙታን አስነሣው፤
31Jis per daugelį dienų rodėsi tiems, kurie buvo su Juo atėję iš Galilėjos į Jeruzalę. Jie yra Jo liudytojai žmonėms.
31በሕዝብም ዘንድ ምስክሮቹ ለሆኑት ከእርሱ ጋር ከገሊላ ወደ ኢየሩሳሌም ለወጡት ብዙ ቀን ታያቸው።
32Ir mes jums skelbiame Gerąją naujieną: tėvams duotąjį pažadą
32እኛም ለአባቶች የተሰጠውን ተስፋ የምስራቹን ለእናንተ እንሰብካለን፤
33Dievas įvykdė mums, jų vaikams, prikeldamas Jėzų, kaip ir parašyta antroje psalmėje: ‘Tu esi mano Sūnus, šiandien Aš pagimdžiau Tave!’
33ይህን ተስፋ እግዚአብሔር በሁለተኛው መዝሙር ደግሞ። አንተ ልጄ ነህ እኔ ዛሬ ወለድሁህ ተብሎ እንደ ተጻፈ፥ ኢየሱስን አስነሥቶ ለእኛ ለልጆቻቸው ፈጽሞአልና።
34O kad Jį prikėlė iš numirusių ir kad Jis neturėjo supūti, Dievas buvo taip nusakęs: ‘Aš ištesėsiu šventus bei tikrus pažadus Dovydui’.
34እንደገናም ወደ መበስበስ እንዳይመለስ ከሙታን እንደ አስነሣው፥ እንዲህ። የታመነውን የዳዊትን ቅዱስ ተስፋ እሰጣችኋለሁ ብሎአል።
35Todėl ir kitoje vietoje sakoma: ‘Tu neleisi savo Šventajam matyti supuvimo’.
35ደግሞ በሌላ ስፍራ። ቅዱስህን መበስበስን ያይ ዘንድ አትሰጠውም ይላልና።
36Juk Dovydas, patarnavęs savajai kartai pagal Dievo valią, užmigo, buvo palaidotas prie savo tėvų ir supuvo.
36ዳዊትም በራሱ ዘመን የእግዚአብሔርን አሳብ ካገለገለ በኋላ አንቀላፋ፥ ከአባቶቹም ጋር ተጨምሮ መበስበስን አየ፤
37O Tas, kurį Dievas prikėlė, nesupuvo.
37ይህ እግዚአብሔር ያስነሣው ግን መበስበስን አላየም።
38Taigi tebūnie jums žinoma, vyrai broliai, kad per Jį jums skelbiamas nuodėmių atleidimas.
38እንግዲህ ወንድሞች ሆይ፥ በእርሱ በኩል የኃጢአት ስርየት እንዲነገርላችሁ፥ በሙሴም ሕግ ትጸድቁበት ዘንድ ከማይቻላችሁ ሁሉ ያመነ ሁሉ በእርሱ እንዲጸድቅ በእናንተ ዘንድ የታወቀ ይሁን።
39Ir kiekvienas, kuris tiki, išteisinamas Juo nuo viso to, nuo ko nepajėgė jūsų išteisinti Mozės Įstatymas.
40እንግዲህ። እናንተ የምትንቁ፥ እዩ ተደነቁም ጥፉም አንድ ስንኳ ቢተርክላችሁ የማታምኑትን ሥራ በዘመናችሁ እኔ እሠራለሁና ተብሎ በነቢያት የተነገረው እንዳይደርስባችሁ ተጠንቀቁ።
40Tad saugokitės, kad jums nepritaptų, kas pasakyta Pranašuose:
42በወጡም ጊዜ ይህን ነገር በሚመጣው ሰንበት ይነግሩአቸው ዘንድ ለመኑአቸው።
41‘Žiūrėkite, niekintojai, stebėkitės ir pranykite! Nes Aš darau darbą jūsų dienomis, darbą, kuriuo nepatikėsite, jei kas jums pasakos’ ”.
43ጉባኤውም ከተፈታ በኋላ ከአይሁድና ወደ ይሁዲነት ገብተው ከሚያመልኩ ብዙዎች ጳውሎስንና በርናባስን ተከተሉአቸው፥ እነርሱም ሲነግሩአቸው በእግዚአብሔር ጸጋ ጸንተው እንዲኖሩ አስረዱአቸው።
42Žydams išeinant iš sinagogos, pagonys prašė, kad ir kitą sabatą būtų kalbama apie tuos dalykus.
44በሁለተኛውም ሰንበት ከጥቂቶቹ በቀር የከተማው ሰው ሁሉ የእግዚአብሔርን ቃል ይሰሙ ዘንድ ተሰበሰቡ።
43Sinagogos susirinkimui pasibaigus, daugelis žydų ir pamaldžių prozelitų sekė Paulių ir Barnabą, kurie, kalbėdami jiems, įtikinėjo pasilikti Dievo malonėje.
45አይሁድም ብዙ ሕዝብ ባዩ ጊዜ ቅንዓት ሞላባቸው፥ እየተሳደቡም ጳውሎስ የተናገረውን ቃል ተቃወሙ።
44Kitą sabatą beveik visas miestas susirinko pasiklausyti Dievo žodžio.
46ጳውሎስና በርናባስም ገልጠው። የእግዚአብሔር ቃል አስቀድሞ ለእናንተ ይነገር ዘንድ ያስፈልጋል፤ ከገፋችሁትና የዘላለም ሕይወት እንዳይገባችሁ በራሳችሁ ከፈረዳችሁ ግን፥ እነሆ፥ ወደ አሕዛብ ዘወር እንላለን።
45Išvydusius tokias minias žydus apėmė pavydas, ir jie piktžodžiaudami ėmė prieštarauti tam, ką kalbėjo Paulius.
47እንዲሁ ጌታ። እስከ ምድር ዳርቻ ድረስ ለማዳን ትሆን ዘንድ ለአሕዛብ ብርሃን አድርጌሃለሁ ብሎ አዞናልና አሉ።
46Bet Paulius ir Barnabas drąsiai pasakė: “Pirmiausia jums turėjo būti skelbiamas Dievo žodis. Bet kadangi jūs Jį atmetate ir patys laikote save nevertais amžinojo gyvenimo, tai štai mes kreipiamės į pagonis.
48አሕዛብም ሰምተው ደስ አላቸው የእግዚአብሔርንም ቃል አከበሩ፥ ለዘላለም ሕይወትም የተዘጋጁ ሁሉ አመኑ፤
47Nes taip mums liepė Viešpats: ‘Paskyriau Tave, kad būtum šviesa pagonims, kad būtumei išgelbėjimu iki pat žemės pakraščių’ ”.
49የጌታም ቃል በአገሩ ሁሉ ተስፋፋ።
48Tai girdėdami, pagonys džiaugėsi ir šlovino Viešpaties žodį; ir įtikėjo visi skirtieji amžinajam gyvenimui.
50አይሁድ ግን የሚያመልኩትን የከበሩትንም ሴቶችና የከተማውን መኳንንት አወኩ፥ በጳውሎስና በበርናባስም ላይ ስደትን አስነሥተው ከአገራቸው አወጡአቸው።
49Ir Viešpaties žodis pasklido po visą kraštą.
51እነርሱ ግን የእግራቸውን ትቢያ አራግፈውባቸው ወደ ኢቆንዮን መጡ።
50Bet žydai, sukurstę pamaldžias bei gerbiamas moteris ir įtakingus miesto piliečius, sukėlė Pauliaus ir Barnabo persekiojimą ir išvijo juos iš savo žemių.
52በደቀ መዛሙርትም ደስታና መንፈስ ቅዱስ ሞላባቸው።
51O tie, nusikratę prieš juos nuo kojų dulkes, atvyko į Ikonijų.
52Mokiniai buvo pilni džiaugsmo ir Šventosios Dvasios.