1Apolui būnant Korinte, Paulius, perėjęs aukštutines sritis, atvyko į Efezą. Užtikęs ten kelis mokinius,
1አጵሎስም በቆሮንቶስ ሳለ ጳውሎስ በላይኛው አገር አልፎ ወደ ኤፌሶን መጣ፥
2paklausė: “Ar įtikėję gavote Šventąją Dvasią?” Jie atsakė: “Mes nė girdėti negirdėjome, kad yra Šventoji Dvasia”.
2አንዳንድ ደቀ መዛሙርትንም አገኘ። ባመናችሁ ጊዜ መንፈስ ቅዱስን ተቀበላችሁን? አላቸው። እነርሱም። አልተቀበልንም መንፈስ ቅዱስ እንዳለ ስንኳ አልሰማንም አሉት።
3Jis klausė toliau: “Kokiu tad krikštu jūs buvote pakrikštyti?” Jie atsakė: “Jono krikštu”.
3እንኪያ በምን ተጠመቃችሁ? አላቸው። እነርሱም። በዮሐንስ ጥምቀት አሉት።
4Tada Paulius tarė: “Jonas krikštijo atgailos krikštu, ragindamas žmones tikėti Tą, kuris ateis po jo, būtent Kristų Jėzų”.
4ጳውሎስም። ዮሐንስስ ከእርሱ በኋላ በሚመጣው በኢየሱስ ክርስቶስ ያምኑ ዘንድ ለሕዝብ እየተናገረ በንስሐ ጥምቀት አጠመቀ አላቸው።
5Tai išgirdę, jie buvo pakrikštyti Viešpaties Jėzaus vardu.
5ይህንም በሰሙ ጊዜ በጌታ በኢየሱስ ስም ተጠመቁ፤
6Kai Paulius jiems uždėjo rankas, ant jų nužengė Šventoji Dvasia ir jie ėmė kalbėti kalbomis ir pranašauti.
6ጳውሎስም እጁን በጫነባቸው ጊዜ መንፈስ ቅዱስ ወረደባቸው በልሳኖችም ተናገሩ፥ ትንቢትም ተናገሩ።
7Iš viso jų buvo apie dvylika vyrų.
7ሰዎቹም ሁሉ አሥራ ሁለት ያህሉ ነበር።
8Paulius nuėjo į sinagogą ir ten per tris mėnesius drąsiai kalbėjo, įtikinėdamas ir aiškindamas apie Dievo karalystę.
8ወደ ምኵራብም ገብቶ ስለ እግዚአብሔር መንግሥት እየተነጋገረና እያስረዳቸው ሦስት ወር ያህል በግልጥ ይናገር ነበር።
9Kai kurie užkietėjo ir netikėjo, piktžodžiaudami tam Keliui daugumos akyse, tad Paulius pasitraukė nuo jų, atskyrė mokinius ir kasdien juos mokė Tirano mokykloje.
9አንዳንዶች ግን እልከኞች ሆነው በሕዝብ ፊት መንገዱን እየሰደቡ ባላመኑ ጊዜ፥ ከእነርሱ ርቆ ደቀ መዛሙርትን ለየ፥ ጢራኖስም በሚሉት በትምህርት ቤት ዕለት ዕለት ይነጋገር ነበር።
10Tai truko dvejus metus, ir visi Azijos gyventojai, tiek žydai, tiek graikai, išgirdo Viešpaties Jėzaus žodį.
10በእስያም የኖሩት ሁሉ አይሁድም የግሪክ ሰዎችም የጌታን ቃል እስኪሰሙ ድረስ ሁለት ዓመት ያህል እንዲህ ሆነ።
11Pauliaus rankomis Dievas darė ypatingų stebuklų.
11እግዚአብሔርም በጳውሎስ እጅ የሚያስገርም ተአምራት ያደርግ ነበር፤ ስለዚህም ከአካሉ ጨርቅ ወይም ልብስ ወደ ድውዮች ይወስዱ ነበር፥
12Žmonės net dėdavo ligoniams jo kūną lietusias skepetėles bei prijuostes, ir nuo jų pasitraukdavo ligos, išeidavo piktosios dvasios.
12ደዌያቸውም ይለቃቸው ነበር ክፉዎች መናፍስትም ይወጡ ነበር።
13Panašiai ir kai kurie keliaujantys žydų egzorcistai mėgino turėjusiems piktųjų dvasių prišaukti Viešpaties Jėzaus vardą, sakydami: “Mes jus saikdiname Jėzaus vardu, kurį skelbia Paulius”.
13አጋንንትንም እያወጡ ይዞሩ ከነበሩት አይሁድ አንዳንዶች። ጳውሎስ በሚሰብከው በኢየሱስ እናምላችኋለን እያሉ ክፉዎች መናፍስት ባሉባቸው ላይ የጌታን የኢየሱስን ስም ይጠሩባቸው ዘንድ ሞከሩ።
14Taip darė vieno žydų vyresniojo kunigo Skėvo septyni sūnūs.
14የካህናትም አለቃ ለሆነ አስቄዋ ለሚሉት ለአንድ አይሁዳዊ ይህን ያደረጉ ሰባት ልጆች ነበሩት።
15Bet piktoji dvasia jiems atsakė: “Pažįstu Jėzų ir žinau Paulių. O kas jūs esate?”
15ክፉው መንፈስ ግን መልሶ። ኢየሱስንስ አውቀዋለሁ ጳውሎስንም አውቀዋለሁ፤ እናንተሳ እነማን ናችሁ? አላቸው።
16Ir žmogus, turįs piktąją dvasią, užpuolė juos ir nugalėjo su tokia jėga, kad jie nuogi ir sužaloti išbėgo iš anų namų.
16ክፉው መንፈስም ያለበት ሰው ዘለለባቸው ቆስለውም ከዚያ ቤት ዕራቁታቸውን እስኪሸሹ ድረስ በረታባቸው አሸነፋቸውም።
17Apie tai sužinojo visi žydai ir graikai, gyvenantys Efeze. Visus apėmė baimė, o Viešpaties Jėzaus vardas buvo išaukštintas.
17ይህም በኤፌሶን በሚኖሩት ሁሉ በአይሁድና በግሪክ ሰዎች ዘንድ የታወቀ ሆነ፥ በሁላቸውም ላይ ፍርሃት ወደቀባቸው፥ የጌታም የኢየሱስ ስም ተከበረ፤
18Daug įtikėjusiųjų atėję išpažindavo ir pasisakydavo, ką buvo darę.
18አምነውም ከነበሩት እጅግ ሰዎች ያደረጉትን እየተናዘዙና እየተናገሩ ይመጡ ነበር።
19Daugelis, užsiiminėjusių magija, sunešė savo knygas ir visų akyse sudegino. Apskaičiuota, kad jos buvo vertos penkiasdešimties tūkstančių sidabro drachmų.
19ከአስማተኞችም ብዙዎቹ መጽሐፋቸውን ሰብስበው በሰው ሁሉ ፊት አቃጠሉት፤ ዋጋውም ቢታሰብ አምሳ ሺህ ብር ሆኖ ተገኘ።
20Šitaip galingai Viešpaties žodis plito ir ėmė viršų.
20እንዲህም የጌታ ቃል በኃይል ያድግና ያሸንፍ ነበር።
21Atlikęs tuos darbus, Paulius dvasioje nusprendė keliauti per Makedoniją ir Achają į Jeruzalę. “Pabuvęs ten,sakė jis,turiu pamatyti ir Romą”.
21ይህም በተፈጸመ ጊዜ ጳውሎስ። ወደዚያ ደርሼ ሮሜን ደግሞ አይ ዘንድ ይገባኛል ብሎ በመቄዶንያና በአካይያ አልፎ ወደ ኢየሩሳሌም እንዲሄድ በመንፈስ አሰበ።
22Jis nusiuntė į Makedoniją du savo pagalbininkus, Timotiejų ir Erastą, o pats kurį laiką pasiliko Azijoje.
22ከሚያገለግሉትም ሁለቱን ጢሞቴዎስንና ኤርስጦንን ወደ መቄዶንያ ልኮ ራሱ በእስያ ጥቂት ቀን ቆየ።
23Tuo metu kilo nemažas sąmyšis dėl Kelio.
23በዚያም ጊዜ ስለዚህ መንገድ ብዙ ሁከት ሆነ።
24Vienas sidabrakalys, vardu Demetrijas, gaminęs sidabrines Artemidės šventyklos miniatiūras ir duodavęs gerai uždirbti amatininkams,
24ብር ሠሪ የሆነ ድሜጥሮስ የሚሉት አንድ ሰው የአርጤምስን ቤተ መቅደስ ምስሎች በብር እየሠራ ለአንጥረኞች እጅግ ትርፍ ያገኝ ነበርና፤
25susivadino juos bei kitus to amato darbininkus ir kalbėjo: “Vyrai, jūs žinote, kad šiuo amatu remiasi mūsų gerovė.
25እነዚህንም ይህንም የሚመስለውን ሥራ የሠሩትን ሰብስቦ እንዲህ አላቸው። ሰዎች ሆይ፥ ትርፋችን በዚህ ሥራ እንደ ሆነ ታውቃላችሁ።
26Bet jūs matote ir girdite, kad tas Paulius ne tik Efeze, bet ir beveik visoje Azijoje įtikino ir nukreipė į šalį daug žmonių, tvirtindamas, esą tai ne dievai, kurie pagaminami žmonių rankomis.
26ይህም ጳውሎስ። በእጅ የተሠሩቱ አማልክት አይደሉም ብሎ፥ በኤፌሶን ብቻ ሳይሆን ከጥቂት ክፍል በቀር በእስያ ሁሉ ብዙ ሕዝብን እንደ አስረዳና እንደ አሳተ አይታችኋል ሰምታችሁማል።
27Gresia pavojus, kad ne tik nusmuks mūsų amatas, bet kad bus paniekinta didžiosios deivės Artemidės šventykla ir žlugs didybė tos, kurią garbina visa Azija ir visas pasaulis”.
27ሥራችንም እንዲናቅ ብቻ አይደለም፥ እስያ ሁሉ ዓለሙም የሚያመልካት የታላቂቱ አምላክ የአርጤምስ መቅደስ ምናምን ሆኖ እንዲቆጠር እንጂ፥ ታላቅነትዋም ደግሞ እንዳይሻር ያስፈራል።
28Tai išgirdę, jie labai įniršo ir ėmė šaukti: “Didi efeziečių Artemidė!”
28ይህንም በሰሙ ጊዜ ቍጣ ሞላባቸው። የኤፌሶን አርጤምስ ታላቅ ናት እያሉም ጮኹ።
29Sąmyšis apėmė visą miestą, ir jie, pagriebę Pauliaus palydovus, makedoniečius Gajų ir Aristarchą, visi kaip vienas pasileido bėgti į teatrą.
29ከተማውም በሙሉው ተደባለቀ፥ የመቄዶንያም ሰዎች የጳውሎስን ጓደኞች ጋይዮስንና አርስጥሮኮስን ከእነርሱ ጋር ነጥቀው በአንድ ልብ ሆነው ወደ ጨዋታ ስፍራ ሮጡ።
30Pauliui panorus įsimaišyti į minią, mokiniai jo neleido.
30ጳውሎስም ወደ ሕዝቡ ይገባ ዘንድ በፈቀደ ጊዜ ደቀ መዛሙርት ከለከሉት።
31Taip pat ir keli jo bičiuliai, Azijos valdininkai, per kitus prašė, kad jis neitų į teatrą.
31ከእስያም አለቆች ወዳጆቹ የሆኑት አንዳንዶች ደግሞ ወደ እርሱ ልከው ወደ ጨዋታ ስፍራ ራሱን እንዳይሰጥ ለመኑት።
32O ten vieni rėkavo vienaip, kitikitaip. Susirinkimas buvo toks pakrikęs, jog daugumas net nežinojo, kuriam galui susirinkta.
32ወዲያና ወዲህም እያሉ ይጮኹ ነበር፤ በጉባኤው ድብልቅልቅ ሆኖ የሚበልጡት ስንኳ ስለ ምን እንደተሰበሰቡ አላወቁም ነበርና።
33Iš minios ištempė Aleksandrą, kurį žydai stūmė į priekį. Aleksandras, pamojęs ranka, norėjo pasiaiškinti miniai.
33አይሁድም ሲያቀርቡት፥ እስክንድሮስን ከሕዝቡ መካከል ወደ ፊት ገፉት፤ እስክንድሮስም በእጁ ጠቅሶ በሕዝብ ፊት እንዲምዋገትላቸው ወደደ።
34Bet, pažinę jį esant žydą, visi vienu balsu ėmė rėkti ir kokias dvi valandas šūkavo: “Didi efeziečių Artemidė!”
34አይሁዳዊ ግን እንደ ሆነ ባወቁ ጊዜ፥ ሁሉ በአንድ ድምፅ። የኤፌሶን አርጤምስ ታላቅ ናት እያሉ ሁለት ሰዓት ያህል ጮኹ።
35Galiausiai miesto raštininkas, nuraminęs minią, pasakė: “Efezo vyrai! Kur rasi žmogų, kuris nežinotų, jog efeziečių miestas garbina didžiąją deivę Artemidę ir iš dangaus nukritusią jos statulą?!
35የከተማይቱም ጸሐፊ ሕዝቡን ጸጥ አሰኝቶ እንዲህ አለ። የኤፌሶን ሰዎች ሆይ፥ የኤፌሶን ከተማ ለታላቂቱ አርጤምስ ከሰማይም ለወረደው ጣዖትዋ የመቅደስ ጠባቂ መሆንዋን የማያውቅ ሰው ማን ነው?
36Šito niekas negali paneigti. Taigi nusiraminkite ir nieko galvotrūkčiais nedarykite.
36ይህንም የሚክደው ከሌለ፥ ጸጥ እንድትሉና አንዳች በችኮላ እንዳታደርጉ ይገባል።
37Jūs atitempėte čionai šiuos vyrus, kurie nėra nei šventyklos vagys, nei piktžodžiautojai mūsų deivei.
37የመቅደስን ዕቃ ያልሰረቁ አምላካችንንም ያልሰደቡ እነዚህን ሰዎች አምጥታችኋቸዋልና።
38Jei Demetrijas ir jo bendrai amatininkai turi prieš ką nors skundą, tai tam yra teismo dienos ir prokonsulai, tegul sau bylinėjasi.
38ድሜጥሮስና ከእርሱ ጋር ያሉት አንጥረኞች ግን በሰው ላይ ነገር እንዳላቸው፥ የመጋቢያ ቀንና አገረ ገዢዎች አሉ፤ እርስ በርሳቸው ይምዋገቱ።
39O jeigu jūs turite kokį kitą apsvarstytiną reikalą, tai jį bus galima išspręsti teisėtame susirinkime.
39ስለ ሌላ ነገር እንደ ሆነ ግን አንዳች ብትፈልጉ፥ በተደነገገው ጉባኤ ይፈታል።
40Šiaip jau yra pavojus būti apkaltintiems maištu dėl to, kas šiandien čia dėjosi, nes nėra jokio pagrindo, kuriuo galėtume pateisinti šį sambrūzdį”. Tai pasakęs, jis paleido susirinkimą.
40ዛሬ ስለ ተደረገው። ሁከት ነው ሲሉ እንዳይከሱን ያስፈራልና፤ ስለዚህም ስብሰባ ምላሽ መስጠት አንችልም፥ ምክንያት የለምና።