1Todėl, kol tebegalioja pažadas įeiti į Jo poilsį, bijokime, kad kuris nors iš jūsų nepasirodytų pavėlavęs.
1እንግዲህ ወደ ዕረፍቱ ለመግባት ተስፋ ገና ቀርቶልን ከሆነ፥ ምናልባት ከእናንተ ማንም የማይበቃ መስሎ እንዳይታይ እንፍራ።
2Mums, kaip ir jiems, buvo paskelbta Evangelija. Bet išgirstas žodis neišėjo jiems į naudą, nes nebuvo sujungtas su girdėjusiųjų tikėjimu.
2ለእነዚያ ደግሞ እንደ ተነገረ ለእኛ የምስራች ተሰብኮልናልና፤ ዳሩ ግን የሰሙት ቃል ከሰሚዎቹ ጋር በእምነት ስላልተዋሐደ አልጠቀማቸውም።
3O mes, įtikėjusieji, einame į tą poilsį, kaip Jo pasakyta: “Aš prisiekiau savo rūstybėje: ‘Jie neįeis į mano poilsį’ ”, nors darbai buvo užbaigti nuo pasaulio sutvėrimo.
3ሥራው ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ ምንም እንኳ ቢፈጸም። እንዲህ። ወደ ዕረፍቴ አይገቡም ብዬ በቁጣዬ ማልሁ እንዳለ፥ እኛስ ያመንን ወደ ዕረፍቱ እንገባለን።
4Jis vienoje vietoje pasakė apie septintąją dieną: “Septintąją dieną Dievas ilsėjosi po visų savo darbų”.
4ስለ ሰባተኛው ቀን በአንድ ስፍራ። እግዚአብሔርም በሰባተኛው ቀን ከሥራው ሁሉ ዐረፈ ብሎአልና፤
5Ir vėl anoje vietoje: “Jie neįeis į mano poilsį”.
5በዚህ ስፍራም ደግሞ። ወደ ዕረፍቴ አይገቡም።
6Kadangi kai kuriems belieka įeiti, o tie, kuriems pirma buvo paskelbta Evangelija, neįėjo dėl neklusnumo,
6እንግዲህ አንዳንዶች በዚያ እንዲገቡ ስለ ቀሩ፥ ቀድሞም የምስራች የተሰበከላቸው ባለመታዘዝ ጠንቅ ስላልገቡ።
7Jis vėl nustato tam tikrą dieną, po tiek daug laiko, kartodamas Dovydo lūpomis,“šiandien”,kaip ir buvo pasakyta: “Šiandien, jei išgirsite Jo balsą, neužkietinkite savo širdžių”.
7ዛሬ ድምፁን ብትሰሙት ልባችሁን እልከኛ አታድርጉ በፊት እንደ ተባለ፥ ይህን ከሚያህል ዘመን በኋላ በዳዊት ሲናገር። ዛሬ ብሎ አንድ ቀን እንደ ገና ይቀጥራል።
8Jeigu Jozuė būtų juos įvedęs į poilsį, Dievas nebūtų po to kalbėjęs apie kitą dieną.
8ኢያሱ አሳርፎአቸው ኖሮ ቢሆንስ፥ ከዚያ በኋላ ስለ ሌላ ቀን ባልተናገረ ነበር።
9Taigi sabato poilsis tebepasilieka Dievo tautai,
9እንግዲያስ የሰንበት ዕረፍት ለእግዚአብሔር ሕዝብ ቀርቶላቸዋል።
10nes, kas įeina į Jo poilsį, taip pat ilsisi po savo darbų, kaip Dievas ilsėjosi po savųjų.
10ወደ ዕረፍቱ የገባ፥ እግዚአብሔር ከሥራው እንዳረፈ፥ እርሱ ደግሞ ከሥራው አርፎአልና።
11Tad stenkimės įeiti į tą poilsį, kad niekas nebenupultų, sekdamas ano neklusnumo pavyzdžiu.
11እንግዲህ እንደዚያ እንደ አለመታዘዝ ምሳሌ ማንም እንዳይወድቅ ወደዚያ ዕረፍት ለመግባት እንትጋ።
12Dievo žodis yra gyvas ir veiksmingas, aštresnis už bet kokį dviašmenį kalaviją. Jis prasiskverbia iki pat sielos ir dvasios atšakos, iki sąnarių ir kaulų smegenų, ir teisia širdies mintis bei sumanymus.
12የእግዚአብሔር ቃል ሕያው ነውና፥ የሚሠራም፥ ሁለትም አፍ ካለው ሰይፍ ሁሉ ይልቅ የተሳለ ነው፥ ነፍስንና መንፈስንም ጅማትንና ቅልጥምንም እስኪለይ ድረስ ይወጋል፥ የልብንም ስሜትና አሳብ ይመረምራል፤
13Ir joks kūrinys nėra paslėptas nuo Jo žvilgsnio, bet visa yra nuoga ir atidengta akims To, kuriam turėsime duoti apyskaitą.
13እኛን በሚቆጣጠር በእርሱ ዓይኖቹ ፊት ሁሉ ነገር የተራቆተና የተገለጠ ነው እንጂ፥ በእርሱ ፊት የተሰወረ ፍጥረት የለም።
14Taigi, turėdami didį vyriausiąjį Kunigą, praėjusį pro dangus Dievo Sūnų Jėzų, tvirtai laikykimės mūsų išpažinimo.
14እንግዲህ በሰማያት ያለፈ ትልቅ ሊቀ ካህናት የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ስላለን፥ ጸንተን ሃይማኖታችንን እንጠብቅ።
15Juk mes turime ne tokį vyriausiąjį Kunigą, kuris negalėtų atjausti mūsų silpnybių, bet, kaip ir mes, visaip gundytą, tačiau nenusidėjusį.
15ከኃጢአት በቀር በነገር ሁሉ እንደ እኛ የተፈተነ ነው እንጂ፥ በድካማችን ሊራራልን የማይችል ሊቀ ካህናት የለንም።
16Todėl drąsiai artinkimės prie malonės sosto, kad gautume gailestingumą ir rastume malonę pagalbai reikiamu metu.
16እንግዲህ ምሕረትን እንድንቀበል በሚያስፈልገንም ጊዜ የሚረዳንን ጸጋ እንድናገኝ ወደ ጸጋው ዙፋን በእምነት እንቅረብ።