1Jie priplaukė ežero krantą gadariečių krašte.
1ወደ ባሕር ማዶም ወደ ጌርጌሴኖን አገር መጡ።
2Jam išlipus iš valties, tuojau prieš Jį iš kapinių atbėgo vyras, turintis netyrąją dvasią.
2ከታንኳይቱም በወጣ ጊዜ፥ ርኵስ መንፈስ የያዘው ሰው ከመቃብር ወጥቶ ወዲያው ተገናኘው፤
3Jis gyveno kapų rūsiuose, ir niekas negalėjo nė grandinėmis jo surakinti.
3እርሱም በመቃብር ይኖር ነበር፥ በሰንሰለትም ስንኳ ማንም ሊያስረው በዚያን ጊዜ አይችልም ነበር፤
4Nors jis jau daug kartų buvo pančiojamas ir grandinėmis rakinamas, bet sutrupindavo grandines, nutraukydavo pančius, ir niekas negalėdavo jo suvaldyti.
4ብዙ ጊዜ በእግር ብረትና በሰንሰለት ይታሰር ነበርና ዳሩ ግን ሰንሰለቱን ይበጣጥስ እግር ብረቱንም ይሰባብር ነበር፥ ሊያሸንፈውም የሚችል አልነበረም፤
5Per kiauras naktis ir dienas jis bastydavosi po kalnus ir kapines, klykdamas ir daužydamas save akmenimis.
5ሁልጊዜም ሌሊትና ቀን በመቃብርና በተራራ ሆኖ ይጮኽ ነበር ሰውነቱንም በድንጋይ ይቧጭር ነበር።
6Iš tolo pamatęs Jėzų, atbėgo, parpuolė prieš Jį
6ኢየሱስንም ከሩቅ ባየ ጊዜ ሮጦ ሰገደለት፥
7ir ėmė garsiai šaukti: “Ko Tau reikia iš manęs, Jėzau, aukščiausiojo Dievo Sūnau? Saikdinu tave Dievu, nekankink manęs!”
7በታላቅ ድምፅም እየጮኸ። የልዑል እግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ሆይ፥ ከአንተ ጋር ምን አለኝ? እንዳታሠቃየኝ በእግዚአብሔር አምልሃለሁ አለ፤
8Jėzus mat buvo paliepęs: “Išeik, netyroji dvasia, iš žmogaus!”
8አንተ ርኵስ መንፈስ፥ ከዚህ ሰው ውጣ ብሎት ነበርና።
9Jėzus dar paklausė: “O kaip tu vadiniesi?” Ji atsakė: “Mano vardasLegionas, nes mūsų daug”.
9ስምህ ማን ነው? ብሎ ጠየቀው። ብዙዎች ነንና ስሜ ሌጌዎን ነው አለው፥
10Ir pradėjo labai prašytis nevaryti jų iš to krašto.
10ከአገርም ውጭ እንዳይሰዳቸው አጥብቆ ለመነው።
11Ten pat, atkalnėje, ganėsi didžiulė kiaulių banda.
11በዚያም በተራራ ጥግ ብዙ የእሪያ መንጋ ይሰማራ ነበርና።
12Visi demonai maldavo Jį, sakydami: “Pasiųsk mus į tas kiaules, kad į jas sueitume!”
12ወደ እሪያዎቹ እንድንገባ ስደደን ብለው ለመኑት።
13Jėzus iškart jiems leido. Išėjusios netyrosios dvasios apniko kiaules, ir visa banda, apie du tūkstančius kiaulių, metėsi nuo skardžio į ežerą ir prigėrė.
13ኢየሱስም ፈቀደላቸው። ርኵሳን መናፍስቱም ወጥተው ወደ እሪያዎቹ ገቡ፥ ሁለት ሺህም የሚያህል መንጋ ከአፋፉ ወደ ባሕር ተጣደፉና በባሕር ሰጠሙ።
14Tie, kurie jas ganė, išbėgiojo ir pranešė apie įvykį mieste ir kaimuose. Žmonės išėjo pažiūrėti, kas atsitiko.
14እረኞቹም ሸሽተው በከተማውና በአገሩ አወሩ፤ ነገሩም ምን እንደ ሆነ ለማየት መጡ።
15Atėję prie Jėzaus, pamatė sėdintį demonų apsėstąjįtą, kuriame buvo Legionas,apsirengusį ir sveiko proto, ir juos apėmė baimė.
15ወደ ኢየሱስም መጡ፥ አጋንንትም ያደሩበትን ሌጌዎንም የነበረበትን ሰው ተቀምጦ ለብሶም ልቡም ተመልሶ አዩና ፈሩ።
16Mačiusieji papasakojo jiems, kas nutiko su apsėstuoju, ir apie kiaules.
16ያዩት ሰዎችም አጋንንት ላደሩበት ሰው የሆነውንና ስለ እሪያዎቹ ተረኩላቸው።
17Tada žmonės ėmė Jėzų maldauti, kad Jis pasišalintų iš jų krašto.
17ከአገራቸውም እንዲሄድላቸው ይለምኑት ጀመር።
18Jėzui lipant į valtį, buvęs demonų apsėstasis prašė leisti pasilikti su Juo,
18ወደ ታንኳይቱም በገባ ጊዜ አጋንንት አድረውበት የነበረው ሰው ከእርሱ ጋር እንዲኖር ለመነው።
19bet Jėzus nesutiko ir pasakė: “Eik namo pas saviškius ir papasakok, kokių didžių dalykų Viešpats tau padarė ir kaip tavęs pasigailėjo”.
19ኢየሱስም አልፈቀደለትም፥ ነገር ግን። ወደ ቤትህ በቤተ ሰዎችህ ዘንድ ሄደህ ጌታ እንዴት ያለ ታላቅ ነገር እንዳደረገልህ እንዴትስ እንደ ማረህ አውራላቸው አለው።
20Tada jis nuėjo savo keliu ir Dekapolyje ėmė skelbti, kokių didžių dalykų Jėzus jam padarė, ir visi stebėjosi.
20ሄዶም ኢየሱስ እንዴት ያለ ታላቅ ነገር እንዳደረገለት አሥር ከተማ በሚባል አገር ይሰብክ ጀመር፥ ሁሉም ተደነቁ።
21Jėzui vėl persikėlus valtimi į kitą pusę, prie Jo susirinko didžiulė minia, ir Jis buvo paežerėje.
21ኢየሱስም ደግሞ በታንኳይቱ ወደ ማዶ ከተሻገረ በኋላ ብዙ ሰዎች ወደ እርሱ ተሰበሰቡ፥ በባሕርም አጠገብ ነበረ።
22Štai ateina vienas iš sinagogos vyresniųjų, vardu Jayras, ir, pamatęs Jį, puola Jam po kojų,
22ኢያኢሮስ የተባለ ከምኵራብ አለቆች አንዱ መጣ፤ ባየውም ጊዜ በእግሩ ላይ ወደቀና።
23karštai maldaudamas: “Mano dukrelė miršta! Ateik ir uždėk ant jos rankas, kad pagytų ir gyventų”.
23ታናሽቱ ልጄ ልትሞት ቀርባለችና እንድትድንና በሕይወት እንድትኖር መጥተህ እጅህን ጫንባት ብሎ አጥብቆ ለመነው።
24Jėzus nuėjo su juo. Paskui Jį sekė didžiulė minia ir Jį spauste spaudė.
24ከእርሱም ጋር ሄደ። ብዙ ሕዝብም ተከተሉት አጋፉትም።
25Ten buvo viena moteris, dvylika metų serganti kraujoplūdžiu.
25ከአሥራ ሁለት ዓመትም ጀምሮ ደም የሚፈሳት ሴት ነበረች፥
26Nemaža iškentėjusi nuo daugelio gydytojų ir išleidusi visa, ką turėjo, ji nė kiek nepasitaisė, bet ėjo vis blogyn.
26ከብዙ ባለ መድኃኒቶችም ብዙ ተሠቃየች፤ ገንዘብዋንም ሁሉ ከስራ ባሰባት እንጂ ምንም አልተጠቀመችም፤
27Išgirdusi apie Jėzų, ji prasispraudė iš minios galo ir prisilietė prie Jo apsiausto.
27የኢየሱስንም ወሬ ሰምታ በስተኋላው በሰዎች መካከል መጥታ ልብሱን ዳሰሰች።
28Mat ji kalbėjo: “Jeigu paliesiu bent Jo drabužįišgysiu!”
28ልብሱን ብቻ የዳሰስሁ እንደ ሆነ እድናለሁ ብላለችና።
29Tuojau kraujas nustojo jai plūdęs, ir ji pajuto kūnu, kad yra pasveikusi nuo savo ligos.
29ወዲያውም የደምዋ ምንጭ ደረቀ ከሥቃይዋም እንደዳነች በሰውነትዋ አወቀች።
30Ir Jėzus iš karto pajuto, kad iš Jo išėjo jėga, ir, atsigręžęs į minią, paklausė: “Kas prisilietė prie mano apsiausto?”
30ወዲያውም ኢየሱስ ከእርሱ ኃይል እንደ ወጣ በገዛ ራሱ አውቆ በሕዝቡ መካከል ዘወር ብሎ። ልብሴን የዳሰሰ ማን ነው? አለ።
31Jo mokiniai Jam atsakė: “Matai, kaip minia Tave spaudžia, o Tu klausi: ‘Kas mane palietė?’ ”
31ደቀ መዛሙርቱም። ሕዝቡ ሲያጋፉህ እያየህ። ማን ዳሰሰኝ ትላለህን? አሉት።
32Bet Jis dairėsi tos, kuri taip buvo padariusi.
32ይህንም ያደረገችውን ለማየት ዘወር ብሎ ይመለከት ነበር።
33Moteris išėjo į priekį išsigandusi ir virpėdama, nes žinojo, kas jai atsitiko, ir, puolusi prieš Jį, papasakojo visą tiesą.
33ሴቲቱ ግን የተደረገላትን ስላወቀች፥ እየፈራች እየተንቀጠቀጠችም፥ መጥታ በፊቱ ተደፋች እውነቱንም ሁሉ ነገረችው።
34O Jis tarė jai: “Dukra, tavo tikėjimas išgydė tave, eik rami ir būk sveika nuo savo ligos”.
34እርሱም። ልጄ ሆይ፥ እምነትሽ አድኖሻል፤ በሰላም ሂጂ ከሥቃይሽም ተፈወሽ አላት።
35Jam dar tebekalbant, atėjo sinagogos vyresniojo žmonės ir pranešė: “Tavo duktė numirė, kam dar vargini Mokytoją?”
35እርሱም ገና ሲናገር ከምኵራብ አለቃው ቤት ዘንድ የመጡት። ልጅህ ሞታለች፤ ስለ ምን መምህሩን አሁን ታደክመዋለህ? አሉት።
36Išgirdęs tuos žodžius, Jėzus tarė sinagogos vyresniajam: “Nebijok, vien tik tikėk!”
36ኢየሱስ ግን የተናገሩትን ቃል አድምጦ ለምኵራቡ አለቃ። እመን ብቻ እንጂ አትፍራ አለው።
37Ir Jis niekam neleido eiti kartu, išskyrus Petrą, Jokūbą ir Jokūbo brolį Joną.
37ከጴጥሮስም ከያዕቆብም ከያዕቆብም ወንድም ከዮሐንስ በቀር ማንም እንዲከተለው አልፈቀደም።
38Atėjęs į sinagogos vyresniojo namus, Jėzus pamatė sujudimą ir garsiai verkiančius bei raudančius.
38ወደ ምኵራቡ አለቃ ቤትም መጥቶ ሰዎች ሲንጫጩና ሲያለቅሱ ዋይታም ሲያበዙ አየ፤
39Įžengęs vidun, Jis tarė: “Kam tas triukšmas ir verksmas?! Vaikas nėra miręs, o miega”.
39ገብቶም። ስለ ምን ትንጫጫላችሁ ታለቅሳላችሁም? ብላቴናይቱ ተኝታለች እንጂ አልሞተችም አላቸው።
40Žmonės šaipėsi iš Jo. Tada, išvaręs juos visus, Jis pasiėmė vaiko tėvą ir motiną, taip pat savo palydovus ir įėjo ten, kur vaikas gulėjo.
40በጣምም ሳቁበት። እርሱ ግን ሁሉን አስወጥቶ የብላቴናይቱን አባትና እናትም ከእርሱ ጋር የነበሩትንም ይዞ ብላቴናይቱ ወዳለችበት ገባ።
41Paėmęs mergaitę už rankos, pasakė jai: “Talitį kum”; išvertus reiškia: “Mergaite, sakau tau, kelkis!”
41የብላቴናይቱንም እጅ ይዞ። ጣሊታ ቁሚ አላት፤ ፍችውም አንቺ ብላቴና ተነሽ እልሻለሁ ነው።
42Mergaitė tuojau atsikėlė ir ėmė vaikščioti. Jai buvo dvylika metų. Jie nustėro iš nuostabos.
42ብላቴናይቱም የአሥራ ሁለት ዓመት ልጅ ነበረችና ወዲያው ቆማ ተመላለሰች። ወዲያውም ታላቅ መገረም ተገረሙ።
43Jis griežtai įsakė, kad niekas to nežinotų, ir liepė duoti mergaitei valgyti.
43ይህንም ማንም እንዳያውቅ አጥብቆ አዞአቸው። የምትበላውን ስጡአት አላቸው።