1И ја дошавши к вама, браћо, не дођох с високом речи или премудрости да вам јављам сведочанство Божије.
1እኔም፥ ወንድሞች ሆይ፥ ወደ እናንተ በመጣሁ ጊዜ በቃልና በጥበብ ብልጫ ለእግዚአብሔር ምስክርነቴን ለእናንተ እየነገርሁ አልመጣሁም።
2Јер нисам мислио да знам шта међу вама осим Исуса Христа, и то распетог.
2በመካከላችሁ ሳለሁ ከኢየሱስ ክርስቶስ በቀር እርሱም እንደተሰቀለ ሌላ ነገር እንዳላውቅ ቆርጬ ነበርና።
3И ја бејах међу вама у слабости, и у страху и у великом дрхтању.
3እኔም በድካምና በፍርሃት በብዙ መንቀጥቀጥም በእናንተ ዘንድ ነበርሁ፤
4И реч моја, и поучење моје не беше у надговорљивим речима људске премудрости, него у доказивању Духа и силе.
4እምነታችሁም በእግዚአብሔር ኃይል እንጂ በሰው ጥበብ እንዳይሆን፥ ቃሌም ስብከቴም መንፈስንና ኃይልን በመግለጥ ነበረ እንጂ፥ በሚያባብል በጥበብ ቃል አልነበረም።
5Да вера ваша не буде у мудрости људској него у сили Божијој.
6በበሰሉት መካከል ግን ጥበብን እንናገራለን፥ ነገር ግን የዚችን ዓለም ጥበብ አይደለም የሚሻሩትንም የዚችን ዓለም ገዦች ጥበብ አይደለም፤
6Али премудрост говоримо која је у савршенима, а не премудрост века овог ни кнезова века овог који пролазе.
7ነገር ግን እግዚአብሔር አስቀድሞ ከዘመናት በፊት ለክብራችን የወሰነውን፥ ተሰውሮም የነበረውን የእግዚአብሔርን ጥበብ በምሥጢር እንናገራለን።
7Него говоримо премудрост Божију у тајности сакривену, коју одреди Бог пре света за славу нашу;
8ከዚችም ዓለም ገዦች አንዱ እንኳ ይህን ጥበብ አላወቀም፤ አውቀውስ ቢሆኑ የክብርን ጌታ ባልሰቀሉትም ነበር፤
8Које ниједан од кнезова века овог не позна; јер да су је познали, не би Господа славе разапели.
9ነገር ግን። ዓይን ያላየችው ጆሮም ያልሰማው በሰውም ልብ ያልታሰበው እግዚአብሔር ለሚወዱት ያዘጋጀው ተብሎ እንድተጻፈ፥ እንዲህ እንናገራለን።
9Него као што је писано: Шта око не виде, и ухо не чу, и у срце човеку не дође, оно уготови Бог онима, који Га љубе.
10መንፈስም የእግዚአብሔርን ጥልቅ ነገር ስንኳ ሳይቀር ሁሉን ይመረምራልና ለእኛ እግዚአብሔር በመንፈሱ በኩል ገለጠው።
10А нама је Бог открио Духом својим; јер Дух све испитује, и дубине Божије.
11በእርሱ ውስጥ ካለው ከሰው መንፈስ በቀር ለሰው ያለውን የሚያውቅ ሰው ማን ነው? እንዲሁም ደግሞ ከእግዚአብሔር መንፈስ በቀር ለእግዚአብሔር ያለውን ማንም አያውቅም።
11Јер ко од људи зна шта је у човеку осим духа човечијег који живи у њему? Тако и у Богу шта је нико не зна осим Духа Божијег.
12እኛ ግን ከእግዚአብሔር እንዲያው የተሰጠንን እናውቅ ዘንድ ከእግዚአብሔር የሆነውን መንፈስ እንጂ የዓለምን መንፈስ አልተቀበልንም።
12А ми не примисмо духа овог света, него Духа који је из Бога, да знамо шта нам је даровано од Бога;
13መንፈሳዊውን ነገር ከመንፈሳዊው ነገር ጋር አስተያይተን መንፈስ በሚያስተምረን ቃል ይህን ደግሞ እንናገራለን እንጂ የሰው ጥበብ በሚያስተምረን ቃል አይደለም።
13Које и говоримо не речима што је научила човечија премудрост, него шта учи Дух Свети; и духовне ствари духовно радимо.
14ለፍጥረታዊ ሰው የእግዚአብሔር መንፈስ ነገር ሞኝነት ነውና አይቀበለውም፤ በመንፈስም የሚመረመር ስለ ሆነ ሊያውቀው አይችልም።
14А телесни човек не разуме шта је од Духа Божијег; јер му се чини лудост и не може да разуме, јер треба духовно да се разгледа.
15መንፈሳዊ ሰው ግን ሁሉን ይመረምራል ራሱ ግን በማንም አይመረመርም።
15Духовни пак све разгледа, а њега самог нико не разгледа.
16እንዲያስተምረው የጌታን ልብ ማን አውቆት ነው? እኛ ግን የክርስቶስ ልብ አለን።
16Јер ко позна ум Господњи да Га поучи? А ми ум Христов имамо.