Serbian: Cyrillic

Amharic: New Testament

1 John

4

1Љубазни! Не верујте сваком духу, него кушајте духове јесу ли од Бога; јер многи лажни пророци изиђоше на свет.
1ወዳጆች ሆይ፥ መንፈስን ሁሉ አትመኑ፥ ነገር ግን መናፍስት ከእግዚአብሔር ሆነው እንደ ሆነ መርምሩ፤ ብዙዎች ሐሰተኞች ነቢያት ወደ ዓለም ወጥተዋልና።
2По овом познајте Духа Божијег, и духа лажног; сваки дух који признаје да је Исус Христос у телу дошао, од Бога је;
2የእግዚአብሔርን መንፈስ በዚህ ታውቃላችሁ፤ ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ እንደ መጣ የሚታመን መንፈስ ሁሉ ከእግዚአብሔር ነው፥
3А сваки дух који не признаје да је Исус Христос у телу дошао, није од Бога: и овај је антихристов, за ког чусте да ће доћи, и сад је већ на свету.
3ኢየሱስ ክርስቶስም በሥጋ እንደ መጣ የማይታመን መንፈስ ሁሉ ከእግዚአብሔር አይደለም፤ ይህም የክርስቶስ ተቃዋሚው መንፈስ ነው፤ ይህም እንዲመጣ ሰምታችኋል፥ አሁንም እንኳ በዓለም አለ።
4Ви сте од Бога, дечице, и надвладасте их, јер је већи који је у вама неголи који је на свету.
4ልጆች ሆይ፥ እናንተ ከእግዚአብሔር ናችሁ አሸንፋችኋቸውማል፥ በዓለም ካለው ይልቅ በእናንተ ያለው ታላቅ ነውና።
5Они су од света, зато говоре од света, и свет их слуша.
5እነርሱ ከዓለም ናቸው፤ ስለዚህ ከዓለም የሆነውን ይናገራሉ ዓለሙም ይሰማቸዋል።
6Ми смо од Бога; који познаје Бога слуша нас, а који није од Бога не слуша нас. По овом познајемо духа истине и духа преваре.
6እኛ ከእግዚአብሔር ነን፤ እግዚአብሔርን የሚያውቅ ይሰማናል፤ ከእግዚአብሔር ያልሆነ አይሰማንም። የእውነትን መንፈስና የስሕተትን መንፈስ በዚህ እናውቃለን።
7Љубазни! Да љубимо један другог; јер је љубав од Бога, и сваки који има љубав од Бога је рођен, и познаје Бога.
7ወዳጆች ሆይ፥ ፍቅር ከእግዚአብሔር ስለ ሆነ፥ የሚወደውም ሁሉ ከእግዚአብሔር ስለ ተወለደ እግዚአብሔርንም ስለሚያውቅ፥ እርስ በርሳችን እንዋደድ።
8А који нема љубави не позна Бога; јер је Бог љубав.
8ፍቅር የሌለው እግዚአብሔርን አያውቅም፥ እግዚአብሔር ፍቅር ነውና።
9По том се показа љубав Божија к нама што Бог Сина свог Јединородног посла на свет да живимо кроза Њ.
9በዚህ የእግዚአብሔር ፍቅር በእኛ ዘንድ ተገለጠ፥ በእርሱ በኩል በሕይወት እንኖር ዘንድ እግዚአብሔር አንድ ልጁን ወደ ዓለም ልኮታልና።
10У овом је љубав не да ми показасмо љубав к Богу, него да Он показа љубав к нама, и посла Сина свог да очисти грехе наше.
10ፍቅርም እንደዚህ ነው፤ እግዚአብሔር እርሱ ራሱ እንደ ወደደን ስለ ኃጢአታችንም ማስተስሪያ ይሆን ዘንድ ልጁን እንደ ላከ እንጂ እኛ እግዚአብሔርን እንደ ወደድነው አይደለም።
11Љубазни! Кад је овако Бог показао љубав к нама, и ми смо дужни љубити један другог.
11ወዳጆች ሆይ፥ እግዚአብሔር እንዲህ አድርጎ ከወደደን እኛ ደግሞ እርስ በርሳችን ልንዋደድ ይገባናል።
12Бога нико не виде никад: ако имамо љубав међу собом, Бог у нама стоји, и љубав је Његова савршена у нама.
12እግዚአብሔርን ማንም ከቶ አላየውም፤ እርስ በርሳችን ብንዋደድ እግዚአብሔር በእኛ ይኖራል ፍቅሩም በእኛ ፍጹም ሆኖአል።
13По том дознајемо да у Њему стојимо, и Он у нама, што нам је дао од Духа свог.
13ከመንፈሱ ስለ ሰጠን፥ በእርሱ እንድንኖር እርሱም በእኛ እንዲኖር በዚህ እናውቃለን።
14И ми видесмо и сведочимо да Отац посла Сина да се спасе свет.
14እኛም አይተናል አባትም ልጁን የዓለም መድኃኒት ሊሆን እንደ ላከው እንመሰክራለን።
15Који призна да је Исус Син Божји, Бог у њему стоји и он у Богу.
15ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ በሚታመን ሁሉ እግዚአብሔር በእርሱ ይኖራል እርሱም በእግዚአብሔር ይኖራል።
16И ми познасмо и веровасмо љубав коју Бог има к нама. Бог је љубав, и који стоји у љубави, у Богу стоји и Бог у њему стоји.
16እኛም እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን ፍቅር አውቀናል አምነንማል። እግዚአብሔር ፍቅር ነው፥ በፍቅርም የሚኖር በእግዚአብሔር ይኖራል እግዚአብሔርም በእርሱ ይኖራል።
17Тим се љубав у нама савршује да имамо слободу на дан судни; јер као што је Он и ми смо на свету овом.
17በፍርድ ቀን ድፍረት ይሆንልን ዘንድ ፍቅር በዚህ ከእኛ ጋር ተፈጽሞአል፤ እርሱ እንዳለ እኛ ደግሞ እንዲሁ በዚህ ዓለም ነንና።
18У љубави нема страха, него савршена љубав изгони страх напоље; јер страх има муку. А ко се боји није савршен у љубави.
18ፍጹም ፍቅር ፍርሃትን አውጥቶ ይጥላል እንጂ በፍቅር ፍርሃት የለም፥ ፍርሃት ቅጣት አለውና፤ የሚፈራም ሰው ፍቅሩ ፍጹም አይደለም።
19Да имамо ми љубав к Њему, јер Он најпре показа љубав к нама.
19እርሱ አስቀድሞ ወዶናልና እኛ እንወደዋለን።
20Ако ко рече: Ја љубим Бога, а мрзи на брата свог, лажа је; јер који не љуби брата свог, кога види, како може љубити Бога, кога не види?
20ማንም። እግዚአብሔርን እወዳለሁ እያለ ወንድሙን ቢጠላ ሐሰተኛ ነው፤ ያየውን ወንድሙን የማይወድ ያላየውን እግዚአብሔርን ሊወደው እንዴት ይችላል?
21И ову заповест имамо од Њега: Који љуби Бога да љуби и брата свог.
21እግዚአብሔርንም የሚወድ ወንድሙን ደግሞ እንዲወድ ይህች ትእዛዝ ከእርሱ አለችን።