Serbian: Cyrillic

Amharic: New Testament

Galatians

3

1О неразумни Галати! Ко вас је опчинио да се не покоравате истини? Ви, којима пред очима беше написан Исус Христос, а сад се међу вама разапе.
1የማታስተውሉ የገላትያ ሰዎች ሆይ፥ በዓይናችሁ ፊት ኢየሱስ ክርስቶስ እንደ ተሰቀለ ሆኖ ተሥሎ ነበር፤ ለእውነት እንዳትታዘዙ አዚም ያደረገባችሁ ማን ነው?
2Ово једно хоћу од вас да дознам, или Духа примисте кроз дела закона или кроз чувење вере?
2ይህን ብቻ ከእናንተ እንድማር እወዳለሁ፤ በሕግ ሥራ ወይም ከእምነት ጋር በሆነ መስማት መንፈስን ተቀበላችሁን?
3Тако ли сте неразумни? Почевши Духом, сад телом свршујете?
3እንዲህን የማታስተውሉ ናችሁ? በመንፈስ ጀምራችሁ አሁን በሥጋ ትፈጽማላችሁን?
4Тако ли узалуд пострадасте? Кад би било само узалуд!
4በውኑ ከንቱ እንደ ሆነስ እንደዚህ ያለ መከራ በከንቱ ተቀበላችሁን?
5Који вам дакле даје Духа и чини чудеса међу вама, чини ли делима закона или чувењем вере?
5እንግዲህ መንፈስን የሚሰጣችሁ በእናንተም ዘንድ ተአምራት የሚያደርግ፥ በሕግ ሥራ ነውን ወይስ ከእምነት ጋር በሆነ መስማት ነው?
6Као што Авраам верова Богу, и прими му се у правду.
6እንዲሁ አብርሃም በእግዚአብሔር አመነና ጽድቅ ሆኖ ተቆጠረለት።
7Познајте дакле да су они синови Авраамови који су од вере.
7እንኪያስ ከእምነት የሆኑት እነዚህ የአብርሃም ልጆች እንደ ሆኑ እወቁ።
8А писмо видевши унапред да Бог вером незнабошце правда, напред објави Аврааму: У теби ће се благословити сви незнабошци.
8መጽሐፍም እግዚአብሔር አሕዛብን በእምነት እንዲያጸድቅ አስቀድሞ አይቶ። በአንተ አሕዛብ ሁሉ ይባረካሉ ብሎ ወንጌልን ለአብርሃም አስቀድሞ ሰበከ።
9Тако који су од вере, благословиће се с верним Авраамом.
9እንደዚህ ከእምነት የሆኑት ካመነው ከአብርሃም ጋር ይባረካሉ።
10Јер који су год од дела закона под клетвом су, јер је писано: Проклет сваки који не остане у свему што је написано у књизи законској да чини.
10ከሕግ ሥራ የሆኑት ሁሉ በእርግማን በታች ናቸውና፤ በሕግ መጽሐፍ በተጻፉት ሁሉ ጸንቶ የማይኖር የማያደርግም ሁሉ የተረገመ ነው ተብሎ ተጽፎአልና።
11А да се законом нико не оправдава пред Богом, познато је: јер праведник од вере живеће.
11ጻድቅ በእምነት ይኖራል ተብሎአልና ማንም በእግዚአብሔር ፊት በሕግ እንዳይጸድቅ ግልጥ ነው።
12А закон није од вере; него човек који то твори живеће у томе.
12ሕግም ከእምነት አይደለም ነገር ግን። የሚያደርገው ይኖርበታል ተብሎአል።
13Христос је нас искупио од клетве законске поставши за нас клетва, јер је писано: Проклет сваки који виси на дрвету:
13በእንጨት የሚሰቀል ሁሉ የተረገመ ነው ተብሎ ተጽፎአልና ክርስቶስ ስለ እኛ እርግማን ሆኖ ከሕግ እርግማን ዋጀን፤
14Да међу незнабошцима буде благослов Аврамов у Христу Исусу, да обећање Духа примимо кроз веру.
14የመንፈስን ተስፋ በእምነት እንድንቀበል፥ የአብርሃም በረከት ወደ አሕዛብ በኢየሱስ ክርስቶስ ይደርስላቸው ዘንድ።
15Браћо, по човеку говорим, нико човечији потврђен завет не одбацује нити му шта домеће.
15ወንድሞች ሆይ፥ እንደ ሰው ልማድ እላለሁ። የሰው ስንኳ ቢሆን እርግጠኛውን ኪዳን ማንም አይንቅም ወይም አይጨምርበትም።
16А Аврааму и семену његовом речена бише обећања. А не вели: и семенима, као за многа, него као за једно: и семену твом, које је Христос.
16ለአብርሃምና ለዘሩም የተስፋው ቃል ተነገረ። ስለ ብዙዎች እንደሚነገር። ለዘሮቹም አይልም፤ ስለ አንድ እንደሚነገር ግን። ለዘርህም ይላል፥ እርሱም ክርስቶስ።
17Ово пак велим: завет, који је од Бога потврђен за Христа, не одбацује закон, који је постао после четири стотине и тридесет година, да укине обећање.
17ይህንም እላለሁ፤ ከአራት መቶ ሠላሳ ዓመት በኋላ የተሰጠው ሕግ አስቀድሞ በእግዚአብሔር የተረጋገጠውን ኪዳን የተስፋውን ቃል እስኪሽር ድረስ አያፈርስም።
18Јер ако је наследство од закона, онда већ није од обећања, а Аврааму обећањем дарова Бог.
18ርስቱ በሕግ ቢሆንስ እንግዲያስ በተስፋ ቃል አይሆንም፤ በተስፋ ቃል ግን እግዚአብሔር ለአብርሃም ሰጥቶአል።
19Шта ће дакле закон? Ради греха додаде се докле дође семе које му се обећа, и поставили су га анђели руком посредника.
19እንግዲህ ሕግ ምንድር ነው? ተስፋው የተሰጠው ዘር እስኪመጣ ድረስ በመካከለኛ እጅ በመላእክት በኩል ስለ ሕግ መተላለፍ ተጨመረ።
20Али посредник није једног; а Бог је један.
20መካከለኛውም ለአንድ ብቻ አይደለም እግዚአብሔር ግን አንድ ነው።
21Еда ли је дакле закон противан обећањима Божјим? Боже сачувај! Јер да је дан закон који може оживети, заиста би од закона била правда.
21እንግዲህ ሕግ የእግዚአብሔርን የተስፋ ቃል የሚቃወም ነውን? አይደለም። ሕያው ሊያደርግ የሚቻለው ሕግ ተሰጥቶ ቢሆንስ በእውነት ጽድቅ ከሕግ በሆነ ነበር፤
22Али писмо затвори све под грех, да се обећање даде кроз веру Исуса Христа онима који верују.
22ነገር ግን በኢየሱስ ክርስቶስ ከማመን የሆነው የተስፋ ቃል ለሚያምኑ ይሰጥ ዘንድ መጽሐፍ ከኃጢአት በታች ሁሉን ዘግቶታል።
23А пре доласка вере бисмо под законом чувани и затворени за веру која се хтела показати.
23እምነትም ሳይመጣ ሊገለጥ ላለው እምነት ተዘግተን ከሕግ በታች እንጠበቅ ነበር።
24Тако нам закон би чувар до Христа, да се вером оправдамо.
24እንደዚህ በእምነት እንጸድቅ ዘንድ ሕግ ወደ ክርስቶስ የሚያመጣ ሞግዚታችን ሆኖአል፤
25А кад дође вера, већ нисмо под чуваром.
25እምነት ግን መጥቶአልና ከእንግዲህ ወዲህ ከሞግዚት በታች አይደለንም።
26Јер сте ви сви синови Божји вером Христа Исуса;
26በእምነት በኩል ሁላችሁ በክርስቶስ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጆች ናችሁና፤
27Јер који се год у Христа крстисте, у Христа се обукосте.
27ከክርስቶስ ጋር አንድ ትሆኑ ዘንድ የተጠመቃችሁ ሁሉ ክርስቶስን ለብሳችኋልና።
28Нема ту Јеврејина ни Грка, нема роба ни господара, нема мушког рода ни женског; јер сте ви сви једно у Христу Исусу.
28አይሁዳዊ ወይም የግሪክ ሰው የለም፥ ባሪያ ወይም ጨዋ ሰው የለም፥ ወንድም ሴትም የለም፤ ሁላችሁ በክርስቶስ ኢየሱስ አንድ ሰው ናችሁና።
29А кад сте ви Христови, онда сте семе Авраамово, и по обећању наследници.
29እናንተም የክርስቶስ ከሆናችሁ እንኪያስ የአብርሃም ዘር እንደ ተስፋውም ቃል ወራሾች ናችሁ።