1Be therefore imitators of God, as beloved children.
1እንግዲህ እንደ ተወደዱ ልጆች እግዚአብሔርን የምትከተሉ ሁኑ፥
2Walk in love, even as Christ also loved you, and gave himself up for us, an offering and a sacrifice to God for a sweet-smelling fragrance.
2ክርስቶስም ደግሞ እንደ ወደዳችሁ ለእግዚአብሔርም የመዓዛ ሽታ የሚሆንን መባንና መሥዋዕትን አድርጎ ስለ እናንተ ራሱን አሳልፎ እንደ ሰጠ በፍቅር ተመላለሱ።
3But sexual immorality, and all uncleanness, or covetousness, let it not even be mentioned among you, as becomes saints;
3ለቅዱሳን እንደሚገባ ግን ዝሙትና ርኵሰት ሁሉ ወይም መመኘት በእናንተ ዘንድ ከቶ አይሰማ፤
4nor filthiness, nor foolish talking, nor jesting, which are not appropriate; but rather giving of thanks.
4የሚያሳፍር ነገርም የስንፍና ንግግርም ወይም ዋዛ የማይገቡ ናቸውና አይሁኑ፥ ይልቁን ምስጋና እንጂ።
5Know this for sure, that no sexually immoral person, nor unclean person, nor covetous man, who is an idolater, has any inheritance in the Kingdom of Christ and God.
5ይህን እወቁ፤ አመንዝራም ቢሆን ወይም ርኵስ ወይም የሚመኝ እርሱም ጣዖትን የሚያመልክ በክርስቶስና በእግዚአብሔር መንግሥት ርስት የለውም።
6Let no one deceive you with empty words. For because of these things, the wrath of God comes on the children of disobedience.
6ከዚህ የተነሣ በማይታዘዙት ልጆች ላይ የእግዚአብሔር ቁጣ ይመጣልና ማንም በከንቱ ንግግር አያታልላችሁ።
7Therefore don’t be partakers with them.
7እንግዲህ ከእነርሱ ጋር ተካፋዮች አትሁኑ፤
8For you were once darkness, but are now light in the Lord. Walk as children of light,
8ቀድሞ ጨለማ ነበራችሁና፥ አሁን ግን በጌታ ብርሃን ናችሁ፤
9for the fruit of the Spirit is in all goodness and righteousness and truth,
9የብርሃኑ ፍሬ በበጎነትና በጽድቅ በእውነትም ሁሉ ነውና ለጌታ ደስ የሚያሰኘውን እየመረመራችሁ፥ እንደ ብርሃን ልጆች ተመላለሱ፤
10proving what is well pleasing to the Lord.
11ፍሬም ከሌለው ከጨለማ ሥራ ጋር አትተባበሩ፥ ይልቁን ግለጡት እንጂ፥
11Have no fellowship with the unfruitful works of darkness, but rather even reprove them.
12እነርሱ በስውር ስለሚያደርጉት መናገር እንኳ ነውር ነውና፤
12For the things which are done by them in secret, it is a shame even to speak of.
13ሁሉ ግን በብርሃን ሲገለጥ ይታያል፤ የሚታየው ሁሉ ብርሃን ነውና።
13But all things, when they are reproved, are revealed by the light, for everything that reveals is light.
14ስለዚህ። አንተ የምትተኛ ንቃ ከሙታንም ተነሣ ክርስቶስም ያበራልሃል ይላል።
14Therefore he says, “Awake, you who sleep, and arise from the dead, and Christ will shine on you.”
15እንግዲህ እንደ ጥበበኞች እንጂ ጥበብ እንደሌላቸው ሳይሆን እንዴት እንድትመላለሱ በጥንቃቄ ተጠበቁ፤
15Therefore watch carefully how you walk, not as unwise, but as wise;
16ቀኖቹ ክፉዎች ናቸውና ዘመኑን ዋጁ።
16redeeming the time, because the days are evil.
17ስለዚህ የጌታ ፈቃድ ምን እንደ ሆነ አስተውሉ እንጂ ሞኞች አትሁኑ።
17Therefore don’t be foolish, but understand what the will of the Lord is.
18መንፈስ ይሙላባችሁ እንጂ በወይን ጠጅ አትስከሩ ይህ ማባከን ነውና፤
18Don’t be drunken with wine, in which is dissipation, but be filled with the Spirit,
19በመዝሙርና በዝማሬ በመንፈሳዊም ቅኔ እርስ በርሳችሁ ተነጋገሩ፤ ለጌታ በልባችሁ ተቀኙና ዘምሩ፤
19speaking to one another in psalms, hymns, and spiritual songs; singing, and making melody in your heart to the Lord;
20ሁልጊዜ ስለ ሁሉ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አምላካችንንና አባታችንን ስለ ሁሉ አመስግኑ።
20giving thanks always concerning all things in the name of our Lord Jesus Christ, to God, even the Father;
21ለእያንዳንዳችሁ በክርስቶስ ፍርሃት የተገዛችሁ ሁኑ።
21subjecting yourselves one to another in the fear of Christ.
22ሚስቶች ሆይ፥ ለጌታ እንደምትገዙ ለባሎቻችሁ ተገዙ፤
22Wives, be subject to your own husbands, as to the Lord.
23ክርስቶስ ደግሞ የቤተ ክርስቲያን ራስ እንደ ሆነ እርሱም አካሉን የሚያድን እንደ ሆነ ባል የሚስት ራስ ነውና።
23For the husband is the head of the wife, and Christ also is the head of the assembly, being himself the savior of the body.
24ዳሩ ግን ቤተ ክርስቲያን ለክርስቶስ እንደምትገዛ እንዲሁ ሚስቶች ደግሞ በሁሉ ለባሎቻቸው ይገዙ።
24But as the assembly is subject to Christ, so let the wives also be to their own husbands in everything.
25ባሎች ሆይ፥ ክርስቶስ ደግሞ ቤተ ክርስቲያንን እንደ ወደዳት ሚስቶቻችሁን ውደዱ፤ በውኃ መታጠብና ከቃሉ ጋር አንጽቶ እንዲቀድሳት ስለ እርስዋ ራሱን አሳልፎ ሰጠ፤
25Husbands, love your wives, even as Christ also loved the assembly, and gave himself up for it;
27እድፈት ወይም የፊት መጨማደድ ወይም እንዲህ ያለ ነገር ሳይሆንባት ቅድስትና ያለ ነውር ትሆን ዘንድ ክብርት የሆነችን ቤተ ክርስቲያን ለራሱ እንዲያቀርብ ፈለገ።
26that he might sanctify it, having cleansed it by the washing of water with the word,
28እንዲሁም ባሎች ደግሞ እንደ ገዛ ሥጋቸው አድርገው የገዛ ሚስቶቻቸውን ሊወዱአቸው ይገባቸዋል። የገዛ ሚስቱን የሚወድ ራሱን ይወዳል፤
27that he might present the assembly to himself gloriously, not having spot or wrinkle or any such thing; but that it should be holy and without blemish.
29ማንም የገዛ ሥጋውን የሚጠላ ከቶ የለምና፥ ነገር ግን የአካሉ ብልቶች ስለሆንን፥ ክርስቶስ ደግሞ ለቤተ ክርስቲያን እንዳደረገላት፥ ይመግበዋል ይከባከበውማል።
28Even so husbands also ought to love their own wives as their own bodies. He who loves his own wife loves himself.
31ስለዚህ ሰው አባቱንና እናቱን ይተዋል ከሚስቱም ጋር ይተባበራል ሁለቱም አንድ ሥጋ ይሆናሉ።
29For no man ever hated his own flesh; but nourishes and cherishes it, even as the Lord also does the assembly;
32ይህ ምሥጢር ታላቅ ነው፥ እኔ ግን ይህን ስለ ክርስቶስና ስለ ቤተ ክርስቲያን እላለሁ።
30because we are members of his body, of his flesh and bones.
33ሆኖም ከእናንተ ደግሞ እያንዳንዱ የገዛ ሚስቱን እንዲህ እንደ ራሱ አድርጎ ይውደዳት፥ ሚስቱም ባልዋን ትፍራ።
31“For this cause a man will leave his father and mother, and will be joined to his wife. The two will become one flesh.” Genesis 2:24
32This mystery is great, but I speak concerning Christ and of the assembly.
33Nevertheless each of you must also love his own wife even as himself; and let the wife see that she respects her husband.