1Stand firm therefore in the liberty by which Christ has made us free, and don’t be entangled again with a yoke of bondage.
1በነጻነት ልንኖር ክርስቶስ ነጻነት አወጣን፤ እንግዲህ ጸንታችሁ ቁሙ እንደ ገናም በባርነት ቀንበር አትያዙ።
2Behold, I, Paul, tell you that if you receive circumcision, Christ will profit you nothing.
2እነሆ፥ እኔ ጳውሎስ እላችኋለሁ። ብትገረዙ ክርስቶስ ምንም አይጠቅማችሁም።
3Yes, I testify again to every man who receives circumcision, that he is a debtor to do the whole law.
3ሕግንም ሁሉ እንዲፈጽም ግድ አለበት ብዬ ለሚገረዙት ሁሉ ለእያንዳንዶች ደግሜ እመሰክራለሁ።
4You are alienated from Christ, you who desire to be justified by the law. You have fallen away from grace.
4በሕግ ልትጸድቁ የምትፈልጉ ከክርስቶስ ተለይታችሁ ከጸጋው ወድቃችኋል።
5For we, through the Spirit, by faith wait for the hope of righteousness.
5እኛ በመንፈስ ከእምነት የጽድቅን ተስፋ እንጠባበቃለንና።
6For in Christ Jesus neither circumcision amounts to anything, nor uncircumcision, but faith working through love.
6በክርስቶስ ኢየሱስ ሆኖ፥ በፍቅር የሚሠራ እምነት እንጂ መገረዝ ቢሆን ወይም አለመገረዝ አይጠቅምምና።
7You were running well! Who interfered with you that you should not obey the truth?
7በመልካም ትሮጡ ነበር፤ ለእውነት እንዳትታዘዙ ማን ከለከላችሁ?
8This persuasion is not from him who calls you.
8ይህ ማባበል ከሚጠራችሁ አልወጣም። ጥቂት እርሾ ሊጡን ሁሉ ያቦካል።
9A little yeast grows through the whole lump.
9የተለየ ነገር ከቶ እንዳታስቡ እኔ በጌታ ስለ እናንተ ታምኜአለሁ፤ የሚያናውጣችሁ ማንም ቢኖር ግን ፍርዱን ሊሸከም ነው።
10I have confidence toward you in the Lord that you will think no other way. But he who troubles you will bear his judgment, whoever he is.
11ነገር ግን፥ ወንድሞች ሆይ፥ እኔ ገና እስከ አሁን መገረዝን ብሰብክ እስከ አሁን ድረስ ለምን ያሳድዱኛል? እንኪያስ የመስቀል ዕንቅፋት ተወግዶአል።
11But I, brothers, if I still preach circumcision, why am I still persecuted? Then the stumbling block of the cross has been removed.
12የሚያውኩአችሁ ይቆረጡ።
12I wish that those who disturb you would cut themselves off.
13ወንድሞች ሆይ፥ እናንተ ለአርነት ተጠርታችኋልና፤ ብቻ አርነታችሁ ለሥጋ ምክንያትን አይስጥ፥ ነገር ግን በፍቅር እርስ በርሳችሁ እንደ ባሪያዎች ሁኑ።
13For you, brothers, were called for freedom. Only don’t use your freedom for gain to the flesh, but through love be servants to one another.
14ሕግ ሁሉ በአንድ ቃል ይፈጸማልና፥ እርሱም። ባልንጀራህን እንደ ራስህ ውደድ የሚል ነው።
14For the whole law is fulfilled in one word, in this: “You shall love your neighbor as yourself.” Leviticus 19:18
15ነገር ግን እርስ በርሳችሁ ብትነካከሱ ብትበላሉ እርስ በርሳችሁ እንዳትጠፋፉ ተጠንቀቁ።
15But if you bite and devour one another, be careful that you don’t consume one another.
16ነገር ግን እላለሁ፥ በመንፈስ ተመላለሱ፥ የሥጋንም ምኞት ከቶ አትፈጽሙ።
16But I say, walk by the Spirit, and you won’t fulfill the lust of the flesh.
17ሥጋ በመንፈስ ላይ መንፈስም በሥጋ ላይ ይመኛልና፥ እነዚህም እርስ በርሳቸው ይቀዋወማሉ፤ ስለዚህም የምትወዱትን ልታደርጉ አትችሉም።
17For the flesh lusts against the Spirit, and the Spirit against the flesh; and these are contrary to one another, that you may not do the things that you desire.
18በመንፈስ ብትመሩ ግን ከሕግ በታች አይደላችሁም።
18But if you are led by the Spirit, you are not under the law.
19የሥጋ ሥራም የተገለጠ ነው እርሱም ዝሙት፥ ርኵሰት፥
19Now the works of the flesh are obvious, which are: adultery, sexual immorality, uncleanness, lustfulness,
20መዳራት፥ ጣዖትን ማምለክ፥ ምዋርት፥ ጥል፥ ክርክር፥ ቅንዓት፥ ቁጣ፥ አድመኛነት፥
20idolatry, sorcery, hatred, strife, jealousies, outbursts of anger, rivalries, divisions, heresies,
21መለያየት፥ መናፍቅነት፥ ምቀኝነት፥ መግደል፥ ስካር፥ ዘፋኝነት፥ ይህንም የሚመስል ነው። አስቀድሜም እንዳልሁ፥ እንደዚህ ያሉትን የሚያደርጉ የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም።
21envyings, murders, drunkenness, orgies, and things like these; of which I forewarn you, even as I also forewarned you, that those who practice such things will not inherit the Kingdom of God.
22የመንፈስ ፍሬ ግን ፍቅር፥ ደስታ፥ ሰላም፥ ትዕግሥት፥ ቸርነት፥ በጎነት፥ እምነት፥ የውሃት፥ ራስን መግዛት ነው።
22But the fruit of the Spirit is love, joy, peace, patience, kindness, goodness, faith, or, faithfulness
23እንደዚህ ያሉትን የሚከለክል ሕግ የለም።
23gentleness, and self-control. Against such things there is no law.
24የክርስቶስ ኢየሱስም የሆኑቱ ሥጋን ከክፉ መሻቱና ከምኞቱ ጋር ሰቀሉ።
24Those who belong to Christ have crucified the flesh with its passions and lusts.
25በመንፈስ ብንኖር በመንፈስ ደግሞ እንመላለስ።
25If we live by the Spirit, let’s also walk by the Spirit.
26እርስ በርሳችን እየተነሣሣንና እየተቀናናን በከንቱ አንመካ።
26Let’s not become conceited, provoking one another, and envying one another.