1He entered and was passing through Jericho.
1ወደ ኢያሪኮም ገብቶ ያልፍ ነበር። እነሆም ዘኬዎስ የሚባል ሰው፥ እርሱም የቀራጮች አለቃ ነበረ፥ ባለ ጠጋም ነበረ።
2There was a man named Zacchaeus. He was a chief tax collector, and he was rich.
3ኢየሱስንም የትኛው እንደ ሆነ ሊያይ ይፈልግ ነበር፤ ቁመቱም አጭር ነበረና ስለ ሕዝቡ ብዛት አቃተው።
3He was trying to see who Jesus was, and couldn’t because of the crowd, because he was short.
4በዚያችም መንገድ ያልፍ ዘንድ አለውና ያየው ዘንድ ወደ ፊት ሮጦ በአንድ ሾላ ላይ ወጣ።
4He ran on ahead, and climbed up into a sycamore tree to see him, for he was to pass that way.
5ኢየሱስም ወደዚያ ስፍራ በደረሰ ጊዜ፥ አሻቅቦ አየና። ዘኬዎስ ሆይ፥ ዛሬ በቤትህ እውል ዘንድ ይገባኛልና ፈጥነህ ውረድ አለው።
5When Jesus came to the place, he looked up and saw him, and said to him, “Zacchaeus, hurry and come down, for today I must stay at your house.”
6ፈጥኖም ወረደ በደስታም ተቀበለው።
6He hurried, came down, and received him joyfully.
7ሁሉም አይተው። ከኃጢአተኛ ሰው ጋር ሊውል ገባ ብለው አንጐራጐሩ።
7When they saw it, they all murmured, saying, “He has gone in to lodge with a man who is a sinner.”
8ዘኬዎስ ግን ቆሞ ጌታን። ጌታ ሆይ፥ ካለኝ ሁሉ እኵሌታውን ለድሆች እሰጣለሁ፤ ማንንም በሐሰት ከስሼ እንደ ሆንሁ አራት እጥፍ እመልሳለሁ አለው።
8Zacchaeus stood and said to the Lord, “Behold, Lord, half of my goods I give to the poor. If I have wrongfully exacted anything of anyone, I restore four times as much.”
9ኢየሱስም። እርሱ ደግሞ የአብርሃም ልጅ ነውና ዛሬ ለዚህ ቤት መዳን ሆኖለታል፤
9Jesus said to him, “Today, salvation has come to this house, because he also is a son of Abraham.
10የሰው ልጅ የጠፋውን ሊፈልግና ሊያድን መጥቶአለና አለው።
10 For the Son of Man came to seek and to save that which was lost.”
11እነርሱም ይህን ሲሰሙ፥ ወደ ኢየሩሳሌም መቅረቡ ስለ ሆነ የእግዚአብሔርም መንግሥት ፈጥኖ ሊገለጥ እንዳለው ስለ መሰላቸው ምሳሌ ጭምር ተናገረ።
11As they heard these things, he went on and told a parable, because he was near Jerusalem, and they supposed that the Kingdom of God would be revealed immediately.
12ስለዚህም እንዲህ አላቸው። አንድ መኰንን ለራሱ መንግሥትን ይዞ ሊመለሰ ወደ ሩቅ አገር ሄደ።
12He said therefore, “A certain nobleman went into a far country to receive for himself a kingdom, and to return.
13አሥር ባሪያዎችንም ጠርቶ አሥር ምናን ሰጣቸውና። እስክመጣ ድረስ ነግዱ አላቸው።
13 He called ten servants of his, and gave them ten mina coins, 10 minas was more than 3 years’ wages for an agricultural laborer. and told them, ‘Conduct business until I come.’
14የአገሩ ሰዎች ግን ይጠሉት ነበርና። ይህ በላያችን ሊነግሥ አንወድም ብለው በኋላው መልክተኞችን ላኩ።
14 But his citizens hated him, and sent an envoy after him, saying, ‘We don’t want this man to reign over us.’
15መንግሥትንም ይዞ በተመለሰ ጊዜ፥ ገንዘብ የሰጣቸውን እነዚህን ባሪያዎች ነግደው ምን ያህል እንዳተረፉ ያውቅ ዘንድ እንዲጠሩለት አዘዘ።
15 “It happened when he had come back again, having received the kingdom, that he commanded these servants, to whom he had given the money, to be called to him, that he might know what they had gained by conducting business.
16የፊተኛውም ደርሶ። ጌታ ሆይ፥ ምናንህ አሥር ምናን አተረፈ አለው።
16 The first came before him, saying, ‘Lord, your mina has made ten more minas.’
17እርሱም። መልካም፥ አንተ በጎ ባሪያ፥ በጥቂት የታመንህ ስለ ሆንህ በአሥር ከተማዎች ላይ ሥልጣን ይሁንልህ አለው።
17 “He said to him, ‘Well done, you good servant! Because you were found faithful with very little, you shall have authority over ten cities.’
18ሁለተኛውም መጥቶ። ጌታ ሆይ፥ ምናንህ አምስት ምናን አተረፈ አለው።
18 “The second came, saying, ‘Your mina, Lord, has made five minas.’
19ይህንም ደግሞ። አንተም በአምስት ከተማዎች ላይ ሁን አለው።
19 “So he said to him, ‘And you are to be over five cities.’
20ሌላውም መጥቶ። ጌታ ሆይ፥ በጨርቅ ጠቅልዬ የጠበቅኋት ምናንህ እነሆ፤
20 Another came, saying, ‘Lord, behold, your mina, which I kept laid away in a handkerchief,
21ፈርቼሃለሁና፥ ጨካኝ ሰው ስለ ሆንህ፤ ያላኖርኸውን ትወስዳለህ ያልዘራኸውንም ታጭዳለህ አለው።
21 for I feared you, because you are an exacting man. You take up that which you didn’t lay down, and reap that which you didn’t sow.’
22እርሱም። አንተ ክፉ ባሪያ፥ አፍህ በተናገረው እፈርድብሃለሁ። እኔ ያላኖርሁትን የምወስድና ያልዘራሁትን የማጭድ ጨካኝ ሰው እንደ ሆንሁ አወቅህ፤ ምን ነው ገንዘቤን ለለዋጮች አደራ ያልሰጠኸው?
22 “He said to him, ‘Out of your own mouth will I judge you, you wicked servant! You knew that I am an exacting man, taking up that which I didn’t lay down, and reaping that which I didn’t sow.
23እኔም መጥቼ ከትርፉ ጋር እወስደው ነበር አለው።
23 Then why didn’t you deposit my money in the bank, and at my coming, I might have earned interest on it?’
24በዚያም ቆመው የነበሩትን። ምናኑን ውሰዱበት አሥሩ ምናን ላለውም ስጡት አላቸው።
24 He said to those who stood by, ‘Take the mina away from him, and give it to him who has the ten minas.’
25እነርሱም። ጌታ ሆይ፥ አሥር ምናን አለው አሉት።
25 “They said to him, ‘Lord, he has ten minas!’
26እላችኋለሁ፥ ላለው ሁሉ ይሰጠዋል፥ ከሌለው ግን ያው ያለው ስንኳ ይወሰድበታል።
26 ‘For I tell you that to everyone who has, will more be given; but from him who doesn’t have, even that which he has will be taken away from him.
27ነገር ግን እነዚያን በላያቸው ልነግሥ ያልወደዱትን ጠላቶቼን ወደዚህ አምጡአቸው በፊቴም እረዱአቸው።
27 But bring those enemies of mine who didn’t want me to reign over them here, and kill them before me.’”
28ይህንም ከተናገረ በኋላ፥ ወደ ኢየሩሳሌም ሲወጣ ይቀድማቸው ነበር።
28Having said these things, he went on ahead, going up to Jerusalem.
29ደብረ ዘይትም በሚባል ተራራ አጠገብ ወዳሉት ወደ ቤተ ፋጌና ወደ ቢታንያ በቀረበ ጊዜ፥ ከደቀ መዛሙርቱ ሁለቱን ላከና።
29It happened, when he drew near to Bethsphage TR, NU read “Bethpage” instead of “Bethsphage” and Bethany, at the mountain that is called Olivet, he sent two of his disciples,
30በፊታችሁ ወዳለችው መንደር ሂዱ፥ ወደ እርስዋም ገብታችሁ ከሰው ማንም ገና ያልተቀመጠበት ውርንጫ ታስሮ ታገኛላችሁ፥ ፈትታችሁም አምጡት።
30saying, “Go your way into the village on the other side, in which, as you enter, you will find a colt tied, whereon no man ever yet sat. Untie it, and bring it.
31ማንም። ስለ ምን ትፈቱታላችሁ? ብሎ ቢጠይቃችሁ፥ እንዲሁ። ለጌታ ያስፈልገዋል በሉ አላቸው።
31 If anyone asks you, ‘Why are you untying it?’ say to him: ‘The Lord needs it.’”
32የተላኩትም ሄደው እንዳላቸው አገኙ።
32Those who were sent went away, and found things just as he had told them.
33እነርሱም ውርንጫውን ሲፈቱ ጌቶቹ። ውርንጫውን ስለ ምን ትፈቱታላችሁ? አሉአቸውም
33As they were untying the colt, its owners said to them, “Why are you untying the colt?”
34እነርሱም። ለጌታ ያስፈልገዋል አሉ።
34They said, “The Lord needs it.”
35ወደ ኢየሱስም አመጡት፥ በውርንጫውም ላይ ልብሳቸውን ጭነው ኢየሱስን አስቀመጡት።
35They brought it to Jesus. They threw their cloaks on the colt, and set Jesus on them.
36ሲሄድም ልብሳቸውን በመንገድ ያነጥፉ ነበር።
36As he went, they spread their cloaks in the way.
37ወደ ደብረ ዘይት ቍልቍለትም አሁን በቀረበ ጊዜ፥ ደቀ መዛሙርቱ ሁላቸው ደስ እያላቸው ተአምራትን ሁሉ ስላዩ በታላቅ ድምፅ እግዚአብሔርን ሊያመሰግኑ ጀምረው።
37As he was now getting near, at the descent of the Mount of Olives, the whole multitude of the disciples began to rejoice and praise God with a loud voice for all the mighty works which they had seen,
38በጌታ ስም የሚመጣ ንጉሥ የተባረከ ነው፤ በሰማይ ሰላም በአርያምም ክብር አሉ።
38saying, “Blessed is the King who comes in the name of the Lord! Psalm 118:26 Peace in heaven, and glory in the highest!”
39ከሕዝብም መካከል ከፈሪሳውያን አንዳንዱ። መምህር ሆይ፥ ደቀ መዛሙርትህን ገሥጻቸው አሉት።
39Some of the Pharisees from the multitude said to him, “Teacher, rebuke your disciples!”
40መልሶም። እላችኋለሁ፥ እነዚህ ዝም ቢሉ ድንጋዮች ይጮኻሉ አላቸው።
40He answered them, “I tell you that if these were silent, the stones would cry out.”
41ሲቀርብም ከተማይቱን አይቶ አለቀሰላት፥
41When he drew near, he saw the city and wept over it,
42እንዲህ እያለ። ለሰላምሽ የሚሆነውን በዚህ ቀን አንቺስ ስንኳ ብታውቂ፤ አሁን ግን ከዓይንሽ ተሰውሮአል።
42saying, “If you, even you, had known today the things which belong to your peace! But now, they are hidden from your eyes.
43ወራት ይመጣብሻልና፥ ጠላቶችሽም ቅጥር ይቀጥሩብሻል ይከቡሻልም በየበኵሉም ያስጨንቁሻል፤
43 For the days will come on you, when your enemies will throw up a barricade against you, surround you, hem you in on every side,
44አንቺንም በአንቺም ውስጥ የሚኖሩትን ልጆችሽን ወደ ታች ይጥላሉ፥ በአንቺ ውስጥም ድንጋይ በድንጋይ ላይ አይተዉም፥ የመጐብኘትሽን ዘመን አላወቅሽምና።
44 and will dash you and your children within you to the ground. They will not leave in you one stone on another, because you didn’t know the time of your visitation.”
45ወደ መቅደስም ገብቶ በእርሱ የሚሸጡትን የሚገዙትንም ያወጣ ጀመር፤
45He entered into the temple, and began to drive out those who bought and sold in it,
46እርሱም። ቤቴ የጸሎት ቤት ይሆናል ተብሎ ተጽፎአል፤ እናንተ ግን የወንበዴዎች ዋሻ አደረጋችሁት አላቸው።
46saying to them, “It is written, ‘My house is a house of prayer,’ Isaiah 56:7 but you have made it a ‘den of robbers’!” Jeremiah 7:11
47ዕለት ዕለትም በመቅደስ ያስተምር ነበር፤ ነገር ግን የካህናት አለቆችና ጻፎች የሕዝቡ ታላላቆችም ሊገድሉት ይፈልጉ ነበር፥
47He was teaching daily in the temple, but the chief priests and the scribes and the leading men among the people sought to destroy him.
48የሚያደርጉበትንም አጡ፤ ሕዝቡ ሁሉ ሲሰሙት ተንጠልጥለውበት ነበርና።
48They couldn’t find what they might do, for all the people hung on to every word that he said.