1Now the feast of unleavened bread, which is called the Passover, drew near.
1ፋሲካም የሚባለው የቂጣ በዓል ቀረበ።
2The chief priests and the scribes sought how they might put him to death, for they feared the people.
2የካህናት አለቆችና ጻፎችም እንዴት እንዲያጠፉት ይፈልጉ ነበር፤ ሕዝቡን ይፈሩ ነበርና።
3Satan entered into Judas, who was surnamed Iscariot, who was numbered with the twelve.
3ሰይጣንም ከአሥራ ሁለቱ ቍጥር አንዱ በነበረው የአስቆሮቱ በሚባለው በይሁዳ ገባ፤
4He went away, and talked with the chief priests and captains about how he might deliver him to them.
4ሄዶም እንዴት አሳልፎ እንዲሰጣቸው ከካህናት አለቆችና ከመቅደስ አዛዦች ጋር ተነጋገረ።
5They were glad, and agreed to give him money.
5እነርሱም ደስ አላቸው፥ ገንዘብም ሊሰጡት ተዋዋሉ።
6He consented, and sought an opportunity to deliver him to them in the absence of the multitude.
6እሺም አለ፥ ሕዝብም በሌለበት አሳልፎ እንዲሰጣቸው ምቹ ጊዜ ይፈልግ ነበር።
7The day of unleavened bread came, on which the Passover must be sacrificed.
7ፋሲካንም ሊያርዱበት የሚገባው የቂጣ በዓል ደረሰ፤
8He sent Peter and John, saying, “Go and prepare the Passover for us, that we may eat.”
8ጴጥሮስንና ዮሐንስንም። ፋሲካን እንድንበላ ሄዳችሁ አዘጋጁልን ብሎ ላካቸው።
9They said to him, “Where do you want us to prepare?”
9እነርሱም። ወዴት እናዘጋጅ ዘንድ ትወዳለህ? አሉት።
10He said to them, “Behold, when you have entered into the city, a man carrying a pitcher of water will meet you. Follow him into the house which he enters.
10እርሱም አላቸው። እነሆ፥ ወደ ከተማ ስትገቡ ማድጋ ውኃ የተሸከመ ሰው ይገናኛችኋል፤ ወደ ሚገባበት ቤት ተከተሉት፤
11 Tell the master of the house, ‘The Teacher says to you, “Where is the guest room, where I may eat the Passover with my disciples?”’
11ለባለቤቱም። መምህሩ። ከደቀ መዛሙርቴ ጋር ፋሲካን የምበላበት የእንግዳ ቤት ክፍል ወዴት ነው? ይልሃል በሉት፤
12 He will show you a large, furnished upper room. Make preparations there.”
12ያም በደርብ ላይ ያለውን የተነጠፈ ታላቅ አዳራሽ ያሳያችኋል፤ በዚያም አሰናዱልን።
13They went, found things as he had told them, and they prepared the Passover.
13ሄደውም እንዳላቸው አገኙና ፋሲካን አሰናዱ።
14When the hour had come, he sat down with the twelve apostles.
14ሰዓቱም በደረሰ ጊዜ ከአሥራ ሁለቱ ሐዋርያት ጋር በማዕድ ተቀመጠ።
15He said to them, “I have earnestly desired to eat this Passover with you before I suffer,
15እርሱም። ከመከራዬ በፊት ከእናንተ ጋር ይህን ፋሲካ ልበላ እጅግ እመኝ ነበር፤
16 for I tell you, I will no longer by any means eat of it until it is fulfilled in the Kingdom of God.”
16እላችኋለሁና፥ በእግዚአብሔር መንግሥት እስኪፈጸም ድረስ፥ ወደ ፊት ከዚህ አልበላም አላቸው።
17He received a cup, and when he had given thanks, he said, “Take this, and share it among yourselves,
17ጽዋንም ተቀበለ አመስግኖም። ይህን እንካችሁ በመካከላችሁም ተካፈሉት፤
18 for I tell you, I will not drink at all again from the fruit of the vine, until the Kingdom of God comes.”
18እላችኋለሁና፥ የእግዚአብሔር መንግሥት እስክትመጣ ድረስ ከአሁን ጀምሮ ከወይኑ ፍሬ አልጠጣም አለ።
19He took bread, and when he had given thanks, he broke it, and gave to them, saying, “This is my body which is given for you. Do this in memory of me.”
19እንጀራንም አንሥቶ አመሰገነ ቆርሶም ሰጣቸውና። ስለ እናንተ የሚሰጠው ሥጋዬ ይህ ነው፤ ይህን ለመታሰቢያዬ አድርጉት አለ።
20Likewise, he took the cup after supper, saying, “This cup is the new covenant in my blood, which is poured out for you.
20እንዲሁም ከእራት በኋላ ጽዋውን አንሥቶ እንዲህ አለ። ይህ ጽዋ ስለ እናንተ በሚፈሰው በደሜ የሚሆን አዲስ ኪዳን ነው።
21 But behold, the hand of him who betrays me is with me on the table.
21ነገር ግን አሳልፎ የሚሰጠኝ እጅ እነሆ በማዕድ ከእኔ ጋር ናት።
22 The Son of Man indeed goes, as it has been determined, but woe to that man through whom he is betrayed!”
22የሰው ልጅስ እንደ ተወሰነው ይሄዳል፥ ነገር ግን አልፎ ለሚሰጥበት ለዚያ ሰው ወዮለት።
23They began to question among themselves, which of them it was who would do this thing.
23ከእነርሱም ይህን ሊያደርግ ያለው ማን እንደ ሆነ እርስ በርሳቸው ይጠያየቁ ጀመር።
24There arose also a contention among them, which of them was considered to be greatest.
24ደግሞም ማናቸውም ታላቅ ሆኖ እንዲቈጠር በመካከላቸው ክርክር ሆነ።
25He said to them, “The kings of the nations lord it over them, and those who have authority over them are called ‘benefactors.’
25እንዲህም አላቸው። የአሕዛብ ነገሥታት ይገዙአቸዋል፥ በላያቸውም የሚሠለጥኑት ቸርነት አድራጊዎች ይባላሉ።
26 But not so with you. But one who is the greater among you, let him become as the younger, and one who is governing, as one who serves.
26እናንተ ግን እንዲህ አትሁኑ፤ ነገር ግን ከእናንተ ታላቅ የሆነ በመካከላችሁ እንደ ታናሽ፥ የሚገዛም እንደሚያገለግል ይሁን።
27 For who is greater, one who sits at the table, or one who serves? Isn’t it he who sits at the table? But I am in the midst of you as one who serves.
27በማዕድ የተቀመጠ ወይስ የሚያገለግል ማናቸው ታላቅ ነው? የተቀመጠው አይደለምን? እኔ ግን በመካከላችሁ እንደሚያገለግል ነኝ።
28 But you are those who have continued with me in my trials.
28ነገር ግን እናንተ በፈተናዎቼ ከእኔ ጋር ጸንታችሁ የኖራችሁ ናችሁ፤
29 I confer on you a kingdom, even as my Father conferred on me,
29አባቴ እኔን እንደ ሾመኝ እኔ ደግሞ በመንግሥቴ ከማዕዴ ትበሉና ትጠጡ ዘንድ፥ በአሥራ ሁለቱ በእስራኤል ነገድ ስትፈርዱ በዙፋኖች ትቀመጡ ዘንድ ለመንግሥት እሾማችኋለሁ።
30 that you may eat and drink at my table in my Kingdom. You will sit on thrones, judging the twelve tribes of Israel.”
31ጌታም። ስምዖን ስምዖን ሆይ፥ እነሆ፥ ሰይጣን እንደ ስንዴ ሊያበጥራችሁ ለመነ፤
31The Lord said, “Simon, Simon, behold, Satan asked to have you, that he might sift you as wheat,
32እኔ ግን እምነትህ እንዳይጠፋ ስለ አንተ አማለድሁ፤ አንተም በተመለስህ ጊዜ ወንድሞችህን አጽና አለ።
32 but I prayed for you, that your faith wouldn’t fail. You, when once you have turned again, establish your brothers The word for “brothers” here may be also correctly translated “brothers and sisters” or “siblings.” .”
33እርሱም። ጌታ ሆይ፥ ወደ ወኅኒም ወደ ሞትም ከአንተ ጋር ለመሄድ የተዘጋጀሁ ነኝ አለው።
33He said to him, “Lord, I am ready to go with you both to prison and to death!”
34እርሱ ግን። ጴጥሮስ ሆይ፥ እልሃለሁ፥ እንዳታውቀኝ ሦስት ጊዜ እስክትክደኝ ድረስ ዛሬ ዶሮ አይጮኽም አለው።
34He said, “I tell you, Peter, the rooster will by no means crow today until you deny that you know me three times.”
35ደግሞም። ያለ ኮረጆና ያለ ከረጢት ያለ ጫማም በላክኋችሁ ጊዜ፥ አንዳች ጐደለባችሁን? አላቸው። እነርሱም። አንዳች እንኳ አሉ።
35He said to them, “When I sent you out without purse, and wallet, and shoes, did you lack anything?” They said, “Nothing.”
36እርሱም። አሁን ግን ኮረጆ ያለው ከእርሱ ጋር ይውሰድ፥ ከረጢትም ያለው እንዲሁ፤ የሌለውም ልብሱን ሽጦ ሰይፍ ይግዛ።
36Then he said to them, “But now, whoever has a purse, let him take it, and likewise a wallet. Whoever has none, let him sell his cloak, and buy a sword.
37እላችኋለሁና፥ ይህ። ከዓመፀኞች ጋር ተቈጠረ ተብሎ የተጻፈው በእኔ ሊፈጸም ግድ ነው፤ አዎን፥ ስለ እኔ የሚሆነው አሁን ይፈጸማልና አላቸው።
37 For I tell you that this which is written must still be fulfilled in me: ‘He was counted with transgressors.’ Isaiah 53:12 For that which concerns me has an end.”
38እነርሱም። ጌታ ሆይ፥ እነሆ፥ በዚህ ሁለት ሰይፎች አሉ አሉት። እርሱም። ይበቃል አላቸው።
38They said, “Lord, behold, here are two swords.” He said to them, “That is enough.”
39ወጥቶም እንደ ልማዱ ወደ ደብረ ዘይት ሄደ፤ ደቀ መዛሙርቱም ደግሞ ተከተሉት።
39He came out, and went, as his custom was, to the Mount of Olives. His disciples also followed him.
40ወደ ስፍራውም ደርሶ። ወደ ፈተና እንዳትገቡ ጸልዩ አላቸው።
40When he was at the place, he said to them, “Pray that you don’t enter into temptation.”
41ከእነርሱም የድንጋይ ውርወራ የሚያህል ራቀ፥ ተንበርክኮም። አባት ሆይ፥
41He was withdrawn from them about a stone’s throw, and he knelt down and prayed,
42ብትፈቅድ ይህችን ጽዋ ከእኔ ውሰድ፤ ነገር ግን የእኔ ፈቃድ አይሁን የአንተ እንጂ እያለ ይጸልይ ነበር።
42saying, “Father, if you are willing, remove this cup from me. Nevertheless, not my will, but yours, be done.”
43ከሰማይም መጥቶ የሚያበረታ መልአክ ታየው።
43An angel from heaven appeared to him, strengthening him.
44በፍርሃትም ሲጣጣር አጽንቶ ይጸልይ ነበር፤ ወዙም በምድር ላይ እንደሚወርድ እንደ ደም ነጠብጣብ ነበረ።
44Being in agony he prayed more earnestly. His sweat became like great drops of blood falling down on the ground.
45ከጸሎትም ተነሥቶ ወደ ደቀ መዛሙርቱ መጣና ከኀዘን የተነሣ ተኝተው ሲያገኛቸው።
45When he rose up from his prayer, he came to the disciples, and found them sleeping because of grief,
46ስለ ምን ትተኛላችሁ? ወደ ፈተና እንዳትገቡ ተነሥታችሁ ጸልዩ አላቸው።
46and said to them, “Why do you sleep? Rise and pray that you may not enter into temptation.”
47ገናም ሲናገር እነሆ፥ ሰዎች መጡ፤ ከአሥራ ሁለቱ አንዱም ይሁዳ የሚባለው ይቀድማቸው ነበር፥ ሊስመውም ወደ ኢየሱስ ቀረበ።
47While he was still speaking, behold, a multitude, and he who was called Judas, one of the twelve, was leading them. He came near to Jesus to kiss him.
48ኢየሱስ ግን። ይሁዳ ሆይ፥ በመሳም የሰውን ልጅ አሳልፈህ ትሰጣለህን? አለው።
48But Jesus said to him, “Judas, do you betray the Son of Man with a kiss?”
49በዙሪያውም የነበሩት የሚሆነውን ባዩ ጊዜ። ጌታ ሆይ፥ በሰይፍ እንምታቸውን? አሉት።
49When those who were around him saw what was about to happen, they said to him, “Lord, shall we strike with the sword?”
50ከእነርሱም አንዱ የሊቀ ካህናቱን ባሪያ መትቶ ቀኝ ጆሮውን ቈረጠው።
50A certain one of them struck the servant of the high priest, and cut off his right ear.
51ኢየሱስ ግን መልሶ። ይህንስ ፍቀዱ አለ፤ ጆሮውንም ዳስሶ ፈወሰው።
51But Jesus answered, “Let me at least do this” —and he touched his ear, and healed him.
52ኢየሱስም ወደ እርሱ ለመጡበት ለካህናት አለቆችና ለመቅደስ አዛዦች ለሽማግሌዎችም። ወንበዴን እንደምትይዙ ሰይፍና ጐመድ ይዛችሁ ወጣችሁን?
52Jesus said to the chief priests, captains of the temple, and elders, who had come against him, “Have you come out as against a robber, with swords and clubs?
53በመቅደስ ዕለት ዕለት ከእናንተ ጋር ስሆን እጆቻችሁን አልዘረጋችሁብኝም፤ ይህ ግን ጊዜያችሁና የጨለማው ሥልጣን ነው አላቸው።
53 When I was with you in the temple daily, you didn’t stretch out your hands against me. But this is your hour, and the power of darkness.”
54ይዘውም ወሰዱት ወደ ሊቀ ካህናት ቤትም አገቡት፤ ጴጥሮስም ርቆ ይከተለው ነበር።
54They seized him, and led him away, and brought him into the high priest’s house. But Peter followed from a distance.
55በግቢ መካከልም እሳት አንድደው በአንድነት ተቀምጠው ሳሉ ጴጥሮስ በመካከላቸው ተቀመጠ።
55When they had kindled a fire in the middle of the courtyard, and had sat down together, Peter sat among them.
56በብርሃኑም በኩል ተቀምጦ ሳለ አንዲት ገረድ አየችውና ትኵር ብላ። ይህ ደግሞ ከእርሱ ጋር ነበረ አለች።
56A certain servant girl saw him as he sat in the light, and looking intently at him, said, “This man also was with him.”
57እርሱ ግን። አንቺ ሴት፥ አላውቀውም ብሎ ካደ።
57He denied Jesus, saying, “Woman, I don’t know him.”
58ከጥቂት ጊዜም በኋላ ሌላው አይቶት። አንተ ደግሞ ከእነርሱ ወገን ነህ አለው። ጴጥሮስ ግን። አንተ ሰው፥ እኔ አይደለሁም አለ።
58After a little while someone else saw him, and said, “You also are one of them!” But Peter answered, “Man, I am not!”
59አንድ ሰዓትም የሚያህል ቆይቶ ሌላው አስረግጦ። እርሱ የገሊላ ሰው ነውና በእውነት ይህ ደግሞ ከእርሱ ጋር ነበረ አለ።
59After about one hour passed, another confidently affirmed, saying, “Truly this man also was with him, for he is a Galilean!”
60ጴጥሮስ ግን። አንተ ሰው፥ የምትለውን አላውቅም አለ። ያን ጊዜም ገና ሲናገር ዶሮ ጮኸ።
60But Peter said, “Man, I don’t know what you are talking about!” Immediately, while he was still speaking, a rooster crowed.
61ጌታም ዘወር ብሎ ጴጥሮስን ተመለከተው፤ ጴጥሮስም። ዛሬ ዶሮ ሳይጮኽ ሦስት ጊዜ ትክደኛለህ እንዳለው የጌታ ቃል ትዝ አለው።
61The Lord turned, and looked at Peter. Then Peter remembered the Lord’s word, how he said to him, “Before the rooster crows you will deny me three times.”
62ጴጥሮስም ወደ ውጭ ወጥቶ ምርር ብሎ አለቀሰ።
62He went out, and wept bitterly.
63ኢየሱስንም የያዙት ሰዎች ይዘብቱበትና ይደበድቡት ነበር፤
63The men who held Jesus mocked him and beat him.
64ሸፍነውም ፊቱን ይመቱት ነበርና። በጥፊ የመታህ ማን ነው? ትንቢት ተናገር እያሉ ይጠይቁት ነበር።
64Having blindfolded him, they struck him on the face and asked him, “Prophesy! Who is the one who struck you?”
65ሌላም ብዙ ነገር እየተሳደቡ በእርሱ ላይ ይናገሩ ነበር።
65They spoke many other things against him, insulting him.
66በነጋም ጊዜ የሕዝቡ ሽማግሌዎችና የካህናት አለቆች ጻፎችም ተሰብስበው ወደ ሸንጎአቸው ወሰዱትና
66As soon as it was day, the assembly of the elders of the people was gathered together, both chief priests and scribes, and they led him away into their council, saying,
67ክርስቶስ አንተ ነህን? ንገረን አሉት። እርሱ ግን እንዲህ አላቸው። ብነግራችሁ አታምኑም፤
67“If you are the Christ, tell us.” But he said to them, “If I tell you, you won’t believe,
68ብጠይቅም አትመልሱልኝም አትፈቱኝምም።
68 and if I ask, you will in no way answer me or let me go.
69ነገር ግን ከአሁን ጀምሮ የሰው ልጅ በእግዚአብሔር ኃይል ቀኝ ይቀመጣል።
69 From now on, the Son of Man will be seated at the right hand of the power of God.”
70ሁላቸውም። እንግዲያስ አንተ የእግዚአብሔር ልጅ ነህን? አሉት። እርሱም። እኔ እንደ ሆንሁ እናንተ ትላላችሁ አላቸው።
70They all said, “Are you then the Son of God?” He said to them, “You say it, because I am.”
71እነርሱም። ራሳችን ከአፉ ሰምተናልና ከእንግዲህ ወዲህ ምን ምስክር ያስፈልገናል? አሉ።
71They said, “Why do we need any more witness? For we ourselves have heard from his own mouth!”