1But on the first day of the week, at early dawn, they and some others came to the tomb, bringing the spices which they had prepared.
1ነገር ግን ከሳምንቱ በመጀመሪያው ቀን ያዘጋጁትን ሽቱ ይዘው ከእነርሱም ጋር አንዳንዶቹ ወደ መቃብሩ እጅግ ማልደው መጡ።
2They found the stone rolled away from the tomb.
2ድንጋዩንም ከመቃብሩ ተንከባሎ አገኙት፥
3They entered in, and didn’t find the Lord Jesus’ body.
3ገብተውም የጌታን የኢየሱስን ሥጋ አላገኙም።
4It happened, while they were greatly perplexed about this, behold, two men stood by them in dazzling clothing.
4እነርሱም በዚህ ሲያመነቱ፥ እነሆ፥ ሁለት ሰዎች የሚያንጸባርቅ ልብስ ለብሰው ወደ እነርሱ ቀረቡ፤
5Becoming terrified, they bowed their faces down to the earth. They said to them, “Why do you seek the living among the dead?
5ፈርተውም ፊታቸውን ወደ ምድር አቀርቅረው ሳሉ፥ እንዲህ አሉአቸው። ሕያውን ከሙታን መካከል ስለ ምን ትፈልጋላችሁ? ተነሥቶአል እንጂ በዚህ የለም።
6He isn’t here, but is risen. Remember what he told you when he was still in Galilee,
6የሰው ልጅ በኃጢአተኞች እጅ አልፎ ሊሰጥና ሊሰቀል በሦስተኛውም ቀን ሊነሣ ግድ ነው እያለ ገና በገሊላ ሳለ ለእናንተ እንደ ተናገረ አስቡ።
7saying that the Son of Man must be delivered up into the hands of sinful men, and be crucified, and the third day rise again?”
8ቃሎቹንም አሰቡ፥ ከመቃብሩም ተመልሰው ይህን ሁሉ ለአሥራ አንዱና ለሌሎች ሁሉ ነገሩአቸው።
8They remembered his words,
10ይህንም ለሐዋርያት የነገሩአቸው መግደላዊት ማርያምና ዮሐና የያዕቆብም እናት ማርያም ከእነርሱም ጋር የነበሩት ሌሎች ሴቶች ነበሩ።
9returned from the tomb, and told all these things to the eleven, and to all the rest.
11ይህም ቃል ቅዠት መስሎ ታያቸውና አላመኑአቸውም።
10Now they were Mary Magdalene, Joanna, and Mary the mother of James. The other women with them told these things to the apostles.
12ጴጥሮስ ግን ተነሥቶ ወደ መቃብር ሮጠ፤ በዚያም ዝቅ ብሎ ሲመለከት የተልባ እግር ልብስን ብቻ አየ፤ በሆነውም ነገር እየተደነቀ ወደ ቤቱ ሄደ።
11These words seemed to them to be nonsense, and they didn’t believe them.
13እነሆም፥ ከእነርሱ ሁለቱ በዚያ ቀን ከኢየሩሳሌም ስድሳ ምዕራፍ ያህል ወደሚርቅ ኤማሁስ ወደሚባል መንደር ይሄዱ ነበር፤
12But Peter got up and ran to the tomb. Stooping and looking in, he saw the strips of linen lying by themselves, and he departed to his home, wondering what had happened.
14ስለዚህም ስለ ሆነው ነገር ሁሉ እርስ በርሳቸው ይነጋገሩ ነበር።
13Behold, two of them were going that very day to a village named Emmaus, which was sixty stadia 60 stadia = about 11 kilometers or about 7 miles. from Jerusalem.
15ሲነጋገሩና ሲመራመሩም፥ ኢየሱስ ራሱ ቀርቦ ከእነርሱ ጋር ይሄድ ነበር፤
14They talked with each other about all of these things which had happened.
16ነገር ግን እንዳያውቁት ዓይናቸው ተይዞ ነበር።
15It happened, while they talked and questioned together, that Jesus himself came near, and went with them.
17እርሱም። እየጠወለጋችሁ ስትሄዱ፥ እርስ በርሳችሁ የምትነጋገሩአቸው እነዚህ ነገሮች ምንድር ናቸው? አላቸው።
16But their eyes were kept from recognizing him.
18ቀለዮጳ የሚባልም አንዱ መልሶ። አንተ በኢየሩሳሌም እንግዳ ሆነህ ለብቻህ ትኖራለህን? በእነዚህ ቀኖች በዚያ የሆነውን ነገር አታውቅምን? አለው።
17He said to them, “What are you talking about as you walk, and are sad?”
19እርሱም። ይህ ምንድር ነው? አላቸው። እነርሱም እንዲህ አሉት። በእግዚአብሔርና በሕዝቡ ሁሉ ፊት በሥራና በቃል ብርቱ ነቢይ ስለ ነበረው ስለ ናዝሬቱ ስለ ኢየሱስ፤
18One of them, named Cleopas, answered him, “Are you the only stranger in Jerusalem who doesn’t know the things which have happened there in these days?”
20እርሱንም የካህናት አለቆችና መኳንንቶቻችን ለሞት ፍርድ እንዴት አሳልፈው እንደ ሰጡትና እንደ ሰቀሉት ነው።
19He said to them, “What things?” They said to him, “The things concerning Jesus, the Nazarene, who was a prophet mighty in deed and word before God and all the people;
21እኛ ግን እስራኤልን እንዲቤዥ ያለው እርሱ እንደ ሆነ ተስፋ አድርገን ነበር፤ ደግሞም ከዚህ ሁሉ ጋር ይህ ከሆነ ዛሬ ሦስተኛው ቀን ነው።
20and how the chief priests and our rulers delivered him up to be condemned to death, and crucified him.
22ደግሞም ከእኛ ውስጥ ማልደው ከመቃብሩ ዘንድ የነበሩት አንዳንድ ሴቶች አስገረሙን፤
21But we were hoping that it was he who would redeem Israel. Yes, and besides all this, it is now the third day since these things happened.
23ሥጋውንም ባጡ ጊዜ። ሕያው ነው የሚሉ የመላእክትን ራእይ ደግሞ አየን ሲሉ መጥተው ነበር።
22Also, certain women of our company amazed us, having arrived early at the tomb;
24ከእኛም ጋር ከነበሩት ወደ መቃብር ሄደው ሴቶች እንደ ተናገሩት ሆኖ አገኙት፥ እርሱን ግን አላዩትም።
23and when they didn’t find his body, they came saying that they had also seen a vision of angels, who said that he was alive.
25እርሱም። እናንተ የማታስተውሉ፥ ነቢያትም የተናገሩትን ሁሉ ልባችሁ ከማመን የዘገየ፤
24Some of us went to the tomb, and found it just like the women had said, but they didn’t see him.”
26ክርስቶስ ይህን መከራ ይቀበል ዘንድና ወደ ክብሩ ይገባ ዘንድ ይገባው የለምን? አላቸው።
25He said to them, “Foolish men, and slow of heart to believe in all that the prophets have spoken!
27ከሙሴና ከነቢያት ሁሉ ጀምሮ ስለ እርሱ በመጻሕፍት ሁሉ የተጻፈውን ተረጐመላቸው።
26 Didn’t the Christ have to suffer these things and to enter into his glory?”
28ወደሚሄዱበትም መንደር ቀረቡ፥ እርሱም ሩቅ የሚሄድ መሰላቸው።
27Beginning from Moses and from all the prophets, he explained to them in all the Scriptures the things concerning himself.
29እነርሱ። ከእኛ ጋር እደር፥ ማታ ቀርቦአልና ቀኑም ሊመሽ ጀምሮአል ብለው ግድ አሉት፤ ከእነርሱም ጋር ሊያድር ገባ።
28They drew near to the village, where they were going, and he acted like he would go further.
30ከእነርሱም ጋር በማዕድ ተቀምጦ ሳለ እንጀራውን አንሥቶ ባረከው፥ ቈርሶም ሰጣቸው፤
29They urged him, saying, “Stay with us, for it is almost evening, and the day is almost over.” He went in to stay with them.
31ዓይናቸውም ተከፈተ፥ አወቁትም፤ እርሱም ከእነርሱ ተሰወረ።
30It happened, that when he had sat down at the table with them, he took the bread and gave thanks. Breaking it, he gave to them.
32እርስ በርሳቸውም። በመንገድ ሲናገረን መጻሕፍትንም ሲከፍትልን ልባችን ይቃጠልብን አልነበረምን? ተባባሉ።
31Their eyes were opened, and they recognized him, and he vanished out of their sight.
33በዚያችም ሰዓት ተነሥተው ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ፥ አሥራ አንዱና ከእነርሱ ጋር የነበሩትም። ጌታ በእውነት ተነሥቶአል ለስምዖንም ታይቶአል እያሉ በአንድነት ተሰብስበው አገኙአቸው።
32They said one to another, “Weren’t our hearts burning within us, while he spoke to us along the way, and while he opened the Scriptures to us?”
35እነርሱም በመንገድ የሆነውን እንጀራውንም በቈረሰ ጊዜ እንዴት እንደ ታወቀላቸው ተረኩላቸው።
33They rose up that very hour, returned to Jerusalem, and found the eleven gathered together, and those who were with them,
36ይህንም ሲነጋገሩ ኢየሱስ ራሱ በመካከላቸው ቆሞ። ሰላም ለእናንተ ይሁን አላቸው።
34saying, “The Lord is risen indeed, and has appeared to Simon!”
37ነገር ግን ደነገጡና ፈሩ መንፈስም ያዩ መሰላቸው።
35They related the things that happened along the way, and how he was recognized by them in the breaking of the bread.
38እርሱም። ስለ ምን ትደነግጣላችሁ? ስለ ምንስ አሳብ በልባችሁ ይነሣል?
36As they said these things, Jesus himself stood among them, and said to them, “Peace be to you.”
39እኔ ራሴ እንደ ሆንሁ እጆቼንና እግሮቼን እዩ፤ በእኔ እንደምታዩት፥ መንፈስ ሥጋና አጥንት የለውምና እኔን ዳስሳችሁ እዩ አላቸው።
37But they were terrified and filled with fear, and supposed that they had seen a spirit.
40ይህንም ብሎ እጆቹንና እግሮቹን አሳያቸው።
38He said to them, “Why are you troubled? Why do doubts arise in your hearts?
41እነርሱም ከደስታ የተነሣ ገና ስላላመኑ ሲደነቁ ሳሉ። በዚህ አንዳች የሚበላ አላችሁን? አላቸው።
39 See my hands and my feet, that it is truly me. Touch me and see, for a spirit doesn’t have flesh and bones, as you see that I have.”
42እነርሱም ከተጠበሰ ዓሣ አንድ ቁራጭ፥ ከማር ወለላም ሰጡት፤
40When he had said this, he showed them his hands and his feet.
43ተቀብሎም በፊታቸው በላ።
41While they still didn’t believe for joy, and wondered, he said to them, “Do you have anything here to eat?”
44እርሱም። ከእናንተ ጋር ሳለሁ በሙሴ ሕግና በነቢያት በመዝሙራትም ስለ እኔ የተጻፈው ሁሉ ይፈጸም ዘንድ ይገባል ብዬ የነገርኋችሁ ቃሌ ይህ ነው አላቸው።
42They gave him a piece of a broiled fish and some honeycomb.
45በዚያን ጊዜም መጻሕፍትን ያስተውሉ ዘንድ አእምሮአቸውን ከፈተላቸው፤
43He took them, and ate in front of them.
46እንዲህም አላቸው። ክርስቶስ መከራ ይቀበላል በሦስተኛውም ቀን ከሙታን ይነሣል፥
44He said to them, “This is what I told you, while I was still with you, that all things which are written in the law of Moses, the prophets, and the psalms, concerning me must be fulfilled.”
47በስሙም ንስሐና የኃጢአት ስርየት ከኢየሩሳሌም ጀምሮ በአሕዛብ ሁሉ ይሰበካል ተብሎ እንዲሁ ተጽፎአል።
45Then he opened their minds, that they might understand the Scriptures.
48እናንተም ለዚህ ምስክሮች ናችሁ።
46He said to them, “Thus it is written, and thus it was necessary for the Christ to suffer and to rise from the dead the third day,
49እነሆም፥ አባቴ የሰጠውን ተስፋ እኔ እልክላችኋለሁ፤ እናንተ ግን ከላይ ኃይል እስክትለብሱ ድረስ በኢየሩሳሌም ከተማ ቆዩ።
47 and that repentance and remission of sins should be preached in his name to all the nations, beginning at Jerusalem.
50እስከ ቢታንያም አወጣቸው እጆቹንም አንሥቶ ባረካቸው።
48 You are witnesses of these things.
51ሲባርካቸውም ከእነርሱ ተለየ ወደ ሰማይም ዐረገ።
49 Behold, I send forth the promise of my Father on you. But wait in the city of Jerusalem until you are clothed with power from on high.”
52እነርሱም፤ ሰገዱለትና በብዙ ደስታ ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ፥
50He led them out as far as Bethany, and he lifted up his hands, and blessed them.
53ዘወትርም እግዚአብሔርን እያመሰገኑና እየባረኩ በመቅደስ ኖሩ።
51It happened, while he blessed them, that he withdrew from them, and was carried up into heaven.
52They worshiped him, and returned to Jerusalem with great joy,
53and were continually in the temple, praising and blessing God. Amen.