1He entered again into the synagogue, and there was a man there who had his hand withered.
1ደግሞም ወደ ምኵራብ ገባ፥ በዚያም እጁ የሰለለች ሰው ነበር፤
2They watched him, whether he would heal him on the Sabbath day, that they might accuse him.
2ሊከሱትም፥ በሰንበት ይፈውሰው እንደ ሆነ ይጠባበቁት ነበር።
3He said to the man who had his hand withered, “Stand up.”
3እጁ የሰለለችውንም ሰው። ተነሥተህ ወደ መካከል ና አለው።
4He said to them, “Is it lawful on the Sabbath day to do good, or to do harm? To save a life, or to kill?” But they were silent.
4በሰንበት በጎ ማድረግ ተፈቅዶአልን? ወይስ ክፉ? ነፍስ ማዳን ወይስ መግደል? አላቸው፤ እነርሱም ዝም አሉ።
5When he had looked around at them with anger, being grieved at the hardening of their hearts, he said to the man, “Stretch out your hand.” He stretched it out, and his hand was restored as healthy as the other.
5ስለ ልባቸውም ድንዛዜ አዝኖ ዙሪያውን እየተመለከተ በቍጣ አያቸው፥ ሰውየውንም። እጅህን ዘርጋ አለው።
6The Pharisees went out, and immediately conspired with the Herodians against him, how they might destroy him.
6ዘረጋትም፥ እጁም ዳነች። ፈሪሳውያንም ወጥተው ወዲያው እንዴት አድርገው እንዲያጠፉት ከሄሮድስ ወገን ጋር ተማከሩበት።
7Jesus withdrew to the sea with his disciples, and a great multitude followed him from Galilee, from Judea,
7ኢየሱስም ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ወደ ባህር ፈቀቅ አለ፤ ከገሊላ የመጡም ብዙ ሰዎች ተከተሉት፤
8from Jerusalem, from Idumaea, beyond the Jordan, and those from around Tyre and Sidon. A great multitude, hearing what great things he did, came to him.
8እንዴት ትልቅ ነገርም እንዳደረገው ሰምተው ብዙ ሰዎች ከይሁዳ ከኢየሩሳሌምም ከኤዶምያስም ከዮርዳኖስ ማዶም ከጢሮስና ከሲዶና ምድርም ወደ እርሱ መጡ።
9He spoke to his disciples that a little boat should stay near him because of the crowd, so that they wouldn’t press on him.
9ሰዎቹም እንዳያጋፉት ታንኳን ያቆዩለት ዘንድ ደቀ መዛሙርቱን አዘዛቸው፤
10For he had healed many, so that as many as had diseases pressed on him that they might touch him.
10ብዙ ሰዎችን አድኖ ነበርና፥ ስለዚህም ሥቃይ ያለባቸው ሁሉ እንዲዳስሱት ይወድቁበት ነበር።
11The unclean spirits, whenever they saw him, fell down before him, and cried, “You are the Son of God!”
11ርኵሳን መናፍስትም ባዩት ጊዜ በፊቱ ተደፍተው። አንተ የእግዚአብሔር ልጅ ነህ እያሉ ጮኹ።
12He sternly warned them that they should not make him known.
12እንዳይገልጡትም በጣም አዘዛቸው።
13He went up into the mountain, and called to himself those whom he wanted, and they went to him.
13ወደ ተራራም ወጣ፥ ራሱም የወደዳቸውን ወደ እርሱ ጠራ፥ ወደ እርሱም ሄዱ።
14He appointed twelve, that they might be with him, and that he might send them out to preach,
14ከእርሱም ጋር እንዲኖሩና ለመስበክ እንዲልካቸው፥
15and to have authority to heal sicknesses and to cast out demons:
15ድውዮችንም ሊፈውሱ አጋንንትንም ሊያወጡ ሥልጣን ይሆንላቸው ዘንድ አሥራ ሁለት አደረገ፤
16Simon, to whom he gave the name Peter;
16ስምዖንንም ጴጥሮስ ብሎ ሰየመው፤
17James the son of Zebedee; John, the brother of James, and he surnamed them Boanerges, which means, Sons of Thunder;
17የዘብዴዎስንም ልጅ ያዕቆብን የያዕቆብንም ወንድም ዮሐንስን ቦአኔርጌስ ብሎ ሰየማቸው፥ የነጎድጓድ ልጆች ማለት ነው፤
18Andrew; Philip; Bartholomew; Matthew; Thomas; James, the son of Alphaeus; Thaddaeus; Simon the Zealot;
18እንድርያስንም ፊልጶስንም በርተሎሜውስንም ማቴዎስንም ቶማስንም የእልፍዮስን ልጅ ያዕቆብንም ታዴዎስንም ቀነናዊውንም ስምዖንን፥
19and Judas Iscariot, who also betrayed him. He came into a house.
19አሳልፎ የሰጠውንም የአስቆሮቱን ይሁዳን።
20The multitude came together again, so that they could not so much as eat bread.
20ወደ ቤትም መጡ፤ እንጀራም መብላት ስንኳ እስኪሳናቸው ድረስ እንደ ገና ብዙ ሰዎች ተሰበሰቡ።
21When his friends heard it, they went out to seize him: for they said, “He is insane.”
21ዘመዶቹም ሰምተው። አበደ ብለዋልና ሊይዙት ወጡ።
22The scribes who came down from Jerusalem said, “He has Beelzebul,” and, “By the prince of the demons he casts out the demons.”
22ከኢየሩሳሌም የወረዱ ጻፎችም። ብዔል ዜቡል አለበት፤ ደግሞ። በአጋንንት አለቃ አጋንንትን ያወጣል ብለው ተናገሩ።
23He summoned them, and said to them in parables, “How can Satan cast out Satan?
23እነርሱንም ወደ እርሱ ጠርቶ በምሳሌ አላቸው። ሰይጣን ሰይጣንን ሊያወጣው እንዴት ይችላል?
24 If a kingdom is divided against itself, that kingdom cannot stand.
24መንግሥትም እርስ በርስዋ ከተለያየች ያች መንግሥት ልትቆም አትችልም፤
25 If a house is divided against itself, that house cannot stand.
25ቤትም እርስ በርሱ ከተለያየ ያ ቤት ሊቆም አይችልም።
26 If Satan has risen up against himself, and is divided, he can’t stand, but has an end.
26ሰይጣንም ራሱን ተቃውሞ ከተለያየ፥ መጨረሻ ይሆንበታል እንጂ ሊቆም አይችልም።
27 But no one can enter into the house of the strong man to plunder, unless he first binds the strong man; and then he will plunder his house.
27ነገር ግን አስቀድሞ ኃይለኛውን ሳያስር ወደ ኃይለኛው ቤት ገብቶ ዕቃውን ሊበዘብዝ የሚችል የለም፥ ከዚያም ወዲያ ቤቱን ይበዘብዛል።
28 Most certainly I tell you, all sins of the descendants of man will be forgiven, including their blasphemies with which they may blaspheme;
28እውነት እላችኋለሁ፥ ለሰው ልጆች ኃጢአት ሁሉ የሚሳደቡትም ስድብ ሁሉ ይሰረይላቸዋል፤
29 but whoever may blaspheme against the Holy Spirit never has forgiveness, but is guilty of an eternal sin”
29በመንፈስ ቅዱስ ላይ የሚሳደብ ሁሉ ግን የዘላለም ኃጢአት ዕዳ ይሆንበታል እንጂ ለዘላለም አይሰረይለትም።
30—because they said, “He has an unclean spirit.”
30ርኵስ መንፈስ አለበት ይሉ ነበርና።
31His mother and his brothers came, and standing outside, they sent to him, calling him.
31እናቱና ወንድሞቹም መጡ በውጭም ቆመው ወደ እርሱ ልከው አስጠሩት።
32A multitude was sitting around him, and they told him, “Behold, your mother, your brothers, and your sisters TR omits “your sisters” are outside looking for you.”
32ብዙ ሰዎችም በዙሪያው ተቀምጠው ነበሩና። እነሆ፥ እናትህ ወንድሞችህም በውጭ ቆመው ይፈልጉሃል አሉት።
33He answered them, “Who are my mother and my brothers?”
33መልሶም። እናቴ ማን ናት? ወንድሞቼስ እነ ማን ናቸው? አላቸው።
34Looking around at those who sat around him, he said, “Behold, my mother and my brothers!
34በዙሪያው ተቀምጠው ወደ ነበሩትም ተመለከተና። እነሆ እናቴ ወንድሞቼም።
35 For whoever does the will of God, the same is my brother, and my sister, and mother.”
35የእግዚአብሔርን ፈቃድ የሚያደርግ ሁሉ፥ እርሱ ወንድሜ ነው እኅቴም እናቴም አለ።