World English Bible

Amharic: New Testament

Mark

7

1Then the Pharisees, and some of the scribes gathered together to him, having come from Jerusalem.
1ፈሪሳውያንና ከጻፎች ወገን ከኢየሩሳሌም የመጡትም ወደ እርሱ ተሰበሰቡ።
2Now when they saw some of his disciples eating bread with defiled, that is, unwashed, hands, they found fault.
2ከደቀ መዛሙርቱም አንዳንድ በርኵስ ማለት ባልታጠበ እጅ እንጀራ ሲበሉ አዩ።
3(For the Pharisees, and all the Jews, don’t eat unless they wash their hands and forearms, holding to the tradition of the elders.
3ፈሪሳውያንና አይሁድም ሁሉ የሽማግሎችን ወግ ሲጠብቁ እጃቸውን ደኅና አድርገው ሳይታጠቡ አይበሉምና፥
4They don’t eat when they come from the marketplace, unless they bathe themselves, and there are many other things, which they have received to hold to: washings of cups, pitchers, bronze vessels, and couches.)
4ከገበያም ተመልሰው ካልታጠቡ አይበሉም፥ ጽዋንም ማድጋንም የናስ ዕቃንም አልጋንም እንደ ማጠብ ሌላ ነገር ሊጠብቁት የተቀበሉት ብዙ አለ።
5The Pharisees and the scribes asked him, “Why don’t your disciples walk according to the tradition of the elders, but eat their bread with unwashed hands?”
5ፈሪሳውያንም ጻፎችም። ደቀ መዛሙርትህ እንደ ሽማግሌዎች ወግ ስለ ምን አይሄዱም? ነገር ግን እጃቸውን ሳይታጠቡ እንጀራ ይበላሉ ብለው ጠየቁት።
6He answered them, “Well did Isaiah prophesy of you hypocrites, as it is written, ‘This people honors me with their lips, but their heart is far from me.
6እርሱ ግን እንዲህ አላቸው። ኢሳይያስ ስለ እናንተ ስለ ግብዞች። ይህ ሕዝብ በከንፈሩ ያከብረኛል ልቡ ግን ከእኔ በጣም የራቀ ነው፤
7 But in vain do they worship me, teaching as doctrines the commandments of men.’
7የሰውም ሥርዓት የሆነ ትምህርት እያስተማሩ በከንቱ ያመልኩኛል ተብሎ እንደ ተጻፈ በእውነት ትንቢት ተናገረ።
8 “For you set aside the commandment of God, and hold tightly to the tradition of men—the washing of pitchers and cups, and you do many other such things.”
8የእግዚአብሔርን ትእዛዝ ትታችሁ ጽዋን ማድጋንም እንደ ማጠብ የሰውን ወግ ትጠብቃላችሁ፥ ይህንም የመሰለ ብዙ ሌላ ነገር ታደርጋላችሁ።
9He said to them, “Full well do you reject the commandment of God, that you may keep your tradition.
9እንዲህም አላቸው። ወጋችሁን ትጠብቁ ዘንድ የእግዚአብሔርን ትእዛዝ እጅግ ንቃችኋል።
10 For Moses said, ‘Honor your father and your mother;’ and, ‘He who speaks evil of father or mother, let him be put to death.’
10ሙሴ። አባትህንና እናትህን አክብር፤ ደግሞ። አባቱን ወይም እናቱን የሰደበ ፈጽሞ ይሙት ብሎአልና።
11 But you say, ‘If a man tells his father or his mother, “Whatever profit you might have received from me is Corban , that is to say, given to God”;’
11እናንተ ግን ትላላችሁ። ሰው አባቱን ወይም እናቱን። ከእኔ የምትጠቀምበት ነገር ሁሉ ቍርባን ማለት መባ ነው ቢል፥
12 then you no longer allow him to do anything for his father or his mother,
12ለአባቱና ለእናቱ ምንም እንኳ ሊያደርግ ወደ ፊት አትፈቅዱለትም፤
13 making void the word of God by your tradition, which you have handed down. You do many things like this.”
13ባስተላለፋችሁትም ወግ የእግዚአብሔርን ቃል ትሽራላችሁ፤ እንደዚሁም ይህን የሚመስል ብዙ ነገር ታደርጋላችሁ።
14He called all the multitude to himself, and said to them, “Hear me, all of you, and understand.
14ደግሞም ሕዝቡን ጠርቶ። ሁላችሁ እኔን ስሙ አስተውሉም።
15 There is nothing from outside of the man, that going into him can defile him; but the things which proceed out of the man are those that defile the man.
15ከሰው የሚወጡት ሰውን የሚያረክሱ ናቸው እንጂ ከሰው ውጭ የሚገባውስ ሊያረክሰው የሚችል ምንም የለም።
16 If anyone has ears to hear, let him hear!”
16የሚሰማ ጆሮ ያለው ቢኖር ይስማ አላቸው።
17When he had entered into a house away from the multitude, his disciples asked him about the parable.
17ከሕዝቡ ዘንድ ወደ ቤት ከገባ በኋላ ደቀ መዛሙርቱ ምሳሌውን ጠየቁት።
18He said to them, “Are you thus without understanding also? Don’t you perceive that whatever goes into the man from outside can’t defile him,
18እርሱም። እናንተ ደግሞ እንደዚህ የማታስተውሉ ናችሁን? ከውጭ ወደ ሰው የሚገባ ሊያረክሰው ምንም እንዳይችል አትመለከቱምን?
19 because it doesn’t go into his heart, but into his stomach, then into the latrine, thus purifying all foods ?”
19ወደ ሆድ ገብቶ ወደ እዳሪ ይወጣል እንጂ ወደ ልብ አይገባምና፤ መብልን ሁሉ እያጠራ አላቸው።
20He said, “That which proceeds out of the man, that defiles the man.
20እርሱም አለ። ከሰው የሚወጣው ሰውን የሚያረክስ ያ ነው።
21 For from within, out of the hearts of men, proceed evil thoughts, adulteries, sexual sins, murders, thefts,
21ከውስጥ ከሰው ልብ የሚወጣ ክፉ አሳብ፥
22 covetings, wickedness, deceit, lustful desires, an evil eye, blasphemy, pride, and foolishness.
22ዝሙት፥ መስረቅ፥ መግደል፥ ምንዝርነት፥ መጐምጀት፥ ክፋት፥ ተንኰል፥ መዳራት፥ ምቀኝነት፥ ስድብ፥ ትዕቢት፥ ስንፍና ናቸውና፤
23 All these evil things come from within, and defile the man.”
23ይህ ክፉው ሁሉ ከውስጥ ይወጣል ሰውን ያረክሰዋል።
24From there he arose, and went away into the borders of Tyre and Sidon. He entered into a house, and didn’t want anyone to know it, but he couldn’t escape notice.
24ከዚያም ተነሥቶ ወደ ጢሮስና ወደ ሲዶና አገር ሄደ። ወደ ቤትም ገብቶ ማንም እንዳያውቅበት ወደደ ሊሰወርም አልተቻለውም፤
25For a woman, whose little daughter had an unclean spirit, having heard of him, came and fell down at his feet.
25ወዲያው ግን ታናሺቱ ልጅዋ ርኵስ መንፈስ ያደረባት አንዲት ሴት ስለ እርሱ ሰምታ መጣችና በእግሩ ላይ ተደፋች
26Now the woman was a Greek, a Syrophoenician by race. She begged him that he would cast the demon out of her daughter.
26ሴቲቱም ግሪክ፥ ትውልድዋም ሲሮፊኒቃዊት ነበረች፤ ከልጅዋ ጋኔን ያወጣላት ዘንድ ለመነችው።
27But Jesus said to her, “Let the children be filled first, for it is not appropriate to take the children’s bread and throw it to the dogs.”
27ኢየሱስ ግን። ልጆቹ በፊት ይጠግቡ ዘንድ ተዪ የልጆቹን እንጀራ ይዞ ለቡችሎች መጣል አይገባምናአላት።
28But she answered him, “Yes, Lord. Yet even the dogs under the table eat the children’s crumbs.”
28እርስዋም መልሳ። አዎን፥ ጌታ ሆይ፥ ቡችሎች እንኳ ከማዕድ በታች ሆነው የልጆችን ፍርፋሪ ይበላሉ አለችው።
29He said to her, “For this saying, go your way. The demon has gone out of your daughter.”
29እርሱም። ስለዚህ ቃልሽ ሂጂ ጋኔኑ ከልጅሽ ወጥቶአል አላት።
30She went away to her house, and found the child having been laid on the bed, with the demon gone out.
30ወደ ቤትዋም ሄዳ ጋኔኑ ወጥቶ ልጅዋም በአልጋ ላይ ተኝታ አገኘች።
31Again he departed from the borders of Tyre and Sidon, and came to the sea of Galilee, through the midst of the region of Decapolis.
31ደግሞም ከጢሮስ አገር ወጥቶ በሲዶና አልፎ አሥር ከተማ በሚባል አገር መካከል ወደ ገሊላ ባሕር መጣ።
32They brought to him one who was deaf and had an impediment in his speech. They begged him to lay his hand on him.
32ደንቆሮና ኰልታፋም የሆነ ሰው ወደ እርሱ አመጡ፥
33He took him aside from the multitude, privately, and put his fingers into his ears, and he spat, and touched his tongue.
33እጁንም ይጭንበት ዘንድ ለመኑት። ከሕዝቡም ለይቶ ለብቻው ወሰደው፥ ጣቶቹንም በጆሮቹ አገባ እንትፍም ብሎ መላሱን ዳሰሰ፤
34Looking up to heaven, he sighed, and said to him, “Ephphatha!” that is, “Be opened!”
34ወደ ሰማይም አሻቅቦ አይቶ ቃተተና። ኤፍታህ አለው፥ እርሱም ተከፈት ማለት ነው።
35Immediately his ears were opened, and the impediment of his tongue was released, and he spoke clearly.
35ወዲያውም ጆሮቹ ተከፈቱ የመላሱም እስራት ተፈታ አጥርቶም ተናገረ።
36He commanded them that they should tell no one, but the more he commanded them, so much the more widely they proclaimed it.
36ለማንም አትንገሩ ብሎ አዘዛቸው እነርሱ ግን ባዘዛቸውም መጠን ይልቅ እጅግ አወሩት።
37They were astonished beyond measure, saying, “He has done all things well. He makes even the deaf hear, and the mute speak!”
37ያለ መጠንም ተገረሙና። ሁሉን ደኅና አድርጎአል፤ ደንቆሮችም እንዲሰሙ ዲዳዎችም እንዲናገሩ ያደርጋል አሉ።