World English Bible

Amharic: New Testament

Matthew

22

1Jesus answered and spoke again in parables to them, saying,
1ኢየሱስም መለሰ ደግሞም በምሳሌ ነገራቸው እንዲህም አለ።
2 “The Kingdom of Heaven is like a certain king, who made a marriage feast for his son,
2መንግሥተ ሰማያት ለልጁ ሰርግ ያደረገ ንጉሥን ትመስላለች።
3 and sent out his servants to call those who were invited to the marriage feast, but they would not come.
3የታደሙትንም ወደ ሰርጉ ይጠሩ ዘንድ ባሮቹን ላከ ሊመጡም አልወደዱም።
4 Again he sent out other servants, saying, ‘Tell those who are invited, “Behold, I have prepared my dinner. My cattle and my fatlings are killed, and all things are ready. Come to the marriage feast!”’
4ደግሞ ሌሎችን ባሮች ልኮ። የታደሙትን። እነሆ፥ ድግሴን አዘጋጀሁ፥ ኮርማዎቼና የሰቡት ከብቶቼ ታርደዋል፥ ሁሉም ተዘጋጅቶአል፤ ወደ ሰርጉ ኑ በሉአቸው አለ።
5 But they made light of it, and went their ways, one to his own farm, another to his merchandise,
5እነርሱ ግን ቸል ብለው አንዱ ወደ እርሻው፥ ሌላውም ወደ ንግዱ ሄደ፤
6 and the rest grabbed his servants, and treated them shamefully, and killed them.
6የቀሩትም ባሮቹን ይዘው አንገላቱአቸው ገደሉአቸውም።
7 When the king heard that, he was angry, and sent his armies, destroyed those murderers, and burned their city.
7ንጉሡም ተቈጣ፥ ጭፍሮቹንም ልኮ እነዚያን ገዳዮች አጠፋ፤ ከተማቸውንም አቃጠለ።
8 “Then he said to his servants, ‘The wedding is ready, but those who were invited weren’t worthy.
8በዚያን ጊዜ ባሮቹን። ሰርጉስ ተዘጋጅቶአል፥ ነገር ግን የታደሙት የማይገባቸው ሆኑ፤
9 Go therefore to the intersections of the highways, and as many as you may find, invite to the marriage feast.’
9እንግዲህ ወደ መንገድ መተላለፊያ ሄዳችሁ ያገኛችሁትን ሁሉ ወደ ሰርጉ ጥሩ አለ።
10 Those servants went out into the highways, and gathered together as many as they found, both bad and good. The wedding was filled with guests.
10እነዚያም ባሮች ወደ መንገድ ወጥተው ያገኙትን ሁሉ ክፉዎችንም በጎዎችንም ሰበሰቡ፤ የሰርጉንም ቤት ተቀማጮች ሞሉት።
11 But when the king came in to see the guests, he saw there a man who didn’t have on wedding clothing,
11ንጉሡም የተቀመጡትን ለማየት በገባ ጊዜ በዚያ የሰርግ ልብስ ያለበሰ አንድ ሰው አየና። ወዳጄ ሆይ፥
12 and he said to him, ‘Friend, how did you come in here not wearing wedding clothing?’ He was speechless.
12የሰርግ ልብስ ሳትለብስ እንዴት ወደዚህ ገባህ? አለው እርሱም ዝም አለ።
13 Then the king said to the servants, ‘Bind him hand and foot, take him away, and throw him into the outer darkness; there is where the weeping and grinding of teeth will be.’
13በዚያን ጊዜ ንጉሡ አገልጋዮቹን። እጁንና እግሩን አስራችሁ በውጭ ወዳለው ጨለማ አውጡት፤ በዚያ ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ይሆናል አለ።
14 For many are called, but few chosen.”
14የተጠሩ ብዙዎች፥ የተመረጡ ግን ጥቂቶች ናቸውና።
15Then the Pharisees went and took counsel how they might entrap him in his talk.
15ስለዚህ ፈሪሳውያን ሄዱና እንዴት አድርገው በነገር እንዲያጠምዱት ተማከሩ።
16They sent their disciples to him, along with the Herodians, saying, “Teacher, we know that you are honest, and teach the way of God in truth, no matter whom you teach, for you aren’t partial to anyone.
16ደቀ መዛሙርታቸውንም ከሄሮድስ ወገን ጋር ላኩበት፥ እነርሱም። መምህር ሆይ፥ እውነተኛ እንደ ሆንህ በእውነትም የእግዚአብሔርን መንገድ እንድታስተምር እናውቃለን፥ ለማንምም አታደላም፥ የሰውን ፊት አትመለከትምና፤
17Tell us therefore, what do you think? Is it lawful to pay taxes to Caesar, or not?”
17እንግዲህ ምን ይመስልሃል? ንገረን ለቄሣር ግብር መስጠት ተፈቅዶአልን ወይስ አልተፈቀደም? አሉት።
18But Jesus perceived their wickedness, and said, “Why do you test me, you hypocrites?
18ኢየሱስም ክፋታቸውን አውቆ። እናንተ ግብዞች፥ ስለ ምን ትፈትኑኛላችሁ?
19 Show me the tax money.” They brought to him a denarius.
19የግብሩን ብር አሳዩኝ አለ። እነርሱም ዲናር አመጡለት።
20He asked them, “Whose is this image and inscription?”
20እርሱም። ይህች መልክ ጽሕፈቲቱስ የማን ናት? አላቸው።
21They said to him, “Caesar’s.” Then he said to them, “Give therefore to Caesar the things that are Caesar’s, and to God the things that are God’s.”
21የቄሣር ነው አሉት። በዚያን ጊዜ። እንኪያስ የቄሣርን ለቄሣር የእግዚአብሔርንም ለእግዚአብሔር አስረክቡ አላቸው።
22When they heard it, they marveled, and left him, and went away.
22ይህንም ሰምተው ተደነቁ፥ ትተውትም ሄዱ።
23On that day Sadducees (those who say that there is no resurrection) came to him. They asked him,
23በዚያን ቀን። ትንሣኤ ሙታን የለም የሚሉ ሰዱቃውያን ወደ እርሱ ቀረቡ፥
24saying, “Teacher, Moses said, ‘If a man dies, having no children, his brother shall marry his wife, and raise up seed for his brother.’
24እንዲህም ብለው ጠየቁት። መምህር ሆይ፥ ሙሴ አንድ ሰው ልጅ ሳይወልድ ሲሞት ወንድሙ ሚስቱን አግብቶ ለወንድሙ ዘር ይተካ አለ።
25Now there were with us seven brothers. The first married and died, and having no seed left his wife to his brother.
25ሰባት ወንድማማች በእኛ ዘንድ ነበሩ፤ ፊተኛውም ሚስት አግብቶ ሞተ፥ ዘርም ስለሌለው ሚስቱን ለወንድሙ ተወለት፤
26In the same way, the second also, and the third, to the seventh.
26እንዲሁ ደግሞ ሁለተኛው ሦስተኛውም፥ እስከ ሰባተኛው ድረስ።
27After them all, the woman died.
27ከሁሉም በኋላ ሴቲቱ ሞተች።
28In the resurrection therefore, whose wife will she be of the seven? For they all had her.”
28ሁሉ አግብተዋታልና በትንሣኤ ቀንስ፥ ከሰባቱ ለማናቸው ሚስት ትሆናለች?
29But Jesus answered them, “You are mistaken, not knowing the Scriptures, nor the power of God.
29ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አላቸው። መጻሕፍትንና የእግዚአብሔርን ኃይል አታውቁምና ትስታላችሁ።
30 For in the resurrection they neither marry, nor are given in marriage, but are like God’s angels in heaven.
30በትንሣኤስ እንደ እግዚአብሔር መላእክት በሰማይ ይሆናሉ እንጂ አያገቡም አይጋቡምም።
31 But concerning the resurrection of the dead, haven’t you read that which was spoken to you by God, saying,
31ስለ ትንሣኤ ሙታን ግን። እኔ የአብርሃም አምላክ፥ የይስሐቅም አምላክ የያዕቆብም አምላክ ነኝ የሚል ከእግዚአብሔር ዘንድ ወደ እናንተ የተባለውን አላነበባችሁምን? የሕያዋን አምላክ ነው እንጂ የሙታን አይደለም።
32 ‘I am the God of Abraham, and the God of Isaac, and the God of Jacob?’ God is not the God of the dead, but of the living.”
33ሕዝቡም ይህን ሰምተው በትምህርቱ ተገረሙ።
33When the multitudes heard it, they were astonished at his teaching.
34ፈሪሳውያንም ሰዱቃውያንን ዝም እንዳሰኛቸው በሰሙ ጊዜ አብረው ተሰበሰቡ።
34But the Pharisees, when they heard that he had silenced the Sadducees, gathered themselves together.
35ከእነርሱም አንድ ሕግ አዋቂ ሊፈትነው።
35One of them, a lawyer, asked him a question, testing him.
36መምህር ሆይ፥ ከሕግ ማናቸይቱ ትእዛዝ ታላቅ ናት? ብሎ ጠየቀው።
36“Teacher, which is the greatest commandment in the law?”
37ኢየሱስም እንዲህ አለው። ጌታ አምላክህን በፍጹም ልብህ በፍጹም ነፍስህም በፍጹም አሳብህም ውደድ።
37Jesus said to him, “‘You shall love the Lord your God with all your heart, with all your soul, and with all your mind.’
38ታላቂቱና ፊተኛይቱ ትእዛዝ ይህች ናት።
38 This is the first and great commandment.
39ሁለተኛይቱም ይህችን ትመስላለች፥ እርስዋም። ባልንጀራህን እንደ ነፍስህ ውደድ የምትለው ናት።
39 A second likewise is this, ‘You shall love your neighbor as yourself.’
40በእነዚህ በሁለቱ ትእዛዛት ሕጉም ሁሉ ነቢያትም ተሰቅለዋል።
40 The whole law and the prophets depend on these two commandments.”
41ፈሪሳውያንም ተሰብስበው ሳሉ፥ ኢየሱስ። ስለ ክርስቶስ ምን ይመስላችኋል? የማንስ ልጅ ነው? ብሎ ጠየቃቸው። የዳዊት ልጅ ነው አሉት።
41Now while the Pharisees were gathered together, Jesus asked them a question,
43እርሱም። እንኪያስ ዳዊት። ጌታ ጌታዬን። ጠላቶችህን የእግርህ መረገጫ እስካደርግልህ ድረስ በቀኜ ተቀመጥ አለው ሲል እንዴት በመንፈስ ጌታ ብሎ ይጠራዋል?
42saying, “What do you think of the Christ? Whose son is he?” They said to him, “Of David.”
45ዳዊትስ ጌታ ብሎ ከጠራው፥ እንዴት ልጁ ይሆናል? አላቸው።
43He said to them, “How then does David in the Spirit call him Lord, saying,
46አንድም ቃል ስንኳ ይመልስለት ዘንድ የተቻለው የለም፥ ከዚያ ቀንም ጀምሮ ወደ ፊት ማንም ሊጠይቀው አልደፈረም።
44 ‘The Lord said to my Lord, sit on my right hand, until I make your enemies a footstool for your feet?’
45 “If then David calls him Lord, how is he his son?”
46No one was able to answer him a word, neither did any man dare ask him any more questions from that day forth.