World English Bible

Amharic: New Testament

Matthew

27

1Now when morning had come, all the chief priests and the elders of the people took counsel against Jesus to put him to death:
1ሲነጋም የካህናት አለቆችና የሕዝቡ ሽማግሎች ሁሉ ሊገድሉት በኢየሱስ ላይ ተማከሩ፤
2and they bound him, and led him away, and delivered him up to Pontius Pilate, the governor.
2አስረውም ወሰዱት፥ ለገዢው ለጴንጤናዊው ጲላጦስም አሳልፈው ሰጡት።
3Then Judas, who betrayed him, when he saw that Jesus was condemned, felt remorse, and brought back the thirty pieces of silver to the chief priests and elders,
3በዚያን ጊዜ አሳልፎ የሰጠው ይሁዳ እንደ ተፈረደበት አይቶ ተጸጸተ፥ ሠላሳውንም ብር ለካህናት አለቆችና ለሽማግሎች መልሶ።
4saying, “I have sinned in that I betrayed innocent blood.” But they said, “What is that to us? You see to it.”
4ንጹሕ ደም አሳልፌ በመስጠቴ በድያለሁ አለ። እነርሱ ግን። እኛስ ምን አግዶን? አንተው ተጠንቀቅ አሉ።
5He threw down the pieces of silver in the sanctuary, and departed. He went away and hanged himself.
5ብሩንም በቤተ መቅደስ ጥሎ ሄደና ታንቆ ሞተ።
6The chief priests took the pieces of silver, and said, “It’s not lawful to put them into the treasury, since it is the price of blood.”
6የካህናት አለቆችም ብሩን አንሥተው። የደም ዋጋ ነውና ወደ መባ ልንጨምረው አልተፈቀደም አሉ።
7They took counsel, and bought the potter’s field with them, to bury strangers in.
7ተማክረውም የሸክላ ሠሪውን መሬት ለእንግዶች መቃብር ገዙበት።
8Therefore that field was called “The Field of Blood” to this day.
8ስለዚህ ያ መሬት እስከ ዛሬ ድረስ የደም መሬት ተባለ።
9Then that which was spoken through Jeremiah the prophet was fulfilled, saying, “They took the thirty pieces of silver, the price of him upon whom a price had been set, whom some of the children of Israel priced,
9በዚያን ጊዜ በነቢዩ በኤርምያስ የተባለው። ከእስራኤል ልጆችም አንዳንዶቹ የገመቱትን፥ የተገመተውን ዋጋ ሠላሳ ብር ያዙ፥
10and they gave them for the potter’s field, as the Lord commanded me.”
10ጌታም እንዳዘዘኝ ስለ ሸክላ ሠሪ መሬት ሰጡት። የሚል ተፈጸመ።
11Now Jesus stood before the governor: and the governor asked him, saying, “Are you the King of the Jews?” Jesus said to him, “So you say.”
11ኢየሱስም በገዢው ፊት ቆመ፤ ገዢውም። የአይሁድ ንጉሥ አንተ ነህን? ብሎ ጠየቀው፤ ኢየሱስም። አንተ አልህ አለው።
12When he was accused by the chief priests and elders, he answered nothing.
12የካህናት አለቆችም ሽማግሎችም ሲከሱት ምንም አልመለሰም።
13Then Pilate said to him, “Don’t you hear how many things they testify against you?”
13በዚያን ጊዜ ጲላጦስ። ስንት ያህል እንዲመሰክሩብህ አትሰማምን? አለው።
14He gave him no answer, not even one word, so that the governor marveled greatly.
14ገዢውም እጅግ እስኪደነቅ ድረስ አንዲት ቃል ስንኳ አልመለሰለትም።
15Now at the feast the governor was accustomed to release to the multitude one prisoner, whom they desired.
15በዚያም በዓል ሕዝቡ የወደዱትን አንድ እስረኛ ሊፈታላቸው ለገዢው ልማድ ነበረው።
16They had then a notable prisoner, called Barabbas.
16በዚያን ጊዜም በርባን የሚባል በጣም የታወቀ እስረኛ ነበራቸው።
17When therefore they were gathered together, Pilate said to them, “Whom do you want me to release to you? Barabbas, or Jesus, who is called Christ?”
17እንግዲህ እነርሱ ተሰብስበው ሳሉ ጲላጦስ። በርባንን ወይስ ክርስቶስ የተባለውን ኢየሱስን ማንኛውን ልፈታላችሁ ትወዳላችሁ? አላቸው፤
18For he knew that because of envy they had delivered him up.
18በቅንዓት አሳልፈው እንደ ሰጡት ያውቅ ነበርና።
19While he was sitting on the judgment seat, his wife sent to him, saying, “Have nothing to do with that righteous man, for I have suffered many things this day in a dream because of him.”
19እርሱም በፍርድ ወንበር ተቀምጦ ሳለ ሚስቱ። ስለ እርሱ ዛሬ በሕልም እጅግ መከራ ተቀብያለሁና በዚያ ጻድቅ ሰው ምንም አታድርግ ብላ ላከችበት።
20Now the chief priests and the elders persuaded the multitudes to ask for Barabbas, and destroy Jesus.
20የካህናት አለቆችና ሽማግሎች ግን በርባንን እንዲለምኑ ኢየሱስን ግን እንዲያጠፉ ሕዝቡን አባበሉ።
21But the governor answered them, “Which of the two do you want me to release to you?” They said, “Barabbas!”
21ገዢውም መልሶ። ከሁለቱ ማንኛውን ልፈታላችሁ ትወዳላችሁ? አላቸው፤ እነርሱም። በርባንን አሉ።
22Pilate said to them, “What then shall I do to Jesus, who is called Christ?” They all said to him, “Let him be crucified!”
22ጲላጦስ። ክርስቶስ የተባለውን ኢየሱስን እንግዲህ ምን ላድርገው? አላቸው፤ ሁሉም። ይሰቀል አሉ።
23But the governor said, “Why? What evil has he done?” But they cried out exceedingly, saying, “Let him be crucified!”
23ገዢውም። ምን ነው? ያደረገው ክፋት ምንድር ነው? አለ፤ እነርሱ ግን። ይሰቀል እያሉ ጩኸት አበዙ።
24So when Pilate saw that nothing was being gained, but rather that a disturbance was starting, he took water, and washed his hands before the multitude, saying, “I am innocent of the blood of this righteous person. You see to it.”
24ጲላጦስም ሁከት እንዲጀመር እንጂ አንዳች እንዳይረባ ባየ ጊዜ፥ ውኃ አንሥቶ። እኔ ከዚህ ጻድቅ ሰው ደም ንጹሕ ነኝ፤ እናንተ ተጠንቀቁ ሲል በሕዝቡ ፊት እጁን ታጠበ።
25All the people answered, “May his blood be on us, and on our children!”
25ሕዝቡም ሁሉ መልሰው። ደሙ በእኛና በልጆቻችን ላይ ይሁን አሉ።
26Then he released to them Barabbas, but Jesus he flogged and delivered to be crucified.
26በዚያን ጊዜ በርባንን ፈታላቸው፥ ኢየሱስን ግን ገርፎ ሊሰቀል አሳልፎ ሰጠ።
27Then the governor’s soldiers took Jesus into the Praetorium, and gathered the whole garrison together against him.
27በዚያን ጊዜ የገዢው ወታደሮች ኢየሱስን ወደ ገዢው ግቢ ውስጥ ወሰዱት ጭፍራውንም ሁሉ ወደ እርሱ አከማቹ።
28They stripped him, and put a scarlet robe on him.
28ልብሱንም ገፈው ቀይ ልብስ አለበሱት፥
29They braided a crown of thorns and put it on his head, and a reed in his right hand; and they kneeled down before him, and mocked him, saying, “Hail, King of the Jews!”
29ከእሾህም አክሊል ጎንጉነው በራሱ ላይ፥ በቀኝ እጁም መቃ አኖሩ፥ በፊቱም ተንበርክከው። የአይሁድ ንጉሥ ሆይ፥ ሰላም ለአንተ ይሁን እያሉ ዘበቱበት፤
30They spat on him, and took the reed and struck him on the head.
30ተፉበትም መቃውንም ይዘው ራሱን መቱት።
31When they had mocked him, they took the robe off of him, and put his clothes on him, and led him away to crucify him.
31ከዘበቱበትም በኋላ ቀዩን ልብስ ገፈፉት፥ ልብሱንም አለበሱት ሊሰቅሉትም ወሰዱት።
32As they came out, they found a man of Cyrene, Simon by name, and they compelled him to go with them, that he might carry his cross.
32ሲወጡም ስምዖን የተባለው የቀሬናን ሰው አገኙ፤ እርሱንም መስቀሉን ይሸከም ዘንድ አስገደዱት።
33They came to a place called “Golgotha,” that is to say, “The place of a skull.”
33ትርጓሜው የራስ ቅል ስፍራ ወደሚሆን ጎልጎታ ወደሚባለው ስፍራ በደረሱ ጊዜም፥
34They gave him sour wine to drink mixed with gall. When he had tasted it, he would not drink.
34በሐሞት የተደባለቀ የወይን ጠጅ ሊጠጣ አቀረቡለት፤ ቀምሶም ሊጠጣው አልወደደም።
35When they had crucified him, they divided his clothing among them, casting lots,
35ከሰቀሉትም በኋላ ልብሱን ዕጣ ጥለው ተካፈሉ፥
36and they sat and watched him there.
36በዚያም ተቀምጠው ይጠብቁት ነበር።
37They set up over his head the accusation against him written, “THIS IS JESUS, THE KING OF THE JEWS.”
37ይህ ኢየሱስ የአይሁድ ንጉሥ ነው የሚል የክሱን ጽሕፈት ከራሱ በላይ አኖሩ።
38Then there were two robbers crucified with him, one on his right hand and one on the left.
38በዚያን ጊዜ ሁለት ወንበዶች አንዱ በቀኝ አንዱም በግራ ከእርሱ ጋር ተሰቀሉ።
39Those who passed by blasphemed him, wagging their heads,
39የሚያልፉትም ራሳቸውን እየነቀነቁ ይሰድቡት ነበርና።
40and saying, “You who destroy the temple, and build it in three days, save yourself! If you are the Son of God, come down from the cross!”
40ቤተ መቅደስን የምታፈርስ በሦስት ቀንም የምትሠራው፥ ራስህን አድን፤ የእግዚአብሔር ልጅስ ከሆንህ ከመስቀል ውረድ አሉት።
41Likewise the chief priests also mocking, with the scribes, the Pharisees, and the elders, said,
41እንዲሁም ደግሞ የካህናት አለቆች ከጻፎችና ከሽማግሎች ጋር እየዘበቱበት እንዲህ አሉ።
42“He saved others, but he can’t save himself. If he is the King of Israel, let him come down from the cross now, and we will believe in him.
42ሌሎችን አዳነ፥ ራሱን ሊያድን አይችልም፤ የእስራኤል ንጉሥ ከሆነ፥ አሁን ከመስቀል ይውረድ እኛም እናምንበታለን።
43He trusts in God. Let God deliver him now, if he wants him; for he said, ‘I am the Son of God.’”
43በእግዚአብሔር ታምኖአል፤ የእግዚአብሔር ልጅ ነኝ ብሎአልና ከወደደውስ አሁን ያድነው።
44The robbers also who were crucified with him cast on him the same reproach.
44ከእርሱ ጋር የተሰቀሉት ወንበዶች ደግሞ ያንኑ እያሉ ይነቅፉት ነበር።
45Now from the sixth hour there was darkness over all the land until the ninth hour.
45ከስድስት ሰዓትም ጀምሮ እስከ ዘጠኝ ሰዓት ድረስ በምድር ሁሉ ላይ ጨለማ ሆነ።
46About the ninth hour Jesus cried with a loud voice, saying, “Eli, Eli, lima sabachthani?” That is, “My God, my God, why have you forsaken me?”
46በዘጠኝ ሰዓትም ኢየሱስ። ኤሎሄ ኤሎሄ ላማ ሰበቅታኒ? ብሎ በታላቅ ድምፅ ጮኸ። ይህም። አምላኬ አምላኬ፥ ስለ ምን ተውኸኝ? ማለት ነው።
47Some of them who stood there, when they heard it, said, “This man is calling Elijah.”
47በዚያም ከቆሙት ሰዎች ሰምተው። ይህስ ኤልያስን ይጠራል አሉ።
48Immediately one of them ran, and took a sponge, and filled it with vinegar, and put it on a reed, and gave him a drink.
48ወዲያውም ከእነርሱ አንዱ ሮጠ፤ ሰፍነግም ይዞ ሆምጣጤ ሞላበት፥ በመቃም አድርጎ አጠጣው።
49The rest said, “Let him be. Let’s see whether Elijah comes to save him.”
49ሌሎቹ ግን። ተው፥ ኤልያስ መጥቶ ያድነው እንደ ሆነ እንይ አሉ።
50Jesus cried again with a loud voice, and yielded up his spirit.
50ኢየሱስም ሁለተኛ በታላቅ ድምፅ ጮኾ ነፍሱን ተወ።
51Behold, the veil of the temple was torn in two from the top to the bottom. The earth quaked and the rocks were split.
51እነሆም፥ የቤተ መቅደስ መጋረጃ ከላይ እስከ ታች ከሁለት ተቀደደ፥ ምድርም ተናወጠች፥ ዓለቶችም ተሰነጠቁ፤
52The tombs were opened, and many bodies of the saints who had fallen asleep were raised;
52መቃብሮችም ተከፈቱ፥ ተኝተው ከነበሩትም ከቅዱሳን ብዙ ሥጋዎች ተነሡ፤
53and coming out of the tombs after his resurrection, they entered into the holy city and appeared to many.
53ከትንሣኤውም በኋላ ከመቃብሮች ወጥተው ወደ ቅድስት ከተማ ገቡና ለብዙዎች ታዩ።
54Now the centurion, and those who were with him watching Jesus, when they saw the earthquake, and the things that were done, feared exceedingly, saying, “Truly this was the Son of God.”
54የመቶ አለቃም ከእርሱም ጋር ኢየሱስን የሚጠብቁ መናወጡንና የሆነውን ነገር አይተው። ይህ በእውነት የእግዚአብሔር ልጅ ነበረ ብለው እጅግ ፈሩ።
55Many women were there watching from afar, who had followed Jesus from Galilee, serving him.
55ኢየሱስን እያገለገሉ ከገሊላ የተከተሉት ብዙ ሴቶች በሩቅ ሆነው ሲመለከቱ በዚያ ነበሩ፤
56Among them were Mary Magdalene, Mary the mother of James and Joses, and the mother of the sons of Zebedee.
56ከእነርሱም መግደላዊት ማርያምና የያዕቆብና የዮሳ እናት ማርያም የዘብዴዎስም የልጆቹ እናት ነበሩ።
57When evening had come, a rich man from Arimathaea, named Joseph, who himself was also Jesus’ disciple came.
57በመሸም ጊዜ ዮሴፍ የተባለው ባለ ጠጋ ሰው ከአርማትያስ መጣ፥ እርሱም ደግሞ የኢየሱስ ደቀ መዝሙር ነበረ፤
58This man went to Pilate, and asked for Jesus’ body. Then Pilate commanded the body to be given up.
58ይኸውም ወደ ጲላጦስ ቀርቦ የኢየሱስን ሥጋ ለመነው።
59Joseph took the body, and wrapped it in a clean linen cloth,
59ጲላጦስም እንዲሰጡት አዘዘ። ዮሴፍም ሥጋውን ይዞ በንጹሕ በፍታ ከፈነው፥
60and laid it in his own new tomb, which he had cut out in the rock, and he rolled a great stone to the door of the tomb, and departed.
60ከዓለት በወቀረው በአዲሱ መቃብርም አኖረው፥ በመቃብሩም ደጃፍ ታላቅ ድንጋይ አንከባሎ ሄደ።
61Mary Magdalene was there, and the other Mary, sitting opposite the tomb.
61መግደላዊት ማርያምም ሁለተኛይቱም ማርያም በመቃብሩ አንጻር ተቀምጠው በዚያ ነበሩ።
62Now on the next day, which was the day after the Preparation Day, the chief priests and the Pharisees were gathered together to Pilate,
62በማግሥቱም ከመዘጋጀት በኋላ በሚሆነው ቀን፥ የካህናት አለቆችና ፈሪሳውያን ወደ ጲላጦስ ተሰበሰቡና።
63saying, “Sir, we remember what that deceiver said while he was still alive: ‘After three days I will rise again.’
63ጌታ ሆይ፥ ያ አሳች በሕይወቱ ገና ሳለ። ከሦስት ቀን በኋላ እነሣለሁ እንዳለ ትዝ አለን።
64Command therefore that the tomb be made secure until the third day, lest perhaps his disciples come at night and steal him away, and tell the people, ‘He is risen from the dead;’ and the last deception will be worse than the first.”
64እንግዲህ ደቀ መዛሙርቱ መጥተው በሌሊት እንዳይሰርቁት ለሕዝቡም። ከሙታን ተነሣ እንዳይሉ፥ የኋለኛይቱ ስሕተት ከፊተኛይቱ ይልቅ የከፋች ትሆናለችና መቃብሩ እስከ ሦስተኛ ቀን ድረስ እንዲጠበቅ እዘዝ አሉት።
65Pilate said to them, “You have a guard. Go, make it as secure as you can.”
65ጲላጦስም። ጠባቆች አሉአችሁ፤ ሄዳችሁ እንዳወቃችሁ አስጠብቁ አላቸው።
66So they went with the guard and made the tomb secure, sealing the stone.
66እነርሱም ሄደው ከጠባቆች ጋር ድንጋዩን አትመው መቃብሩን አስጠበቁ።