World English Bible

Amharic: New Testament

Philemon

1

1Paul, a prisoner of Christ Jesus, and Timothy our brother, to Philemon, our beloved fellow worker,
1የክርስቶስ ኢየሱስ እስር ጳውሎስ ወንድሙም ጢሞቴዎስ፥ ለተወደደውና አብሮን ለሚሠራ ለፊልሞና፥
2to the beloved Apphia, to Archippus, our fellow soldier, and to the assembly in your house:
2ለእኅታችንም ለአፍብያ፥ ከእኛም ጋር አብሮ ወታደር ለሆነ ለአርክጳ፥ በቤትህም ላለች ቤተ ክርስቲያን፤
3Grace to you and peace from God our Father and the Lord Jesus Christ.
3ከእግዚአብሔር ከአባታችን ከጌታም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን።
4I thank my God always, making mention of you in my prayers,
4በጌታ በኢየሱስ ዘንድ በቅዱሳንም ሁሉ ዘንድ ስላለህ ስለ ፍቅርህና ስለ እምነትህ ሰምቼ፥ በጸሎቴ እያሳሰብሁ ሁልጊዜ አምላኬን አመሰግናለሁ፤
5hearing of your love, and of the faith which you have toward the Lord Jesus, and toward all the saints;
6የእምነትህም ኅብረት፥ በእኛ ዘንድ ያለውን በጎ ነገር ሁሉ በማወቅ፥ ለክርስቶስ ኢየሱስ ፍሬ እንዲያፈራ እለምናለሁ፤
6that the fellowship of your faith may become effective, in the knowledge of every good thing which is in us in Christ Jesus.
7የቅዱሳን ልብ በአንተ ስራ ስለ ዐረፈ፥ ወንድሜ ሆይ፥ በፍቅርህ ብዙ ደስታንና መጽናናትን አግኝቼአለሁና።
7For we have much joy and comfort in your love, because the hearts of the saints have been refreshed through you, brother.
8ስለዚህ የሚገባውን አዝህ ዘንድ በክርስቶስ ምንም እንኳ ብዙ ድፍረት ቢኖረኝ፥
8Therefore though I have all boldness in Christ to command you that which is appropriate,
9ይልቁንም እንደዚህ የሆንሁ እኔ ጳውሎስ ሽማግሌው፥ አሁንም ደግሞ የኢየሱስ ክርስቶስ እስር የሆንሁ፥ ስለ ፍቅር እለምናለሁ።
9yet for love’s sake I rather beg, being such a one as Paul, the aged, but also a prisoner of Jesus Christ.
10አስቀድሞ ስላልጠቀመህ፥ አሁን ግን ለእኔም ለአንተም ስለሚጠቅም በእስራቴ ስለ ወለድሁት ስለ ልጄ ስለ አናሲሞስ እለምንሃለሁ።
10I beg you for my child, whom I have become the father of in my chains, Onesimus,
12እርሱን እልከዋለሁ፤
11who once was useless to you, but now is useful to you and to me.
13አንተም ልቤ እንደሚሆን ተቀበለው። እኔስ በወንጌል እስራት ስለ አንተ እንዲያገለግለኝ ለራሴ ላስቀረው እፈቅድ ነበር፥
12I am sending him back. Therefore receive him, that is, my own heart,
14ነገር ግን በጎነትህ በፈቃድህ እንጂ በግድ እንዳይሆን፥ ሳልማከርህ ምንም እንኳ ላደርግ አልወደድሁም።
13whom I desired to keep with me, that on your behalf he might serve me in my chains for the Good News.
15ተቀብለህ ለዘላለም እንድትይዘው ስለዚህ ምናልባት ለጊዜው ተለይቶሃልና፤
14But I was willing to do nothing without your consent, that your goodness would not be as of necessity, but of free will.
16ከእንግዲህ ወዲህ እንደ ባሪያ አይሆንም፥ ነገር ግን ለእኔ በተለየ የተወደደ ወንድም ከሆነ፥ ለአንተማ ይልቅ በስጋውም በጌታም ዘንድ ከባሪያ የሚሻል የተወደደ ወንድም እንዴት አይሆንም።
15For perhaps he was therefore separated from you for a while, that you would have him forever,
17እንግዲህ እንደ ባልንጀራ ብትቈጥረኝ፥ እንደ እኔ አድርገህ ተቀበለው።
16no longer as a slave, but more than a slave, a beloved brother, especially to me, but how much rather to you, both in the flesh and in the Lord.
18በአንዳች ነገር የበደለህ ቢኖር ግን ወይም ብድር ያለበት እንደሆነ፥ ይህን በእኔ ላይ ቍጠር፤
17If then you count me a partner, receive him as you would receive me.
19እኔ ጳውሎስ። እኔ እመልሰዋለሁ ብዬ በእጄ እጽፋለሁ፤ ከዚህም በላይ ለእኔ የራስህ ደግሞ ብድር እንዳለብህ አልልህም።
18But if he has wronged you at all, or owes you anything, put that to my account.
20አዎን፥ ወንድሜ ሆይ፥ በጌታ እኔ እንድጠቀምብህ ይሁን፤ በክርስቶስ ልቤን አሳርፍልኝ።
19I, Paul, write this with my own hand: I will repay it (not to mention to you that you owe to me even your own self besides).
21ከምልህ ይልቅ አብልጠህ እንድታደርግ አውቄ እንድትታዘዝም ታምኜ እጽፍልሃለሁ።
20Yes, brother, let me have joy from you in the Lord. Refresh my heart in the Lord.
22ደግሞ ከዚህም ጋር የማስተናገጃ ቤት አዘጋጅልኝ፤ በጸሎታችሁ ለእናንተ እንድሰጥ ተስፋ አደርጋለሁና።
21Having confidence in your obedience, I write to you, knowing that you will do even beyond what I say.
23በክርስቶስ ኢየሱስ ከእኔ ጋር የታሰረ ኤጳፍራ
22Also, prepare a guest room for me, for I hope that through your prayers I will be restored to you.
24አብረውኝም የሚሰሩ ማርቆስና አርስጥሮኮስ ዴማስም ሉቃስም ሰላምታ ያቀርቡልሃል።
23Epaphras, my fellow prisoner in Christ Jesus, greets you,
25የጌታችን የኢሱስ ክርስቶስ ጸጋ ከመንፈሳችሁ ጋር ይሁን፤ አሜን።
24as do Mark, Aristarchus, Demas, and Luke, my fellow workers.
25The grace of our Lord Jesus Christ be with your spirit. Amen.