1Then what advantage does the Jew have? Or what is the profit of circumcision?
1እንግዲህ የአይሁዳዊ ብልጫው ምንድር ነው? ወይስ የመገረዝ ጥቅሙ ምንድር ነው? በሁሉ ነገር ብዙ ነው።
2Much in every way! Because first of all, they were entrusted with the oracles of God.
2አስቀድሞ የእግዚአብሔር ቃላት አደራ ተሰጡአቸው። ታዲያ ምንድር ነው?
3For what if some were without faith? Will their lack of faith nullify the faithfulness of God?
3የማያምኑ ቢኖሩ አለማመናቸው የእግዚአብሔርን ታማኝነት ያስቀራልን?
4May it never be! Yes, let God be found true, but every man a liar. As it is written, “That you might be justified in your words, and might prevail when you come into judgment.” Psalm 51:4
4እንዲህ አይሁን፤ በቃልህ ትጸድቅ ዘንድ ወደ ፍርድ በገባህም ጊዜ ትረታ ዘንድ ተብሎ እንደ ተጻፈ፥ ሰው ሁሉ ውሸተኛ ከሆነ እግዚአብሔር እውነተኛ ይሁን።
5But if our unrighteousness commends the righteousness of God, what will we say? Is God unrighteous who inflicts wrath? I speak like men do.
5ነገር ግን ዓመፃችን የእግዚአብሔርን ጽድቅ የሚያስረዳ ከሆነ ምን እንላለን? ቍጣን የሚያመጣ እግዚአብሔር ዓመፀኛ ነውን? እንደ ሰው ልማድ እላለሁ።
6May it never be! For then how will God judge the world?
6እንዲህ አይሁን፤ እንዲህ ቢሆን እግዚአብሔር በዓለም እንዴት ይፈርዳል?
7For if the truth of God through my lie abounded to his glory, why am I also still judged as a sinner?
7በእኔ ውሸት ግን የእግዚአብሔር እውነት ለክብሩ ከላቀ ስለምን በእኔ ደግሞ እንደ ኃጢአተኛ ገና ይፈርድብኛል?
8Why not (as we are slanderously reported, and as some affirm that we say), “Let us do evil, that good may come?” Those who say so are justly condemned.
8ስለ ምንስ መልካም እንዲመጣ ክፉ አናደርግም? እንዲሁ ይሰድቡናልና አንዳንዱም እንዲሁ እንድንል ይናገራሉና። የእነርሱም ፍርድ ቅን ነው።
9What then? Are we better than they? No, in no way. For we previously warned both Jews and Greeks, that they are all under sin.
9እንግዲህ ምን ይሁን? ከእነርሱ እንበልጣለንን? ከቶ አይደለም፤ አይሁድም የግሪክ ሰዎችም ሁሉ ከኃጢአት በታች እንደ ሆኑ አስቀድመን ከሰናቸዋልና፤
10As it is written, “There is no one righteous; no, not one.
10እንዲህ ተብሎ እንደ ተጻፈ።
11There is no one who understands. There is no one who seeks after God.
11ጻድቅ የለም አንድ ስንኳ፤ አስተዋይም የለም፤ እግዚአብሔርንም የሚፈልግ የለም፤ ሁሉ ተሳስተዋል፥
12They have all turned aside. They have together become unprofitable. There is no one who does good, no, not, so much as one.” Psalms 14:1-3; 53:1-3; Ecclesiastes 7:20
12በአንድነትም የማይጠቅሙ ሆነዋል፤ ቸርነት የሚያደርግ የለም፥ አንድ ስንኳ የለም።
13“Their throat is an open tomb. With their tongues they have used deceit.” Psalm 5:9 “The poison of vipers is under their lips”; Psalm 140:3
13ጕሮሮአቸው እንደ ተከፈተ መቃብር ነው፥ በመላሳቸውም ሸንግለዋል፤ የእባብ መርዝ ከከንፈሮቻቸው በታች አለ፤
14“whose mouth is full of cursing and bitterness.” Psalm 10:7
14አፋቸውም እርግማንና መራርነት ሞልቶበታል፤
15“Their feet are swift to shed blood.
15እግሮቻቸው ደምን ለማፍሰስ ፈጣኖች ናቸው፤
16Destruction and misery are in their ways.
16ጥፋትና ጉስቁልና በመንገዳቸው ይገኛል፥
17The way of peace, they haven’t known.” Isaiah 59:7-8
17የሰላምንም መንገድ አያውቁም። በዓይኖቻቸው ፊት እግዚአብሔርን መፍራት የለም።
18“There is no fear of God before their eyes.” Psalm 36:1
19አፍም ሁሉ ይዘጋ ዘንድ ዓለምም ሁሉ ከእግዚአብሔር ፍርድ በታች ይሆን ዘንድ ሕግ የሚናገረው ሁሉ ከሕግ በታች ላሉት እንዲናገር እናውቃለን፤
19Now we know that whatever things the law says, it speaks to those who are under the law, that every mouth may be closed, and all the world may be brought under the judgment of God.
20ይህም የሕግን ሥራ በመሥራት ሥጋ የለበሰ ሁሉ በእርሱ ፊት ስለማይጸድቅ ነው፤ ኃጢአት በሕግ ይታወቃልና።
20Because by the works of the law, no flesh will be justified in his sight. For through the law comes the knowledge of sin.
21አሁን ግን በሕግና በነቢያት የተመሰከረለት የእግዚአብሔር ጽድቅ ያለ ሕግ ተገልጦአል፥
21But now apart from the law, a righteousness of God has been revealed, being testified by the law and the prophets;
22እርሱም፥ ለሚያምኑ ሁሉ የሆነ፥ በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን የሚገኘው የእግዚአብሔር ጽድቅ ነው፤ ልዩነት የለምና፤
22even the righteousness of God through faith in Jesus Christ to all and on all those who believe. For there is no distinction,
23ሁሉ ኃጢአትን ሠርተዋልና የእግዚአብሔርም ክብር ጎድሎአቸዋል፤
23for all have sinned, and fall short of the glory of God;
24በኢየሱስ ክርስቶስም በሆነው ቤዛነት በኩል እንዲያው በጸጋው ይጸድቃሉ።
24being justified freely by his grace through the redemption that is in Christ Jesus;
25እርሱንም እግዚአብሔር በእምነት የሚገኝ በደሙም የሆነ ማስተስሪያ አድርጎ አቆመው፤ ይህም በፊት የተደረገውን ኃጢአት በእግዚአብሔር ችሎታ ስለ መተው ጽድቁን ያሳይ ዘንድ ነው፥
25whom God set forth to be an atoning sacrifice or, a propitiation , through faith in his blood, for a demonstration of his righteousness through the passing over of prior sins, in God’s forbearance;
26ራሱም ጻድቅ እንዲሆን በኢየሱስም የሚያምነውን እንዲያጸድቅ አሁን በዚህ ዘመን ጽድቁን ያሳይ ዘንድ ነው።
26to demonstrate his righteousness at this present time; that he might himself be just, and the justifier of him who has faith in Jesus.
27ትምክህት እንግዲህ ወዴት ነው? እርሱ ቀርቶአል። በየትኛው ሕግ ነው? በሥራ ሕግ ነውን? አይደለም፥ በእምነት ሕግ ነው እንጂ።
27Where then is the boasting? It is excluded. By what kind of law? Of works? No, but by a law of faith.
28ሰው ያለ ሕግ ሥራ በእምነት እንዲጸድቅ እንቆጥራለንና።
28We maintain therefore that a man is justified by faith apart from the works of the law.
29ወይስ እግዚአብሔር የአይሁድ ብቻ አምላክ ነውን? የአሕዛብስ ደግሞ አምላክ አይደለምን? አዎን፥ የተገረዘን ስለ እምነት ያልተገረዘንም በእምነት የሚያጸድቅ አምላክ አንድ ስለ ሆነ የአሕዛብ ደግሞ አምላክ ነው።
29Or is God the God of Jews only? Isn’t he the God of Gentiles also? Yes, of Gentiles also,
31እንግዲህ ሕግን በእምነት እንሽራለንን? አይደለም፤ ሕግን እናጸናለን እንጂ።
30since indeed there is one God who will justify the circumcised by faith, and the uncircumcised through faith.
31Do we then nullify the law through faith? May it never be! No, we establish the law.