Young`s Literal Translation

Amharic: New Testament

1 Corinthians

12

1And concerning the spiritual things, brethren, I do not wish you to be ignorant;
1ስለ መንፈሳዊ ነገርም፥ ወንድሞች ሆይ፥ ታውቁ ዘንድ እወዳለሁ።
2ye have known that ye were nations, unto the dumb idols — as ye were led — being carried away;
2አሕዛብ ሳላችሁ በማናቸውም ጊዜ እንደምትመሩ ድምፅ ወደሌላቸው ወደ ጣዖታት እንደ ተወሰዳችሁ ታውቃላችሁ።
3wherefore, I give you to understand that no one, in the Spirit of God speaking, saith Jesus [is] anathema, and no one is able to say Jesus [is] Lord, except in the Holy Spirit.
3ስለዚህ ማንም በእግዚአብሔር መንፈስ ሲናገር። ኢየሱስ የተረገመ ነው የሚል እንደሌለ፥ በመንፈስ ቅዱስም ካልሆነ በቀር። ኢየሱስ ጌታ ነው ሊል አንድ እንኳ እንዳይችል አስታውቃችኋለሁ።
4And there are diversities of gifts, and the same Spirit;
4የጸጋም ስጦታ ልዩ ልዩ ነው መንፈስ ግን አንድ ነው፤
5and there are diversities of ministrations, and the same Lord;
5አገልግሎትም ልዩ ልዩ ነው ጌታም አንድ ነው፤
6and there are diversities of workings, and it is the same God — who is working the all in all.
6አሠራርም ልዩ ልዩ ነው፥ ሁሉን በሁሉ የሚያደርግ እግዚአብሔር ግን አንድ ነው።
7And to each hath been given the manifestation of the Spirit for profit;
7ነገር ግን መንፈስ ቅዱስን መግለጥ ለእያንዳንዱ ለጥቅም ይሰጠዋል።
8for to one through the Spirit hath been given a word of wisdom, and to another a word of knowledge, according to the same Spirit;
8ለአንዱ ጥበብን መናገር በመንፈስ ይሰጠዋልና፥ ለአንዱም በዚያው መንፈስ እውቀትን መናገር ይሰጠዋል፥
9and to another faith in the same Spirit, and to another gifts of healings in the same Spirit;
9ለአንዱም በዚያው መንፈስ እምነት፥ ለአንዱም በአንዱ መንፈስ የመፈወስ ስጦታ፥ ለአንዱም ተአምራትን ማድረግ፥
10and to another in-workings of mighty deeds; and to another prophecy; and to another discernings of spirits; and to another [divers] kinds of tongues; and to another interpretation of tongues:
10ለአንዱም ትንቢትን መናገር፥ ለአንዱም መናፍስትን መለየት፥ ለአንዱም በልዩ ዓይነት ልሳን መናገር፥ ለአንዱም በልሳኖች የተነገረውን መተርጎም ይሰጠዋል፤
11and all these doth work the one and the same Spirit, dividing to each severally as he intendeth.
11ይህን ሁሉ ግን ያ አንዱ መንፈስ እንደሚፈቅድ ለእያንዳንዱ ለብቻው እያካፈለ ያደርጋል።
12For, even as the body is one, and hath many members, and all the members of the one body, being many, are one body, so also [is] the Christ,
12አካልም አንድ እንደ ሆነ ብዙም ብልቶች እንዳሉበት ነገር ግን የአካል ብልቶች ሁሉ ብዙዎች ሳሉ አንድ አካል እንደ ሆኑ፥ ክርስቶስ ደግሞ እንዲሁ ነው፤
13for also in one Spirit we all to one body were baptized, whether Jews or Greeks, whether servants or freemen, and all into one Spirit were made to drink,
13አይሁድ ብንሆን የግሪክ ሰዎችም ብንሆን ባሪያዎችም ብንሆን ጨዋዎችም ብንሆን እኛ ሁላችን በአንድ መንፈስ አንድ አካል እንድንሆን ተጠምቀናልና። ሁላችንም አንዱን መንፈስ ጠጥተናል።
14for also the body is not one member, but many;
14አካል ብዙ ብልቶች እንጂ አንድ ብልት አይደለምና።
15if the foot may say, `Because I am not a hand, I am not of the body;` it is not, because of this, not of the body;
15እግር። እኔ እጅ አይደለሁምና የአካል ክፍል አይደለሁም ብትል፥ ይህን በማለትዋ የአካል ክፍል መሆንዋ ይቀራልን?
16and if the ear may say, `Because I am not an eye, I am not of the body;` it is not, because of this, not of the body?
16ጆሮም። እኔ ዓይን አይደለሁምና የአካል ክፍል አይደለሁም ቢል፥ ይህን በማለቱ የአካል ክፍል መሆኑ ይቀራልን?
17If the whole body [were] an eye, where the hearing? if the whole hearing, where the smelling?
17አካል ሁሉ ዓይን ቢሆን መስማት ወዴት በተገኘ? ሁሉም መስማት ቢሆን ማሽተት ወዴት በተገኘ?
18and now, God did set the members each one of them in the body, according as He willed,
18አሁን ግን እግዚአብሔር እንደ ወደደ ብልቶችን እያንዳንዳቸው በአካል አድርጎአል።
19and if all were one member, where the body?
19ሁሉም አንድ ብልት ቢሆንስ አካል ወዴት በሆነ?
20and now, indeed, [are] many members, and one body;
20ዳሩ ግን አሁን ብልቶች ብዙዎች ናቸው አካል ግን አንድ ነው።
21and an eye is not able to say to the hand, `I have no need of thee;` nor again the head to the feet, `I have no need of you.`
21ዓይን እጅን። አታስፈልገኝም ልትለው አትችልም፥ ወይም ራስ ደግሞ እግሮችን። አታስፈልጉኝም ሊላቸው አይችልም።
22But much more the members of the body which seem to be more infirm are necessary,
22ነገር ግን ደካሞች የሚመስሉ የአካል ብልቶች ይልቁን የሚያስፈልጉ ናቸው፤
23and those that we think to be less honourable of the body, around these we put more abundant honour, and our unseemly things have seemliness more abundant,
23ከአካልም ብልቶች ያልከበሩ ሆነው የሚመስሉን በሚበዛ ክብር እናለብሳቸዋለን፥ በምናፍርባቸውም ብልቶቻችን ክብር ይጨመርላቸዋል፤
24and our seemly things have no need; but God did temper the body together, to the lacking part having given more abundant honour,
24ክብር ያላቸው ብልቶቻችን ግን ይህ አያስፈልጋቸውም። ነገር ግን ብልቶች እርስ በርሳቸው በትክክል ይተሳሰቡ ዘንድ እንጂ በአካል መለያየት እንዳይሆን፥ ለጎደለው ብልት የሚበልጥ ክብር እየሰጠ እግዚአብሔር አካልን አገጣጠመው።
25that there may be no division in the body, but that the members may have the same anxiety for one another,
26አንድም ብልት ቢሣቀይ ብልቶች ሁሉ ከእርሱ ጋር ይሣቀያሉ፤ አንድ ብልትም ቢከበር ብልቶች ሁሉ ከእርሱ ጋር ደስ ይላቸዋል።
26and whether one member doth suffer, suffer with [it] do all the members, or one member is glorified, rejoice with [it] do all the members;
27እናንተም የክርስቶስ አካል ናችሁ እያንዳንዳችሁም ብልቶች ናችሁ።
27and ye are the body of Christ, and members in particular.
28እግዚአብሔርም በቤተ ክርስቲያን አንዳንዶቹን አስቀድሞ ሐዋርያትን፥ ሁለተኛም ነቢያትን፥ ሦስተኛም አስተማሪዎችን፥ ቀጥሎም ተአምራት ማድረግን፥ ቀጥሎም የመፈወስን ስጦታ፥ እርዳታንም፥ አገዛዝንም፥ የልዩ ልዩ ዓይነት ልሳኖችንም አድርጎአል።
28And some, indeed, did God set in the assembly, first apostles, secondly prophets, thirdly teachers, afterwards powers, afterwards gifts of healings, helpings, governings, divers kinds of tongues;
29ሁሉ ሐዋርያት ናቸውን? ሁሉስ ነቢያት ናቸውን? ሁሉስ አስተማሪዎች ናቸውን? ሁሉስ ተአምራትን ይሠራሉን?
29[are] all apostles? [are] all prophets? [are] all teachers? [are] all powers?
30ሁሉስ የመፈወስ ስጦታ አላቸውን? ሁሉስ በልሳኖች ይናገራሉን? ሁሉስ ይተረጉማሉን?
30have all gifts of healings? do all speak with tongues? do all interpret?
31ነገር ግን የሚበልጠውን የጸጋ ስጦታ በብርቱ ፈልጉ። ደግሞም ከሁሉ የሚበልጥ መንገድ አሳያችኋለሁ።
31and desire earnestly the better gifts; and yet a far excelling way do I shew to you: