1Followers of me become ye, as I also [am] of Christ.
1እኔ ክርስቶስን እንደምመስል እኔን ምሰሉ።
2And I praise you, brethren, that in all things ye remember me, and according as I did deliver to you, the deliverances ye keep,
2ወንድሞች ሆይ፥ በሁሉ ስለምታስቡኝና አሳልፌ እንደ ሰጠኋችሁ ወግን ፈጽማችሁ ስለ ያዛችሁ አመሰግናችኋለሁ።
3and I wish you to know that of every man the head is the Christ, and the head of a woman is the husband, and the head of Christ is God.
3ነገር ግን የወንድ ሁሉ ራስ ክርስቶስ፥ የሴትም ራስ ወንድ፥ የክርስቶስም ራስ እግዚአብሔር እንደ ሆነ ልታውቁ እወዳለሁ።
4Every man praying or prophesying, having the head covered, doth dishonour his head,
4ራሱን ተከናንቦ የሚጸልይ ወይም ትንቢት የሚናገር ወንድ ሁሉ ራሱን ያዋርዳል።
5and every woman praying or prophesying with the head uncovered, doth dishonour her own head, for it is one and the same thing with her being shaven,
5ራስዋን ሳትሸፍን ግን የምትጸልይ ወይም ትንቢት የምትናገር ሴት ሁሉ ራስዋን ታዋርዳለች፤ እንደ ተላጨች ያህል አንድ ነውና።
6for if a woman is not covered — then let her be shorn, and if [it is] a shame for a woman to be shorn or shaven — let her be covered;
6ሴትም ራስዋን ባትሸፍን ጠጉርዋን ደግሞ ትቆረጥ፤ ለሴት ግን ጠጉርዋን መቆረጥ ወይም መላጨት የሚያሳፍር ከሆነ ራስዋን ትሸፍን።
7for a man, indeed, ought not to cover the head, being the image and glory of God, and a woman is the glory of a man,
7ወንድ የእግዚአብሔር ምሳሌና ክብር ስለ ሆነ ራሱን መከናነብ አይገባውም፤ ሴት ግን የወንድ ክብር ናት።
8for a man is not of a woman, but a woman [is] of a man,
8ሴት ከወንድ ናት እንጂ ወንድ ከሴት አይደለምና።
9for a man also was not created because of the woman, but a woman because of the man;
9ሴት ስለ ወንድ ተፈጠረች እንጂ ወንድ ስለ ሴት አልተፈጠረምና።
10because of this the woman ought to have [a token of] authority upon the head, because of the messengers;
10ስለዚህ ሴት ከመላእክት የተነሣ በራስዋ ሥልጣን ሊኖራት ይገባል።
11but neither [is] a man apart from a woman, nor a woman apart from a man, in the Lord,
11ነገር ግን በጌታ ዘንድ ሴት ያለ ወንድ ወንድም ያለ ሴት አይሆንም።
12for as the woman [is] of the man, so also the man [is] through the woman, and the all things [are] of God.
12ሴት ከወንድ እንደ ሆነች እንዲሁ ወንድ ደግሞ በሴት ነውና፤ ሁሉም ከእግዚአብሔር ነው።
13In your own selves judge ye; is it seemly for a woman uncovered to pray to God?
13በእናንተ በራሳችሁ መካከል ፍረዱ፤ ሴት ራስዋን ሳትሸፍን ወደ እግዚአብሔር ልትጸልይ ይገባታልን?
14doth not even nature itself teach you, that if a man indeed have long hair, a dishonour it is to him?
14ወንድ ጠጉሩን ቢያስረዝም ነውር እንዲሆንበት፥ ሴት ግን ጠጉርዋን ብታስረዝም ክብር እንዲሆንላት ተፈጥሮ እንኳ አያስተምራችሁምን? ጠጉርዋ መጎናጸፊያ ሊሆን ተሰጥቶአታልና።
15and a woman, if she have long hair, a glory it is to her, because the hair instead of a covering hath been given to her;
16ዳሩ ግን ማንም ሊከራከር ቢፈቅድ፥ እኛ ወይም የእግዚአብሔር አብያተ ክርስቲያናት እንዲህ ያለ ልማድ የለንም።
16and if any one doth think to be contentious, we have no such custom, neither the assemblies of God.
17ነገር ግን በምትሰበሰቡበት ጊዜ ለሚከፋ እንጂ ለሚሻል ስላልሆነ ይህን ትእዛዝ ስሰጥ የማመሰግናችሁ አይደለም።
17And this declaring, I give no praise, because not for the better, but for the worse ye come together;
18በመጀመሪያ ወደ ማኅበር ስትሰበሰቡ በመካከላችሁ መለያየት እንዳለ እሰማለሁና፥ በአንድ በኩልም አምናለሁ።
18for first, indeed, ye coming together in an assembly, I hear of divisions being among you, and partly I believe [it],
19በእናንተ ዘንድ የተፈተኑት እንዲገለጡ በመካከላችሁ ወገኖች ደግሞ ሊሆኑ ግድ ነውና።
19for it behoveth sects also to be among you, that those approved may become manifest among you;
20እንግዲህ አብራችሁ ስትሰበሰቡ የምትበሉት የጌታ እራት አይደለም፤
20ye, then, coming together at the same place — it is not to eat the Lord`s supper;
21በመብላት ጊዜ እያንዳንዱ የራሱን እራት ይበላልና፥ አንዱም ይራባል አንዱ ግን ይሰክራል።
21for each his own supper doth take before in the eating, and one is hungry, and another is drunk;
22የምትበሉባቸውና የምትጠጡባቸው ቤቶች የላችሁምን? ወይስ የእግዚአብሔርን ማኅበር ትንቃላችሁን አንዳችም የሌላቸውን ታሳፍራላችሁን? ምን ልበላችሁ? በዚህ ነገር ላመስግናችሁን? አላመሰግናችሁም።
22why, have ye not houses to eat and to drink in? or the assembly of God do ye despise, and shame those not having? what may I say to you? shall I praise you in this? I do not praise!
23ለእናንተ ደግሞ አሳልፌ የሰጠሁትን እኔ ከጌታ ተቀብያለሁና፤
23For I — I received from the Lord that which also I did deliver to you, that the Lord Jesus in the night in which he was delivered up, took bread,
24ጌታ ኢየሱስ አልፎ በተሰጠበት በዚያች ሌሊት እንጀራን አንሥቶ አመሰገነ፥ ቆርሶም። እንካችሁ ብሉ፤ ይህ ስለ እናንተ የሚሆን ሥጋዬ ነው፤ ይህን ለመታሰቢያዬ አድርጉት አለ።
24and having given thanks, he brake, and said, `Take ye, eat ye, this is my body, that for you is being broken; this do ye — to the remembrance of me.`
25እንደዚሁም ከእራት በኋላ ጽዋውን ደግሞ አንሥቶ። ይህ ጽዋ በደሜ የሚሆን አዲስ ኪዳን ነው፤ በጠጣችሁት ጊዜ ሁሉ ይህን ለመታሰቢያዬ አድርጉት አለ።
25In like manner also the cup after the supping, saying, `This cup is the new covenant in my blood; this do ye, as often as ye may drink [it] — to the remembrance of me;`
26ይህን እንጀራ በበላችሁ ጊዜ ሁሉ፥ ይህንም ጽዋ በጠጣችሁ ጊዜ ሁሉ ጌታ እስኪመጣ ድረስ ሞቱን ትናገራላችሁና።
26for as often as ye may eat this bread, and this cup may drink, the death of the Lord ye do shew forth — till he may come;
27ስለዚህ ሳይገባው ይህን እንጀራ የበላ ወይም የጌታን ጽዋ የጠጣ ሁሉ የጌታ ሥጋና ደም ዕዳ አለበት።
27so that whoever may eat this bread or may drink the cup of the Lord unworthily, guilty he shall be of the body and blood of the Lord:
28ሰው ግን ራሱን ይፈትን፥ እንዲሁም ከእንጀራው ይብላ ከጽዋውም ይጠጣ፤
28and let a man be proving himself, and so of the bread let him eat, and of the cup let him drink;
29ሳይገባው የሚበላና የሚጠጣ የጌታን ሥጋ ስለማይለይ ለራሱ ፍርድ ይበላልና፥ ይጠጣልምና።
29for he who is eating and drinking unworthily, judgment to himself he doth eat and drink — not discerning the body of the Lord.
30ስለዚህ በእናንተ ዘንድ የደከሙና የታመሙ ብዙዎች አሉ አያሌዎችም አንቀላፍተዋል።
30Because of this, among you many [are] weak and sickly, and sleep do many;
31ራሳችንን ብንመረምር ግን ባልተፈረደብንም ነበር፤
31for if ourselves we were discerning, we would not be being judged,
32ነገር ግን በተፈረደብን ጊዜ ከዓለም ጋር እንዳንኮነን በጌታ እንገሠጻለን።
32and being judged by the Lord, we are chastened, that with the world we may not be condemned;
33ስለዚህ፥ ወንድሞቼ ሆይ፥ ለመብላት በተሰበሰባችሁ ጊዜ እርስ በርሳችሁ ተጠባበቁ።
33so then, my brethren, coming together to eat, for one another wait ye;
34ማንም የራበው ቢኖር ለፍርድ እንዳትሰበሰቡ በቤቱ ይብላ። የቀረውንም ነገር በመጣሁ ጊዜ እደነግጋለሁ።
34and if any one is hungry, at home let him eat, that to judgment ye may not come together; and the rest, whenever I may come, I shall arrange.