Young`s Literal Translation

Amharic: New Testament

1 Corinthians

10

1And I do not wish you to be ignorant, brethren, that all our fathers were under the cloud, and all passed through the sea,
1ወንድሞች ሆይ፥ ይህን ታውቁ ዘንድ እወዳለሁ። አባቶቻችን ሁሉ ከደመና በታች ነበሩ ሁሉም በባሕር መካከል ተሻገሩ፤
2and all to Moses were baptized in the cloud, and in the sea;
2ሁሉም ሙሴን ይተባበሩ ዘንድ በደመናና በባሕር ተጠመቁ፤
3and all the same spiritual food did eat,
3ሁሉም ያን መንፈሳዊ መብል በሉ ሁሉም ያን መንፈሳዊ መጠጥ ጠጡ፤
4and all the same spiritual drink did drink, for they were drinking of a spiritual rock following them, and the rock was the Christ;
4ይከተላቸው ከነበረው ከመንፈሳዊ ዓለት ጠጥተዋልና፥ ያም ዓለት ክርስቶስ ነበረ።
5but in the most of them God was not well pleased, for they were strewn in the wilderness,
5እግዚአብሔር ግን ከእነርሱ በሚበዙት ደስ አላለውም፥ በምድረ በዳ ወድቀዋልና።
6and those things became types of us, for our not passionately desiring evil things, as also these did desire.
6እነዚህም ክፉ ነገር እንደ ተመኙ እኛ ደግሞ እንዳንመኝ ይህ ምሳሌ ሆነልን።
7Neither become ye idolaters, as certain of them, as it hath been written, `The people sat down to eat and to drink, and stood up to play;`
7ሕዝብም ሊበሉ ሊጠጡም ተቀመጡ ሊዘፍኑም ተነሡ ተብሎ እንደ ተጻፈ ከእነርሱ አንዳንዶቹ እንዳደረጉት ጣዖትን የምታመልኩ አትሁኑ።
8neither may we commit whoredom, as certain of them did commit whoredom, and there fell in one day twenty-three thousand;
8ከእነርሱም አንዳንዶቹ እንደ ሴሰኑ በአንድ ቀንም ሁለት እልፍ ከሦስት ሺህ እንደ ወደቁ አንሴስን።
9neither may we tempt the Christ, as also certain of them did tempt, and by the serpents did perish;
9ከእነርሱም አንዳንዶቹ ጌታን እንደ ተፈታተኑት በእባቦቹም እንደ ጠፉ ጌታን አንፈታተን።
10neither murmur ye, as also some of them did murmur, and did perish by the destroyer.
10ከእነርሱም አንዳንዶቹ እንዳንጎራጎሩ በሚያጠፋውም እንደ ጠፉ አታንጐርጕሩ።
11And all these things as types did happen to those persons, and they were written for our admonition, to whom the end of the ages did come,
11ይህም ሁሉ እንደ ምሳሌ ሆነባቸው፥ እኛንም የዘመናት መጨረሻ የደረሰብንን ሊገሥጸን ተጻፈ።
12so that he who is thinking to stand — let him observe, lest he fall.
12ስለዚህ እንደ ቆመ የሚመስለው እንዳይወድቅ ይጠንቀቅ።
13No temptation hath taken you — except human; and God is faithful, who will not suffer you to be tempted above what ye are able, but He will make, with the temptation, also the outlet, for your being able to bear [it].
13ለሰው ሁሉ ከሚሆነው በቀር ምንም ፈተና አልደረሰባችሁም፤ ነገር ግን ከሚቻላችሁ መጠን ይልቅ ትፈተኑ ዘንድ የማይፈቅድ እግዚአብሔር የታመነ ነው፥ ትታገሡም ዘንድ እንድትችሉ ከፈተናው ጋር መውጫውን ደግሞ ያደርግላችኋል።
14Wherefore, my beloved, flee from the idolatry;
14ስለዚህ፥ ወዳጆቼ ሆይ፥ ጣዖትን ከማምለክ ሽሹ።
15as to wise men I speak — judge ye what I say:
15ልባሞች እንደ መሆናችሁ እላለሁ፤ በምለው ነገር እናንተ ፍረዱ።
16The cup of the blessing that we bless — is it not the fellowship of the blood of the Christ? the bread that we break — is it not the fellowship of the body of the Christ?
16የምንባርከው የበረከት ጽዋ ከክርስቶስ ደም ጋር ኅብረት ያለው አይደለምን? የምንቆርሰውስ እንጀራ ከክርስቶስ ሥጋ ጋር ኅብረት ያለው አይደለምን?
17because one bread, one body, are we the many — for we all of the one bread do partake.
17አንድ እንጀራ ስለ ሆነ፥ እኛ ብዙዎች ስንሆን አንድ ሥጋ ነን፤ ሁላችን ያን አንዱን እንጀራ እንካፈላለንና።
18See Israel according to the flesh! are not those eating the sacrifices in the fellowship of the altar?
18በሥጋ የሆነውን እስራኤል ተመልከቱ፤ መሥዋዕቱን የሚበሉ የመሠዊያው ማኅበረተኞች አይደሉምን?
19what then do I say? that an idol is anything? or that a sacrifice offered to an idol is anything? —
19እንግዲህ ምን እላለሁ? ለጣዖት የተሠዋ ምናምን ነው እላለሁን? ወይስ ጣዖት ምናምን እንዲሆን እላለሁን?
20[no,] but that the things that the nations sacrifice — they sacrifice to demons and not to God; and I do not wish you to come into the fellowship of the demons.
20አይደለም፤ ነገር ግን አሕዛብ የሚሠዉት ለአጋንንት እንዲሆን እንጂ ለእግዚአብሔር እንዳይሠዉ እላለሁ፤ ከአጋንንትም ጋር ማኅበረተኞች እንድትሆኑ አልወድም።
21Ye are not able the cup of the Lord to drink, and the cup of demons; ye are not able of the table of the Lord to partake, and of the table of demons;
21የጌታን ጽዋና የአጋንንትን ጽዋ ልትጠጡ አትችሉም፤ ከጌታ ማዕድና ከአጋንንት ማዕድ ልትካፈሉ አትችሉም።
22do we arouse the Lord to jealousy? are we stronger than He?
22ወይስ ጌታን እናስቀናውን? እኛስ ከእርሱ ይልቅ እንበረታለንን?
23All things to me are lawful, but all things are not profitable; all things to me are lawful, but all things do not build up;
23ሁሉ ተፈቅዶልኛል፥ ሁሉ ግን የሚጠቅም አይደለም፤ ሁሉ ተፈቅዶልኛል፥ ነገር ግን ሁሉ የሚያንጽ አይደለም።
24let no one seek his own — but each another`s.
24እያንዳንዱ የባልንጀራውን ጥቅም እንጂ አንድ ስንኳ የራሱን ጥቅም አይፈልግ።
25Whatever in the meat-market is sold eat ye, not inquiring, because of the conscience,
25በሥጋ ገበያ የሚሸጠውን ሁሉ ከሕሊና የተነሣ ሳትመራመሩ ብሉ፤
26for the Lord`s [is] the earth, and its fulness;
26ምድርና በእርስዋ የሞላባት ሁሉ የጌታ ነውና።
27and if any one of the unbelieving do call you, and ye wish to go, all that is set before you eat, nothing inquiring, because of the conscience;
27ከማያምኑ ሰዎች አንዱም ቢጠራችሁ ልትሄዱም ብትወዱ ከሕሊና የተነሣ ሳትመራመሩ የሚያቀርቡላችሁን ሁሉ ብሉ።
28and if any one may say to you, `This is a thing sacrificed to an idol,` — do not eat, because of that one who shewed [it], and of the conscience, for the Lord`s [is] the earth and its fulness:
28ማንም ግን። ይህ ለጣዖት የተሠዋ ነው ቢላችሁ ከዚያ ካስታወቃችሁና ከሕሊና የተነሣ አትብሉ፤
29and conscience, I say, not of thyself, but of the other, for why [is it] that my liberty is judged by another`s conscience?
29ስለ ባልንጀራህ ሕሊና እንጂ ስለ ገዛ ሕሊናህ አልናገርም። አርነቴ በሌላ ሰው ሕሊና የሚፈርድ Avረ ስለ ምንድር ነው?
30and if I thankfully do partake, why am I evil spoken of, for that for which I give thanks?
30እኔም በጸጋ ብበላ፥ በነገሩ ስለማመሰግንበት ስለ ምን እሰደባለሁ?
31Whether, then, ye eat, or drink, or do anything, do all to the glory of God;
31እንግዲህ የምትበሉ ወይም የምትጠጡ ብትሆኑ ወይም ማናቸውን ነገር ብታደርጉ ሁሉን ለእግዚአብሔር ክብር አድርጉት።
32become offenceless, both to Jews and Greeks, and to the assembly of God;
32እኔ ደግሞ ብዙዎቹ ይድኑ ዘንድ ለጥቅማቸው እንጂ የራሴን ጥቅም ሳልፈልግ በሁሉ ነገር ሰውን ሁሉ ደስ እንደማሰኝ፥ ለአይሁድም ለግሪክም ሰዎች ለእግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንም ማሰናከያ አትሁኑ።
33as I also in all things do please all, not seeking my own profit, but that of many — that they may be saved.