Young`s Literal Translation

Amharic: New Testament

1 Corinthians

9

1Am not I an apostle? am not I free? Jesus Christ our Lord have I not seen? my work are not ye in the Lord?
1እኔ ነጻ አይደለሁምን? ሐዋርያስ አይደለሁምን? ጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስንስ አላየሁትምን? እናንተስ በጌታ ሥራዬ አይደላችሁምን?
2if to others I am not an apostle — yet doubtless to you I am; for the seal of my apostleship are ye in the Lord.
2የሐዋርያነቴ ማኅተም በጌታ እናንተ ናችሁና ለሌሎች ሐዋርያ ባልሆን ለእናንተስ ምንም ቢሆን ሐዋርያ ነኝ።
3My defence to those who examine me in this;
3ለሚመረምሩኝ መልሴ ይህ ነው። ልንበላና ልንጠጣ መብት የለንምን?
4have we not authority to eat and to drink?
5እንደ ሌሎቹ ሐዋርያትና እንደ ጌታ ወንድሞች እንደ ኬፋም፥ እኅት ሚስታችንን ይዘን ልንዞር መብት የለንምን?
5have we not authority a sister — a wife — to lead about, as also the other apostles, and the brethren of the Lord, and Cephas?
6ወይስ ሥራን ለመተው መብት የሌለን እኔና በርናባስ ብቻ ነን?
6or only I and Barnabas, have we not authority — not to work?
7ከቶ በገዛ ገንዘቡ በወታደርነት የሚያገለግል ማን ነው? ወይስ ወይን ተክሎ ፍሬውን የማይበላ ማን ነው? ወይስ መንጋ እየጠበቀ ከመንጋው ወተት የማይጠጣ ማን ነው?
7who doth serve as a soldier at his own charges at any time? who doth plant a vineyard, and of its fruit doth not eat? or who doth feed a flock, and of the milk of the flock doth not eat?
8ይህን በሰው ሥልጣን ብቻ እላለሁን?
8According to man do I speak these things? or doth not also the law say these things?
9ሕግስ ደግሞ ያን አይልምን? የሚያበራየውን በሬ አፉን አትሰር ተብሎ በሙሴ ሕግ ተጽፎአልና። እግዚአብሔርስ ስለ በሬዎች ይገደዋልን?
9for in the law of Moses it hath been written, `thou shalt not muzzle an ox treading out corn;` for the oxen doth God care?
10ይህን የሚለው ፈጽሞ ስለ እኛ አይደለምን? የሚያርስ በተስፋ ሊያርስ የሚያበራይም እንዲካፈል በተስፋ ሊያበራይ ስለሚገባው በእውነት ስለ እኛ ተጽፎአል።
10or because of us by all means doth He say [it]? yes, because of us it was written, because in hope ought the plower to plow, and he who is treading [ought] of his hope to partake in hope.
11እኛ መንፈሳዊን ነገር የዘራንላችሁ ከሆንን የእናንተን የሥጋዊን ነገር እኛ ብናጭድ ትልቅ ነገር ነውን?
11If we to you the spiritual things did sow — great [is it] if we your fleshly things do reap?
12ሌሎች በእናንተ ላይ ይህን መብት የሚካፈሉ ከሆኑ እኛማ ይልቁን እንዴታ? ነገር ግን የክርስቶስን ወንጌል እንዳንከለክል በሁሉ እንታገሣለን እንጂ በዚህ መብት አልተጠቀምንም።
12if others do partake of the authority over you — not we more? but we did not use this authority, but all things we bear, that we may give no hindrance to the good news of the Christ.
13በመቅደስ ነገር የሚያገለግሉ ከመቅደስ የሆነውን ነገርን እንዲመገቡ፥ በመሠዊያውም የሚጸኑ ከመሠዊያው እንዲካፈሉ አታውቁምን?
13Have ye not known that those working about the things of the temple — of the temple do eat, and those waiting at the altar — with the altar are partakers?
14እንዲሁ ደግሞ ወንጌልን የሚሰብኩ ከወንጌል ቀለብ እንዲቀበሉ ጌታ ደንግጎአል።
14so also did the Lord direct to those proclaiming the good news: of the good news to live.
15እኔ ግን ከእነዚህ ሁሉ ምንም አልተጠቀምሁም። እንዲህ እንዲሆንልኝ ይህን አልጽፍም፤ ማንም ትምክህቴን ከንቱ ከሚያደርግብኝ ሞት ይሻለኛልና።
15And I have used none of these things; neither did I write these things that it may be so done in my case, for [it is] good for me rather to die, than that any one may make my glorying void;
16ወንጌልን ብሰብክ እንኳ የምመካበት የለኝም፤ ግድ ደርሶብኝ ነውና፤ ወንጌልንም ባልሰብክ ወዮልኝ።
16for if I may proclaim good news, it is no glorying for me, for necessity is laid upon me, and wo is to me if I may not proclaim good news;
17ይህን በፈቃዴ ባደርገው ደመወዝ አለኝና፤ ያለ ፈቃዴ ግን ባደርገው መጋቢነት በአደራ ተሰጥቶኛል።
17for if willing I do this, I have a reward; and if unwillingly — with a stewardship I have been entrusted!
18እንግዲህ ደመወዜ ምንድር ነው? ወንጌልን እየሰበክሁ በወንጌል ካለኝ መብት በሙሉ እንዳልጠቀም ወንጌልን ያለ ዋጋ ብናገር ነው።
18What, then, is my reward? — that proclaiming good news, without charge I shall make the good news of the Christ, not to abuse my authority in the good news;
19ከሰው ሁሉ አርነት የወጣሁ ስሆን የሚበልጡትን እንድጠቅም እንደ ባሪያ ራሴን ለሁሉ አስገዛለሁ።
19for being free from all men, to all men I made myself servant, that the more I might gain;
20አይሁድንም እጠቅም ዘንድ ከአይሁድ ጋር እንደ አይሁዳዊ ሆንሁ፤ ከሕግ በታች ያሉትን እጠቅም ዘንድ፥ እኔ ራሴ ከሕግ በታች ሳልሆን፥ ከሕግ በታች ላሉት ከሕግ በታች እንዳለሁ ሆንሁ፤
20and I became to the Jews as a Jew, that Jews I might gain; to those under law as under law, that those under law I might gain;
21ሕግ የሌላቸውን እጠቅም ዘንድ፥ ያለ እግዚአብሔር ህግ ሳልኖር ነገር ግን በክርስቶስ ሕግ በታች ሳለሁ፥ ሕግ ለሌላቸው ሕግ እንደ ሌለኝ ሆንሁ፤
21to those without law, as without law — (not being without law to God, but within law to Christ) — that I might gain those without law;
22ደካሞችን እጠቅም ዘንድ ለደካሞች እንደ ደካማ ሆንሁ፤ በሁሉ መንገድ አንዳንዶችን አድን ዘንድ፥ ከሁሉ ጋር በሁሉ ነገር እንደ እነርሱ ሆንሁ።
22I became to the infirm as infirm, that the infirm I might gain; to all men I have become all things, that by all means I may save some.
23በወንጌልም ማኅበረተኛ እሆን ዘንድ ስለ ወንጌል ሁሉን አደርጋለሁ።
23And this I do because of the good news, that a fellow-partaker of it I may become;
24በእሽቅድምድም ስፍራ የሚሮጡት፥ ሁሉ እንዲሮጡ ነገር ግን አንዱ ብቻ ዋጋውን እንዲቀበል አታውቁምን? እንዲሁም ታገኙ ዘንድ ሩጡ።
24have ye not known that those running in a race — all indeed run, but one doth receive the prize? so run ye, that ye may obtain;
25የሚታገልም ሁሉ በነገር ሁሉ ሰውነቱን ይገዛል፤ እነዚያም የሚጠፋውን አክሊል ሊያገኙ ነው፥ እኛ ግን የማይጠፋውን።
25and every one who is striving, is in all things temperate; these, indeed, then, that a corruptible crown they may receive, but we an incorruptible;
26ስለዚህ እኔ ያለ አሳብ እንደሚሮጥ ሁሉ እንዲሁ አልሮጥም፥ ነፋስን እንደሚጎስም ሁሉ እንዲሁ አልጋደልም፤
26I, therefore, thus run, not as uncertainly, thus I fight, as not beating air;
27ነገር ግን ለሌሎች ከሰበክሁ በኋላ ራሴ የተጣልሁ እንዳልሆን ሥጋዬን እየጎሰምሁ አስገዛዋለሁ።
27but I chastise my body, and bring [it] into servitude, lest by any means, having preached to others — I myself may become disapproved.