Young`s Literal Translation

Amharic: New Testament

1 Corinthians

14

1Pursue the love, and seek earnestly the spiritual things, and rather that ye may prophecy,
1ፍቅርን ተከታተሉ፥ መንፈሳዊ ስጦታንም ይልቁንም ትንቢት መናገርን በብርቱ ፈልጉ።
2for he who is speaking in an [unknown] tongue — to men he doth not speak, but to God, for no one doth hearken, and in spirit he doth speak secrets;
2በልሳን የሚናገርስ ለእግዚአብሔር እንጂ ለሰው አይናገርም፤ የሚያስተውለው የለምና፥ በመንፈስ ግን ምሥጢርን ይናገራል፤
3and he who is prophesying to men doth speak edification, and exhortation, and comfort;
3ትንቢትን የሚናገር ግን ለማነጽና ለመምከር ለማጽናናትም ለሰው ይናገራል።
4he who is speaking in an [unknown] tongue, himself doth edify, and he who is prophesying, an assembly doth edify;
4በልሳን የሚናገር ራሱን ያንጻል፤ ትንቢትን የሚናገር ግን ማኅበሩን ያንጻል።
5and I wish you all to speak with tongues, and more that ye may prophecy, for greater is he who is prophesying than he who is speaking with tongues, except one may interpret, that the assembly may receive edification.
5ሁላችሁ በልሳኖች ልትናገሩ እወድ ነበር፥ ትንቢትን ልትናገሩ ግን ከዚህ ይልቅ እወዳለሁ፤ ማኅበሩ ይታነጽ ዘንድ ንግግሩን ባይተረጐም በልሳኖች ከሚናገር ትንቢትን የሚናገር ይበልጣል።
6And now, brethren, if I may come unto you speaking tongues, what shall I profit you, except I shall speak to you either in revelation, or in knowledge, or in prophesying, or in teaching?
6አሁን ግን፥ ወንድሞች ሆይ፥ ወደ እናንተ መጥቼ በልሳኖች ብናገር፥ በመግለጥ ወይም በእውቀት ወይም በትንቢት ወይም በትምህርት ካልነገርኋችሁ ምን እጠቅማችኋለሁ?
7yet the things without life giving sound — whether pipe or harp — if a difference in the sounds they may not give, how shall be known that which is piped or that which is harped?
7ነፍስ የሌለበት ነገር እንኳ ዋሽንትም ክራርም ቢሆን ድምፅ ሲሰጥ የድምፁን ልዩነት ባይገልጥ በዋሽንት የሚነፋው ወይስ በክራር የሚመታው መዝሙር እንዴት ይታወቃል?
8for if also an uncertain sound a trumpet may give, who shall prepare himself for battle?
8ደግሞም መለከት የማይገለጥን ድምፅ ቢሰጥ ለጦርነት ማን ይዘጋጃል?
9so also ye, if through the tongue, speech easily understood ye may not give — how shall that which is spoken be known? for ye shall be speaking to air.
9እንዲሁ እናንተ ደግሞ የተገለጠውን ቃል በአንደበት ባትናገሩ ሰዎች የምትናገሩትን እንዴት አድርገው ያስተውሉታል? ለነፋስ የምትናገሩ ትሆናላችሁና።
10There are, it may be, so many kinds of voices in the world, and none of them is unmeaning,
10በዓለም ምናልባት ቁጥር የሌለው የቋንቋ ዓይነት ይኖራል ቋንቋም የሌለው ሕዝብ የለም፤
11if, then, I do not know the power of the voice, I shall be to him who is speaking a foreigner, and he who is speaking, is to me a foreigner;
11እንግዲህ የቋንቋውን ፍች ባላውቅ ለሚናገረው እንግዳ እሆናለሁ፥ የሚናገረውም ለእኔ እንግዳ ይሆናል።
12so also ye, since ye are earnestly desirous of spiritual gifts, for the building up of the assembly seek that ye may abound;
12እንዲሁ ደግሞ እናንተ መንፈሳዊ ስጦታን በብርቱ የምትፈልጉ ከሆናችሁ ቤተ ክርስቲያንን ለማነጽ እንዲበዛላችሁ ፈልጉ።
13wherefore he who is speaking in an [unknown] tongue — let him pray that he may interpret;
13ስለዚህ በልሳን የሚናገር እንዲተረጉም ይጸልይ።
14for if I pray in an [unknown] tongue, my spirit doth pray, and my understanding is unfruitful.
14በልሳን ብጸልይ መንፈሴ ይጸልያል አእምሮዬ ግን ያለ ፍሬ ነው።
15What then is it? I will pray with the spirit, and I will pray also with the understanding; I will sing psalms with the spirit, and I will sing psalms also with the understanding;
15እንግዲህ ምንድር ነው? በመንፈስ እጸልያለሁ በአእምሮም ደግሞ እጸልያለሁ፤ በመንፈስ እዘምራለሁ በአእምሮም ደግሞ እዘምራለሁ።
16since, if thou mayest bless with the spirit, he who is filling the place of the unlearned, how shall he say the Amen at thy giving of thanks, since what thou dost say he hath not known?
16እንዲያማ ካልሆነ፥ አንተ በመንፈስ ብትባርክ ባልተማሩት ስፍራ የተቀመጠው የምትለውን ካላወቀ እንዴት አድርጎ ለምስጋናህ አሜን ይላል?
17for thou, indeed, dost give thanks well, but the other is not built up!
17አንተማ መልካም ታመሰግናለህ፥ ሌላው ግን አይታነጽበትም።
18I give thanks to my God — more than you all with tongues speaking —
18ከሁላችሁ ይልቅ በልሳኖች እናገራለሁና እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ፤
19but in an assembly I wish to speak five words through my understanding, that others also I may instruct, rather than myriads of words in an [unknown] tongue.
19ነገር ግን ሌሎችን ደግሞ አስተምር ዘንድ በማኅበር እልፍ ቃላት በልሳን ከመናገር ይልቅ አምስት ቃላት በአእምሮዬ ልናገር እወዳለሁ።
20Brethren, become not children in the understanding, but in the evil be ye babes, and in the understanding become ye perfect;
20ወንድሞች ሆይ፥ በአእምሮ ሕፃናት አትሁኑ፤ ለክፋት ነገር ሕፃናት ሁኑ እንጂ በአእምሮ የበሰሉ ሁኑ።
21in the law it hath been written, that, `With other tongues and with other lips I will speak to this people, and not even so will they hear Me, saith the Lord;`
21ሌሎችን ልሳኖች በሚናገሩ ሰዎችና በሌላ አንደበት ለዚህ ሕዝብ እነግራቸዋለሁ፥ እንዲህም ቢሆን አይሰሙኝም ይላል ጌታ ተብሎ በሕግ ተጽፎአል።
22so that the tongues are for a sign, not to the believing, but to the unbelieving; and the prophesy [is] not for the unbelieving, but for the believing,
22እንግዲያስ በልሳኖች መናገር ለማያምኑ ምልክት ነው እንጂ ለሚያምኑ አይደለም፥ ትንቢት ግን ለሚያምኑ እንጂ ለማያምኑ አይደለም።
23If, therefore, the whole assembly may come together, to the same place, and all may speak with tongues, and there may come in unlearned or unbelievers, will they not say that ye are mad?
23እንግዲህ ማኅበር ሁሉ አብረው ቢሰበሰቡ ሁሉም በልሳኖች ቢናገሩና ያልተማሩ ወይም የማያምኑ ሰዎች ቢገቡ። አብደዋል አይሉምን?
24and if all may prophecy, and any one may come in, an unbeliever or unlearned, he is convicted by all, he is discerned by all,
24ሁሉ ትንቢት ቢናገሩ ግን የማያምን ወይም ያልተማረ ሰው ቢገባ በሁሉ ይወቀሳል፥ በሁሉም ይመረመራል፤
25and so the secrets of his heart become manifest, and so having fallen upon [his] face, he will bow before God, declaring that God really is among you.
25በልቡም የተሰወረ ይገለጣል እንዲሁም። እግዚአብሔር በእውነት በመካከላቸው ነው ብሎ እየተናገረ በፊቱ ወድቆ ለእግዚአብሔር ይሰግዳል።
26What then is it, brethren? whenever ye may come together, each of you hath a psalm, hath a teaching, hath a tongue, hath a revelation, hath an interpretation? let all things be for building up;
26እንግዲህ፥ ወንድሞች ሆይ፥ ምንድር ነው? በምትሰበሰቡበት ጊዜ ለእያንዳንዱ መዝሙር አለው፥ ትምህርት አለው፥ መግለጥ አለው፥ በልሳን መናገር አለው፥ መተርጐም አለው፤ ሁሉ ለማነጽ ይሁን።
27if an [unknown] tongue any one do speak, by two, or at the most, by three, and in turn, and let one interpret;
27በልሳን የሚናገር ቢኖር ሁለት ወይም ቢበዛ ሦስት ሆነው በተራቸው ይናገሩ አንዱም ይተርጉም፤
28and if there may be no interpreter, let him be silent in an assembly, and to himself let him speak, and to God.
28የሚተረጉም ባይኖር ግን በማኅበር መካከል ዝም ይበልና ለራሱና ለእግዚአብሔር ይናገር።
29And prophets — let two or three speak, and let the others discern,
29ነቢያትም ሁለት ወይም ሦስት ሆነው ይናገሩ ሌሎችም ይለዩአቸው፤
30and if to another sitting [anything] may be revealed, let the first be silent;
30በዚያ ለሚቀመጥ ለሌላ ግን አንድ ነገር ቢገለጥለት ፊተኛው ዝም ይበል።
31for ye are able, one by one, all to prophesy, that all may learn, and all may be exhorted,
31ሁሉም እንዲማሩ ሁሉም እንዲመከሩ ሁላችሁ በእያንዳንዳችሁ ትንቢት ልትናገሩ ትችላላችሁ።
32and the spiritual gift of prophets to prophets are subject,
32የነቢያትም መናፍስት ለነቢያት ይገዛሉ፤
33for God is not [a God] of tumult, but of peace, as in all the assemblies of the saints.
33እግዚአብሔርስ የሰላም አምላክ ነው እንጂ የሁከት አምላክ አይደለምና፤ በቅዱሳንም አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ እንዲህ ነው።
34Your women in the assemblies let them be silent, for it hath not been permitted to them to speak, but to be subject, as also the law saith;
34ሴቶች በማኅበር ዝም ይበሉ፤ ሕግ ደግሞ እንደሚል እንዲገዙ እንጂ እንዲናገሩ አልተፈቀደላቸውምና።
35and if they wish to learn anything, at home their own husbands let them question, for it is a shame to women to speak in an assembly.
35ለሴት በማኅበር መካከል መናገር ነውር ነውና፥ ምንም ሊማሩ ቢወዱ በቤታቸው ባሎቻቸውን ይጠይቁ።
36From you did the word of God come forth? or to you alone did it come?
36ምን ነው? የእግዚአብሔር ቃል የወጣ ከእናንተ ነውን? ወይስ ወደ እናንተ ብቻ ደርሶአልን?
37if any one doth think to be a prophet, or spiritual, let him acknowledge the things that I write to you — that of the Lord they are commands;
37ማንም ነቢይ ወይም መንፈሳዊ የሆነ ቢመስለው ይህች የጻፍሁላችሁ የጌታ ትእዛዝ እንደ ሆነች ይወቅ፤
38and if any one is ignorant — let him be ignorant;
38ማንም የማያውቅ ቢኖር ግን አይወቅ።
39so that, brethren, earnestly desire to prophesy, and to speak with tongues do not forbid;
39ስለዚህ፥ ወንድሞች ሆይ፥ ትንቢት ለመናገር በብርቱ ፈልጉ፥ በልሳኖች ከመናገርም አትከልክሉ፤
40let all things be done decently and in order.
40ነገር ግን ሁሉ በአገባብና በሥርዓት ይሁን።